በትረማርያም አበባው Betremariam Abebaw


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Religion


አቀድም አእኵቶቶ ለእግዚአብሔር

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Religion
Statistics
Posts filter


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፶፭
"ቅዱሳን በዓለም ላይ እንዲፈርዱ አታውቁምን" (፩ኛ ቆሮ. ፮፣፪)።

ሐዋርያት ስለኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ አላስተማሩም። ስለጽድቅ ሥራዎች፣ ስለጾም፣ ስለጸሎት፣ በጠቅላላው ስለመልካም ሥራዎች አስተምረዋል። ከዚህም በተጨማሪ ክርስቶስ ባስተማረው ትምህርት ጸንተው ስለኖሩ ቅዱሳን አስተምረዋል። ቅዱሳን በዓለም እንደሚፈርዱ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በግልጽ ነግሮናል። የቅዱሳን ፍርድ የጸጋ ፍርድ ነው። ይኸውም ከፈጣሪ ባገኙት ጸጋ ይፈርዳሉ። እግዚአብሔር ይፈርዳል ስንል ግን በባሕርይው ፈራጅ መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል።

© በትረማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፶፮ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፶፬
"ፋሲካችን ክርስቶስ ታርዷልና" (፩ኛ ቆሮ. ፭፣፯)።

ፋሲካ ማለት ደስታ ማለት ነው። ደስታችን ክርስቶስ ታርዷል ማለት በመስቀል ላይ ሥጋውን ቆርሶ ደሙን አፍስሶ ሰጠን ማለት ነው። ስለዚህ ንስሓ ገብተን፣ ምግባር ትሩፋት ሠርተን መቀበል ይገባናል። ፋሲካ ማለት ሌላ ትርጉሙ መሻገሪያ ማለት ነው። "ፋሲካ ብሂል ማዕዶት ብሂል" እንዲል ቅዱስ ያሬድ (መጽሐፈ ድጓ)። በኢየሱስ ክርስቶስ ከባርነት ወደ ነጻነት፣ ከሲኦል ወደ ገነት፣ ከምግባረ ኃጢአት ወደ ምግባረ ጽድቅ አሸጋግሮናልና ፋሲካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ብሏል። በኦሪት ዘመን እስራኤላውያን በጉን አርደው ከግብፅ ባርነት ተላቀው ባሕረ ኤርትራን ተሻግረው ወደ ከነአን ገብተዋል። ያ በግ የክርስቶስ ምሳሌ ሆኖ ይነገራል።

© በትረማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፶፭ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፶፫
"ሁሉ የእናንተ ነው፥ እናንተም የክርስቶስ ናችኹ ክርስቶስም የእግዚአብሔር ነው" (፩ኛ ቆሮ. ፫፣፳፫)።

በክርስቶስ ስናምን ሁሉ የእኛ ይሆናል። ለዚያ ነው ሁሉ የእናንተ ነው የተባልነው። እናንተም የክርስቶስ ናችሁ ያለው በእርሱ ስም ተጠምቀን፣ በእርሱ ትምህርት ጸንተን፣ የእርሱን ሥጋ በልተን፣ የእርሱን ደም ጠጥተን ዘለዓለማዊ ሕይወትን ስለምናገኝ ነው። በሌላ አገላለጽ እናንተ የክርስቶስ ናቸው የሚለው የክርስቶስ የጸጋ ልጆች ናችሁ ማለት ነው። ክርስቶስም የእግዚአብሔር ነው የሚለው ቃል ደግሞ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እግዚአብሔር መሆኑን ያመለክታል። ይኽውም የአብ የባሕርይ ልጅ መሆኑን ያመለክታል።

© በትረማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፶፬ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፶፪
"ከተመሠረተው በቀር ማንም ሌላ መሠረት ሊመሠርት አይችልምና፥ ርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው" (፩ኛ ቆሮ. ፫፣፲፩)።

የሃይማኖታችን መሠረት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ይህንንም ለማመልከት በእርሱ ስም እንጠራለን። እርሱ ክርስቶስ እንደተባለ እኛም ክርስቲያን እንባላለን። እርሱ ናዝራዊ እንደተባለ እኛም ናዝራውያን እንባላለን። እርሱ መሲሕ እንደተባለ እኛም መሲሓውያን እንባላለን። በጠቅላላው የሃይማኖታችን መሠረት እርሱ ነው። ክርስቶስ ከመሠረተልን መሠረት ማለት ካስተማረን ትምህርት ውጭ ማንም ቢሆን ቢያስተምረን አንቀበለውም። እርሱ ካስተማረው ትምህርት አፈንግጠው ብዙዎች ከእርሱ በኋላ ተነሥተው እምነትን በራሳቸው የተሳሳተ አስተምህሮ መሥርተዋል። ነገር ግን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ካስተማረው ትምህርት ውጭ ማንም ቢሆን ሌላ ትምህርት እንዳያስተምር ተነግሮ ነበር። ስለዚህ ይህንን ቃል ባለመስማታቸው ራሳቸውን በራሳቸው ይጎዳሉ። እኛ ግን እርሱ ባስተማረን ትምህርት ጸንተን እንኖራለን።

© በትረማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፶፫ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፶፩
"ከእግዚአብሔር መንፈስ በቀር ለእግዚአብሔር ያለውን ማንም አያውቅም" (፩ኛ ቆሮ. ፪፣፲፩)።

"በቀር" የሚለው አገላለጽ ከፍጡራን ሲለየው ነው እንጂ ከወልድ ሲለየው አይደለም። አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ በዕውቀት አንድ ናቸው። ወልድ አብንም መንፈስ ቅዱስንም ያውቃቸዋል። መንፈስ ቅዱስ ወልድንም አብም ያውቃቸዋል። አብ ወልድንም መንፈስ ቅዱስንም ያውቃል። በሥላሴ ዘንድ የበላይና የበታች እያደረጉ የሚናገሩ ሰዎች በዚህ ኃይለ ቃል ይረታሉ። በጕስዐተ ልብ ከመንፈስ ቅዱስ ወልድ ይበልጣል ከወልድ አብ ይበልጣል እያሉ ይናገራሉ። ወልድን መንፈስ ቅዱስ አያውቀውም። አብን ወልድ አያውቀውን እያሉ መዓርግ ያበላልጣሉ። ከላይ ያለው ኃይለ ቃል እንደሚነግረን ግን መንፈስ ቅዱስ አብንም ወልድንም እንደሚያውቅና በባሕርይ አንድ መሆናቸውን የሚያመለክት ቃል ነው። ለእግዚአብሔር ያለውን የሚያውቅ እግዚአብሔር ነው። ከዚያ ውጭ ፍጡር እግዚአብሔርን በባሕርይው አይቶት አያውቅም።

© በትረማርያም አበባው


የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፶፪ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፶
"ከዚችም ዓለም ገዢዎች አንዱ እንኳ ይህን ጥበብ አላወቀም ዐውቀውስ ቢሆኑ የክብርን ጌታ ባልሰቀሉትም ነበር" (፩ኛ ቆሮ. ፪፣፰)።

ኢየሱስ ክርስቶስን ሰው ብቻ (ዕሩቅ ብእሲ) አድርገው የሚናገሩ ሰዎች በዚህ ኃይለ ቃል ይረታሉ። ከዚህ የክብር ጌታ ብሎ ገልጾታልና። የክብር ጌታ ደግሞ እግዚአብሔር ነው። ስለዚህ ይህ ኃይለ ቃል የኢየሱስ ክርስቶስን እግዚአብሔርነት በግልጽ ይናገራል። ክርስቶስን ሁለት አካል ሁለት ባሕርይ የሚሉ ሰዎች ደግሞ ወልደ አብ አልታመመም ወልደ ማርያም ታመመ እያሉ አንዱን ለሁለት እየከፈሉ በራሳቸው ስሕተት ራሳቸውን ይጎዳሉ። ይህ ኃይለ ቃል የተሰቀለው በሥጋው የክብር ጌታ (ወልደ እግዚአብሔር) መሆኑን በግልጽ ይናገርባቸዋልና ክሕደታቸው ከንቱ መሆኑን ይወቁ።

© በትረማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፶፩ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፵፱
"እምነታችሁም በእግዚአብሔር ኀይል እንጂ በሰው ጥበብ እንዳይኾን" (፩ኛ ቆሮ. ፪፣፬)።

ሃይማኖታችን በሰው ፍልስፍና የተመሠረተ አይደለም። ሰው ተጠብቦ ያገኘው ነገር አይደለም። ከዚያ ይልቅ እግዚአብሔር በተለያየ መንገድ የገለጠልን እውነት ነው። ይህ እግዚአብሔር የገለጠልን እውነት ደግሞ አንድ ነው። ታዲያ በዓለም ላይ ይህ ሁሉ ቤተ እምነት ከምን ተገኘ ከተባለ በሁለት መንገድ ተገኝቷል። አንደኛ ሰው መሰለኙን እውነት አድርጎ በማመኑ የተመሠረቱ ቤተ እምነቶች አሉ። ሁለተኛ ሰይጣን በተለያዩ ምትሐታዊ ሥራዎቹ አታሏቸው እርሱን የሚያመልኩ ሰዎች አሉ። ሰይጣን በሰው ልቡና ላይ ጥርጥርን በማምጣት ከትክክለኛዋና ከአንዷ ሃይማኖት ሰዎችን እየለየ ሌላ የተሳሳተ አመለካከትንና እምነትን እንዲከተሉ ያደርጋል። የእኛ ግን ሃይማኖታችን በሰው ጥበብ ያይደለ በእግዚአብሔር ኃይል የተገለጠች በመሆኗ ሁልጊዜም ደስ ብሎን እንኖራለን።

© በትረማርያም አበባው


የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፶ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፵፰
"እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን" (፩ኛ ቆሮ. ፩፣፳፫)።

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የትምህርት ዋና ማዕከሏ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። በቅዳሴዋ፣ በማኅሌቷ፣ በቅኔዋ፣ በዝማሬ መዋስእቷ፣ በትርጓሜዋ፣ በዜማዋ እና በጠቅላላው አገልግሎቷ የምትሰብከው ኢየሱስ ክርስቶስን ነው። ሐዋርያት በስሙ ስለእርሱ ሰበኩ። ነቢያትም ቀድሞ እርሱ እንደሚወለድ ትንቢት ተናገሩ። ከሐዋርያት በኋላ የተነሡ ሊቃውንት ስለእርሱ ስለኢየሱስ ክርስቶስ አስተማሩ። ኢየሱስ ክርስቶስ ከሥላሴ አንዱ መሆኑን፣ ከቅድስት ድንግል ማርያም መወለዱን፣ ዓለምን ለማዳን በመስቀል መሰቀሉን፣ በሦስተኛው ቀን ከሙታን መካከል ተለይቶ መነሣቱን፣ በአርባኛው ቀን ወደሰማይ ማረጉን እናስተምራለን።

© በትረማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፵፱ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፵፯
"ወደልጁ ወደጌታችን ወደኢየሱስ ክርስቶስ ኅብረት የጠራችኹ እግዚአብሔር የታመነ ነው" (፩ኛ ቆሮ. ፩፣፱)።

ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ደጋግመን ተማምረናል። የእግዚአብሔር ልጅ ስንልም የአብ ልጅ ማለታችን ነው እንጂ የመንፈስ ቅዱስ ልጅ ማለታችን አይደለም። እግዚአብሔር በሚለው ቃል ሦስቱም አካላት የሚጠሩበት የአንድነት ስም ቢሆንም ከዚህ ላይ የተገለጸው ግን አብ እንደሆነ ልብ ማድረግ ይገባል። አብ ወልድን ስለወለደ የወልድ አባት ይባላል። መንፈስ ቅዱስን ስላሠረጸ ደግሞ አሥራጼ መንፈስ ቅዱስ ይባላል። ከዚህ ላይ ኢየሱስ ክርስቶስን "ጌታችን" ብሎ ገልጾታል። ጌታ መባል የሦስቱም የአንድነት ግብር ስለሆነ አብም ጌታ ይባላል። መንፈስ ቅዱስም ጌታ ይባላል።

© በትረማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፵፰ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፵፮
"ብቻውን ጥበብ ላለው ለእግዚአብሔር በኢየሱስ ክርስቶስ እስከ ዘለዓለም ድረስ ክብር ይሁን አሜን" (ሮሜ ፲፮፣፳፯)።

እግዚአብሔር ብቻውን ጥበብ ያለው ነው። ፍጡራን ጥበብ ቢኖራቸው ፈጣሪ በጸጋ የሰጣቸው ነው። አምላክ ግን ብቻውን ጥበበኛ ነው። "ብቻውን" የሚለው አገላለጽ ከፍጡራን ሲለየው ነው እንጂ አብን ከወልድና ከመንፈስ ቅዱስ፣ ወልድን ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ፣ መንፈስቅዱስን ከአብና ከወልድ ሲለያቸው አይደለም። አብ ብቻውን ጥበብ ያለው ይባላል። ይህን ጊዜ "ብቻውን" የሚለው ቃል ከወልድና ከመንፈስ ቅዱስ ተለይቶ ለማለት ሳይሆን ከፍጡራን ተለይቶ ለማለት ነው። ሦስቱ አካላት በጥበብ፣ በዕውቀት፣ በፈቃድ በጠቅላላው በአምላካዊ ሥራ አንድ ናቸውና።

© በትረማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፵፯ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፵፭
"የክርስቶስ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል" (ሮሜ ፲፮፣፲፮)።

ቤተ ክርስቲያን የሚለው ቃል ሦስት ትርጉም አለው። አንደኛው አምልኮ የምንፈጽምበት፣ የምንጠመቅበት፣ የምንቆርብበት ቤት ሕንፃው ቤተ ክርስቲያን ይባላል። ሁለተኛው እያንዳንዱ ምእመን ቤተ ክርስቲያን ይባላል። ይኽውም ቤተ ክርስቶስ (የክርስቶስ ወገን) ማለት ነው። ሰው በክርስቶስ ሲጠመቅ የክርስቶስ ወገን ይሆናል። ሦስተኛው የምእመናን አንድነት ቤተ ክርስቲያን ይባላል። የክርስቶስ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል የሚለው አገላለጽ በክርስቶስ አምነው፣ በክርስቶስ ስም ተጠምቀው የሚኖሩ ምእመናን ሁሉ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል ማለቱ ነው እንጂ ሕንፃው ሰላምታ ያቀርብላችኋል ማለቱ አይደለም።

© በትረማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፵፮ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፵፬
"በሕይወት ሆነን ብንኖር ለጌታ እንኖራለንና፥ ብንሞትም ለጌታ እንሞታለን። እንግዲህ በሕይወት ሆነን ብንኖር ወይም ብንሞት የጌታ ነን" (ሮሜ ፲፬፣፰)።

ጻድቃን በዚህች ምድር ሲኖሩም ለእግዚአብሔር ኖሩ። ለእግዚአብሔር መኖር ማለትም ሕግጋቱን በመጠበቅ ኖሩ ማለት ነው። ሲሞቱም ለእግዚአብሔር ሞቱ። ለእግዚአብሔር መሞት ማለትም ሕጉን ትእዛዙን እየፈጸሙና ለዓለም ሁሉ እየተናገሩ ሰማዕት ሆኑ ማለት ነው። የቅዱሳን የኑሮ መመሪያቸው ሕገ እግዚአብሔር ነው። ለማንኛውም ሰው ባለቤት አለው። ሰው የራሱ አይደለም። ከአባት ዘር ከእናት ደም ከፍሎ ወደዚህ ምድር እንዲመጣ ያደረገው እግዚአብሔር ነው። ሁላችንም የፈጣሪ ገንዘቦች በመሆናችን ቅዱስ ጳውሎስ "የጌታ ነን" ብሎ ተናገረ።

© በትረማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፵፭ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፵፫
"ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን ልበሱት" (ሮሜ ፲፫፣፲፬)።

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ልበሱት ማለት በእርሱ አምናችሁ፣ ተጠምቃችሁ፣ ሥጋውን ደሙን ተቀበሉ ማለት ነው። በሌላ አገላለጽ ልበሱት ማለት በክርስቶስ ክርስቲያን ተባሉ ማለት ነው። እንዲሁም መልካም ሥራ ሠርታችሁ ክርስቶስ የጸጋ ተዋሕዶን ይዋሐዳችሁ ማለት ነው። ቅዱሳን ጻድቃን ክርስቶስን ስለለበሱት እውነትን በመመስከር ጸንተው ኖሩ፣ ታላላቅ ተአምራትን በእርሱ ስም አደረጉ። ቅዱስ አግናጤዎስ ለባሴ እግዚአብሔር ይባል ነበር። ይኽውም እግዚአብሔር በጸጋ የተዋሐደው የእግዚአብሔርን ሕግ በመዓልትም በሌሊትም የሚፈጽም ማለት ነው። ስለዚህ ክርስቶስን ልበሱት ማለትም በእርሱ አምናችሁ ተጠምቃችሁ ሕጉን ትእዛዙን ጠብቁ ማለት ነው።

© በትረማርያም አበባው


የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፵፬ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፵፪
"ሁሉ ከርሱና በርሱ ለርሱም ነውና ለርሱ ለዘለዓለም ክብር ይሁን አሜን" (ሮሜ ፲፩፣፴፮)።

ራሱን በራሱ ያመጣ ፍጥረት የለም። ማንም ቢሆን ራሱን ካልካደ በቀር ራሴን በራሴ አመጣሁ አይልም። ፍጥረታትን ሁሉ በቸርነቱ ካለመኖር አምጥቶ የፈጠረ ልዑል እግዚአብሔር ነው። ሲፈጥርም በፈቃዱ ፈጥሯቸዋል እንጂ እነርሱን እንዲፈጥር ያስገደደው ሌላ አካል የለም። ከፍጥረታት በፊት ከእግዚአብሔር ውጭ የሆነ ሌላ አካል አልነበረምና። "ሁሉ ከእርሱ ነው" ማለት ፍጥረታት ሁሉ ከእርሱ የተገኙ መሆናቸውን ይገልጻል። "ሁሉ በእርሱ ነው" ማለትም ፍጥረታት ሁሉ የተፈጠሩት በእርሱ መሆኑን ያመለክታል። "ሁሉ ለእርሱ ነው" ማለትም የፍጥረታት ሁሉ ባለቤት እርሱ እግዚአብሔር መሆኑን ያመለክታል። ለእግዚአብሔር መኖር ግን ሌላ ምክንያት የለውም። "እስመ አልቦ ውስተ ህላዌሁ አመክንዮ" እንዲል።

© በትረማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፵፫ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፵፩
"የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናልና" (ሮሜ ፲፣፲፫)።

የጌታን ስም ሰይጣናትም ይጠሩታል። ጠንቋዮችም ይጠሩታል። ሌቦች አመንዝራዎችም ይጠሩታል። በጠቅላላው ኢአማንያንም ይጠሩታል። ምግባረ ብልሹዎችም ይጠሩታል። ታዲያ የጠሩት ሁሉ ይድናሉ ያለው እነዚህን ሁሉ ይድናሉ ማለቱ ነውን? አይደለም። የጌታን ስም የሚጠራ ይድናል የተባለ በኢየሱስ ክርስቶስ አምኖና ተጠምቆ፣ ምግባር ትሩፋት ሠርቶ፣ ሥጋውን ደሙን ተቀብሎ የሚኖር ሰውን ያመለክታል። መልካም ሥራን እየሠሩ የጌታን ስም መጥራት ያድናል። ንሥሓ ገብተው ሥጋውን ደሙን ተቀብለው የጌታን ስም መጥራት ያድናል። እነዚህንና የመሳሰሉ መልካም ሥራዎችን ሳይሠሩ ስሙን መጥራት ብቻውን ግን አያድንም።

© በትረማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፵፪ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፵
"ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃልና፥ በአፉም መስክሮ ይድናልና" (ሮሜ ፲፣፲)።

አንድ ሰው ለመዳን ቢያንስ አራት ነገሮች ያስፈልጉታል። እነዚህም መጀመሪያ ለዚህች ዓለም ሠራዒ፣ አስተዳዳሪ፣ መጋቢ እንዳላት ማመን። የፈጠራት እግዚአብሔር መሆኑን፣ ይህ እግዚአብሔር ደግሞ በአካል ሦስት በባሕርይ አንድ መሆኑን ማመን ይገባል። ከሦስቱ አካላት አንዱ መዋረዳችንን አይቶ ከድንግል ማርያም ተወልዶ በመስቀል ተሰቅሎ እንዳዳነን ማመን ነው። ሁለተኛው አምነን መጠመቅ ነው። ሦስተኛው መልካም ሥራዎችን መሥራት ነው። አራተኛው ሥጋውን ደሙን መቀበል ነው። ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃል ማለቱ እነዚህን ነገሮች ሁሉ አድርጎ ሲያምን ነው። በአፉም መስክሮ ይድናል ያለው እውነትን ይዞ ከላይ ያሉትን ነገሮች ሠርቶ ሲመሰክር ነው። እንጂ እነዚህን ሳያደርግ በማመን ብቻ ይጸድቃል ማለት አይደለም።

© በትረማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፵፩ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፴፱
"ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍኽ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብኽ ብታምን ትድናለኽና" (ሮሜ ፲፣፱)።

ጌትነት የባሕርይ ጌትነትና የጸጋ ጌትነት ተብሎ በሁለት ይከፈላል። ጌትነት ምሥጢሩ ባለቤትነትን፣ ገዢነትን ያመለክታል። ለዓለም ጌታ አላት ማለት ባለቤት አላት ማለት ነው። ኢየሱስ ጌታ ነው ማለት የፍጥረታት ሁሉ ባለቤት እርሱ ነው ማለታችን ነው። ገዢነትን ሲያመለክት ደግሞ ኢየሱስ የፍጥረታት ሁሉ ገዢ ነው ማለታችን ነው። ፍጡራን ግን ጌታ ቢባሉ ከፈጣሪ ባገኙት ጸጋ ነው። ለሀብታቸው ባለቤት ቢሆኑ ሀብታቸውም ባለቤትነታቸውም ከፈጣሪ የተሰጠ ነው። ኢየሱስ ክርስቶስን ጌታ ነው ስንለው ግን ለጌትነቱ፣ ለባለቤትነቱና ለገዢነቱ ሌላ ምክንያት የሌለው በባሕርይው ጌታ የሆነ ነው ማለታችን ነው።

© በትረማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፵ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፴፰
"ከእነርሱም (ከአባቶችም) ክርስቶስ በሥጋ መጣ፥ እርሱም ከሁሉ በላይ ኾኖ ለዘለዓለም የተባረከ አምላክ ነው አሜን" (ሮሜ ፱፣፭)።

ቅዱስ ጳውሎስ የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት በግልጽ ከተናገረበት አንቀጽ አንዱ ይህ ነው። ቅድመ ዓለም የነበረ ዓለምን የፈጠረ ወልደ እግዚአብሔር አዳምን ለማዳን ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደ። ከአባቶች ተወለደ ብሎ የተናገረው አያቶቹን ለመጥቀስ ነው። ይኽውም ከኢያቄም ጀምሮ እነ ዳዊትን እነአብርሃምን እና ሌሎችንም ታላላቅ ቅዱሳን ለመጥቀስ ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ በባሕርይው አምላክ ነው። ቅዱሳን አምላክ ቢባሉ የጸጋ አምላክ ሆነው ነው። እርሱ ግን አምላክነቱ የባሕርይ አምላክ ነው። ለዘለዓለም የተባረከ አምላክ ተብሎ የተገለጸውም ለዚህ ነው።

© በትረማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፴፱ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፴፯
"የሞተው፥ ይልቁንም ከሙታን የተነሣው፥ በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው፥ ደግሞ ስለ እኛ የሚፈርደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው" (ሮሜ ፰፣፴፬)።

ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፴፮ ላይ እንደተመለከትነው መንፈስ ቅዱስም ይማልድልናል (ይከራከርልናል) እንደተባለና አብም ይከራከርልናል (ይትዋቀስ በእንቲኣነ) እንደተባለ አይተናል። በዚህኛው ክፍል ደግሞ ኢየሱስ ክርስቶስ የሚፈርደው ተብሏል። ይህም በግእዙ "ወይትዋቀስ በእንቲኣነ" ይላል። ይኽውም ይከራከርልናል (ይማልድልናል) ተብሎ ሊተረጎም ይችላል። ሁሉንም ቢል ትርጉሙ ተመሳሳይ ነው። ዋጋችንን ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ሆኖ ይሰጠናል ማለት ነው። በሥጋው በደሙ አማካኝነት እስከ ዕለተ ምጽአት ድረስ ጸጋውን እያደለ ሰይጣንን እንድንቃወም ይረዳናልና ይማልድልናል አለ እንጂ ከትንሣኤ በኋላ ኢየሱስ ክርስቶስ ሁልጊዜ እያማለደ ይኖራል ማለት አይደለም። ምድር ላይ በሠራልን የማዳን ሥራ አምነን ተጠምቀን ሥጋውን ደሙን ተቀብለን ብንኖር መንግሥተ ሰማያትን ሰጥቶ የሚፈርድልን እርሱ ነው።

© በትረማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፴፰ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፴፮
"እንዲሁም ደግሞ መንፈስ ድካማችንን ያግዛል እንዴት እንድንጸልይ እንደሚገ፟ባ፟ን አናውቅምና፥ ነገር ግን፥ መንፈስ ራሱ በማይነገር መቃተት ይማልድልናል" (ሮሜ ፰፣፳፮)።

መንፈስ ቅዱስን ይማልድልናል እያለ ነው። ዋጋ መስጠትን መማለድ ብሎ የሚገልጽበት ወቅት አለ። ይኽውም ውጤቱን በመቅድሙ መጥራት ነው። መንፈስ ቅዱስ የተለያዩ መከራዎችን ስንቀበል ዋጋችንን ይሰጠናል። ከአብ ከወልድ ጋር አንድ ሆኖ ለምዕመናን ዋጋቸውን ይሰጣቸዋል። እግዚአብሔር ምእመናን እንዳይወድቁ ይማልድላቸዋል ማለት ጸጋውን ያድላቸዋል። ከእነርሱ ጋር በረድኤት ሆኖ የሚድኑበትን መንገድ ይገልጽላቸዋል ማለት ነው። ይማልድልናል የሚለው ቃል በግእዝ "ይትዋቀስ-ይከራከርልናል" ተብሏል። ይህ ከሆነ ደግሞ አብም እንደሚከራከርልን (እንደሚማልድልን) ተጽፏል። "ስለእርሳቸው ይከራከርላቸዋልና በጠላታቸምም እጅ አይጥላቸውምና ከሚጠሏቸው ከጠላቶቻቸው እጅ ያድናቸዋል" እንዲል (፩ኛ መቃ. ፳፣፫)። ትርጉሙ ዋጋን ይሰጠናል ማለት ነው።

© በትረማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፴፯ ይቀጥላል

20 last posts shown.