ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፴፮
"እንዲሁም ደግሞ መንፈስ ድካማችንን ያግዛል እንዴት እንድንጸልይ እንደሚገ፟ባ፟ን አናውቅምና፥ ነገር ግን፥ መንፈስ ራሱ በማይነገር መቃተት ይማልድልናል" (ሮሜ ፰፣፳፮)።
መንፈስ ቅዱስን ይማልድልናል እያለ ነው። ዋጋ መስጠትን መማለድ ብሎ የሚገልጽበት ወቅት አለ። ይኽውም ውጤቱን በመቅድሙ መጥራት ነው። መንፈስ ቅዱስ የተለያዩ መከራዎችን ስንቀበል ዋጋችንን ይሰጠናል። ከአብ ከወልድ ጋር አንድ ሆኖ ለምዕመናን ዋጋቸውን ይሰጣቸዋል። እግዚአብሔር ምእመናን እንዳይወድቁ ይማልድላቸዋል ማለት ጸጋውን ያድላቸዋል። ከእነርሱ ጋር በረድኤት ሆኖ የሚድኑበትን መንገድ ይገልጽላቸዋል ማለት ነው። ይማልድልናል የሚለው ቃል በግእዝ "ይትዋቀስ-ይከራከርልናል" ተብሏል። ይህ ከሆነ ደግሞ አብም እንደሚከራከርልን (እንደሚማልድልን) ተጽፏል። "ስለእርሳቸው ይከራከርላቸዋልና በጠላታቸምም እጅ አይጥላቸውምና ከሚጠሏቸው ከጠላቶቻቸው እጅ ያድናቸዋል" እንዲል (፩ኛ መቃ. ፳፣፫)። ትርጉሙ ዋጋን ይሰጠናል ማለት ነው።
© በትረማርያም አበባው
የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።
የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>
https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።
ክፍል ፪፻፴፯ ይቀጥላል