በትረማርያም አበባው Betremariam Abebaw


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Religion


አቀድም አእኵቶቶ ለእግዚአብሔር

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Religion
Statistics
Posts filter


💙 ሁለተኛ ቆሮንቶስ ክፍል ፪ 💙

💙ምዕራፍ ፮፦
-ራሳችንን አቅንተን የእግዚአብሔር አገልጋዮች እንሁን መባሉ
-ተጠራጣሪዎች አትሁኑ መባሉ

💙ምዕራፍ ፯፦
-ራሳችንን ማንጻት፣ ሥጋችንን አለማርከስ፣ ነፍሳችንን አለማሳደፍ እንደሚገባ
-እግዚአብሔርን በመፍራት የምንቀደስበትን መሥራት እንደሚገባን
-ስለእግዚአብሔር ተብሎ የሚደረግ ኀዘን የዘለዓለም ሕይወትን የሚያሰጥ ንስሓ እንደሆነ

💙ምዕራፍ ፰፦
-በእርሱ ድህነት እኛ ባለጸጎች እንሆን ዘንድ ክርስቶስ ስለእኛ ራሱን ድሃ እንዳደረገ

💙ምዕራፍ ፱፦
-እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን እንደሚወድ

💙ምዕራፍ ፲፦
-የሚመካ በእግዚአብሔር ይመካ መባሉ
-እግዚአብሔር ያከበረው እንደሚከብር መነገሩ

💙የዕለቱ ጥያቄዎች💙
፩. ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ሰዎች ከነገራቸው መልእክት ያልሆነው የቱ ነው?
ሀ. ጽድቅን ከኃጢአት መቀላቀል ይገባል
ለ. ተጠራጣሪዎች አትሁኑ
ሐ. ወደማያምኑ ሰዎች አንድነት አትሂዱ
መ. ለ እና ሐ
፪. ከሚከተሉት ውስጥ የዘለዓለም ሕይወትን የሚያሰጥ ኃዘን የተባለው የትኛው ነው?
ሀ. ዓለማዊ ኀዘን
ለ. ሥጋዊ ንብረት ስለጠፋብን የምናዝነው ኀዘን
ሐ. ስለእግዚአብሔር ብለን የምናዝነው የንስሓ ኀዘን
መ. ሁሉም

https://youtu.be/tq3hm_dnEhs?si=U3odE9sRXw_BdU8G




❤ ሁለተኛ ቆሮንቶስ ክፍል ፩ ❤

❤ምዕራፍ ፩፦
-የክርስቶስ መከራ በእኛ ላይ ሲበዛ መጽናናታችንም በክርስቶስ እንደሚበዛ መነገሩ
-እግዚአብሔር የታመነ እንደሆነ

❤ምዕራፍ ፪፦
-ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ሰዎች ሥርዓት አላጸናባችሁም እንዳላቸው

❤ምዕራፍ ፫፦
-ኃይላችን ከእግዚአብሔር ስለሆነ ከእኛ ከራሳችን እንደሆነ አድርገን ምንም ልናስብ እንደማይገባን
-የእግዚአብሔር መንፈስ ባለበት ነጻነት አለ መባሉ

❤ምዕራፍ ፬፦
-ኢየሱስ ክርስቶስን ጌታ ነው ብለን እንደምንሰብክ
-ጳውሎስ መከራን እንቀበላለን ግን አንጨነቅም፣ እንናቃለን ግን ተስፋ አንቆርጥም፣ እንወድቃለን ግን አንጠፋም ብሎ እንደተናገረ
-ዘወትር የክርስቶስን ሞት በሥጋ መሸከም እንደሚገባ

❤ምዕራፍ ፭፦
-በሰማይ የሰው እጅ ያልሠራው ዘለዓለማዊ ቤት እንዳለ መነገሩ
-ሁልጊዜ እመኑ፣ ጨክኑም እንደተባለ
-ሁላችንም በክርስቶስ የፍርድ ዙፋን ፊት እንደምንቆም
-በክርስቶስ የሆነው ሁሉ አዲስ ፍጥረት ነው እንደተባለ

❤የዕለቱ ጥያቄ❤
፩. ከሚከተሉት ውስጥ ትክክል የሆነው የቱ ነው?
ሀ. የእግዚአብሔር መንፈስ ባለበት ነጻነት አለ
ለ. እግዚአብሔር የታመነ ነው
ሐ. ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታ ነው
መ. ሁሉም

https://youtu.be/cYotsH_UFgU?si=w7m3iZUF068cSwwt


✔️መልስ፦ መጀመሪያ ላይ የሚበሰብሰው የማይበሰብሰውን አይወርስም የሚለው የኃጥእ ሰው ሰውነት በባሕርይው መበስበስ የሌለበት መንፈስ ቅዱስን አይወርስም ማለት ነው። ይኸውም መንግሥተ ሰማያት አይገባም ማለት ነው። በሁለተኛ ላይ የሚበሰብሰው የማይበሰብሰውን ይለብሳል የሚለው የጻድቃን ሰውነት መንፈስ ቅዱስን በጸጋ ወርሰው ይኖራሉ ለማለት ነው። በአጭሩ ኃጥኣን የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም ጻድቃን ግን የእግዚአብሔርን መንግሥት ይወርሳሉ ማለት ነው።

▶️፴፮. “ከዚያም በኋላ ከአምስት መቶ ለሚበዙ ወንድሞች በአንድ ጊዜ ታየ። ከእነርሱም የሚበዙት እስከ አሁን አሉ አንዳንዶች ግን አንቀላፍተዋል" ይላል (1ኛ ቆሮ.15፥6)። ከ500 የሚበዙ ሰዎች በምን ሁኔታ ተሰብስበው ነው? እስከ አሁን አሉ ያለው መቼ ነው?

✔️መልስ፦ እነዚህ 500 የተባሉ ሰዎች በጌታ ስቅለት ጊዜ ከእግረ መስቀሉ ከሙታን መካከል የተነሡ ሰዎች ናቸው። እስከ አሁን አሉ ያለው ከስቅለት ጀምረው ጳውሎስ ይህንን እስከሚጽፍበት ጊዜ ድረስ ነበሩ ለማለት ነው።

▶️፴፯. “ሁሉ ከተገዛለት በኋላ ግን እግዚአብሔር ሁሉ በሁሉ ይሆን ዘንድ በዚያን ጊዜ ልጁ ራሱ ደግሞ ሁሉን ላስገዛለት ይገዛል" ይላል (1ኛ ቆሮ.15፥28)። እንዴት ይተረጎማል? ኢየሱስ ይገዛል ተብሎ ይነገርለታል?

✔️መልስ፦ ሁሉ ተገዛለት የተባለ ሞት ነው። እግዚአብሔር ሰው ሁሉ ይሞት ዘንድ ሞትን በሰዎች ዘንድ አሠልጥኖታል። ልጁ ራሱ ደግሞ ላስገዛለት ይገዛል ማለት ወልድ በተዋሐደው ሥጋ ይሞታል ማለት ነው። እንዲሁም አብ ሥጋን በተዋሕዶ ሁሉ የሚገዛለት የባሕርይ አምላክ አደረገው። በዚያን ጊዜ ማለት በዕለተ ስቅለት ደግሞ ልጁ ራሱ ሁሉን ላስገዛለት ይገዛል ማለት ለሰው ቤዛ ሆኖ አባት ሆይ ይቅር በላቸው ይላል ማለት ነው። ይቅር በላቸው ብሎ የለመነ እርሱ ቢሆንም ከአባቱና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ይቅር የሚልም ግን እርሱ መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል።

© በትረ ማርያም አበባው

✝️የዩቲዩብ ቻናሌ:- We belong to Christ ንሕነ ዘክርስቶስ https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

🌻የፌስቡክ ገጼ Betremariam Abebaw https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።


✔️መልስ፦ የሞት መውጊያ ኃጢአት ናት ማለት ሞት እንዲመጣ ምክንያቷ ኃጢአት ናት ማለት ነው። የኃጢአትም ኃይሏ ኦሪት ናት ማለት ኃጢአትን አጉልታ ለይታ ለይታ የምታሳውቅ ኦሪት ናት ማለት ነው። እንዲሁም ኦሪትን መሻር ኃጢአትን ስለሚያበዛ የኃጢአት ኃይሏ ኦሪት ናት አለ።

▶️፳፪. “ነገር ግን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ድል መንሣትን ለሚሰጠን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን" ይላል (1ኛ ቆሮ.15፥57)። ራሱ ክርስቶስ አይሰጥም ወይ? ለምን በኩል አለ?

✔️መልስ፦ ራሱ ክርስቶስም ይሰጣል። ድል መንሣትን መስጠት የሦስቱም ማለትም የአብ፣ የወልድ፣ የመንፈስ ቅዱስ የአንድነት ሥራ ስለሆነ አንዱ ብቻ ቢጠራም ሁለቱንም ይመለከታል።

▶️፳፫. 1ኛ ቆሮ.11፥10 ላይ "ሴት ከመላእክት የተነሣ በራሷ ሥልጣን ሊኖራት ይገባል" ይላል። ከመላእክት የተነሣ ማለት ምን ማለትነው?

✔️መልስ፦ ከመላእክት የተነሣ ማለት ጠባቂ መላእክቶቿ እንዳያዝኑባት ጌታ ተከናነቡ እንዳለ መከናነብ አለባት ማለት ነው። መላእክት የሚለው አለቆች ተብሎም ይተረጎማል። አለቆች የተባሉ ቀሳውስት ካህናት ጸጕሯን አይተው በፍትወት እንዳይወድቁ ራሷን ትከናነብ ማለት ነው።

▶️፳፬. 1ኛ ቆሮ.13፥2 ላይ "እምነት ሁሉ ቢኖረኝ ፍቅር ከለለኝ ከንቱ ነኝ" ይላል፡፡ እምነት ጽድቅ ሆኖ ለአብርሃም እንደተቆጠረለት በሮሜ ፬ አይተናል። ከዚህ ጋር አጋጭም?

✔️መልስ፦ አይጋጭም። ከዚህ ላይ እምነት ኖሮን ፍቅር ከሌለን እንደማንጠቀም ለመግለጽ ፍቅር ከሌለኝ ከንቱ ነኝ ብሏል። አብርሃም ደግሞ እምነትን ከፍቅር ጋር አስተባብሮ ይዞ ስለነበረ በመሠረቱ በእምነት ጸደቀ ተብሏል።

▶️፳፭. “ሞት ሆይ መውጊያህ የት አለ? ሲኦል ሆይ ድል መንሣትህ የት አለ" ይላል (1ኛ ቆሮ.15፥55)። ሞት የሆነ አካል ያለው ነገር ነው እንዴ?

✔️መልስ፦ አይደለም። በመጽሐፍ ቅዱስ አካል የሌላቸውን ነገሮች አካል እንዳላቸው አድርጎ መግለጽ የተለመደ ነው። ይኸውም ሐሳቡን በምሳሌ አጉልቶ ለማሳየት (Figurative ለማድረግ) ነው። ፍሬ ነገሩ ሞትም ድል መንሣት አልቻለም። መቃብርም ይዞ ማስቀረት አልቻለም ማለት ነው።

▶️፳፮. ፩ኛ ቆሮ.፲፩፥፰ ላይ "ወንድ ግን ከሴት የተገኘ አይደለም" ይላል። ፩ኛ ቆሮ.፲፩፥፲፪ ደግሞ "ሴት ከወንድ እንደተገኘች እንዲሁ ወንድ ከሴት ተገኘ" ይላል። ይህ እንዴት ይታረቃል?

✔️መልስ፦ የመጀመሪያው ወንድ ከሴት የተገኘ አይደለም የሚለው በጥንተ ተፈጥሮ ነው። በጥንተ ተፈጥሮ አዳም ቀድሞ ተፈጥሮ ሔዋን ከአዳም ጎን ተገኝታለችና ነው። ቁጥር 12 ላይ ያለው ደግሞ ወንድ የተባለ ክርስቶስ ሴት ከተባለች ድንግል ማርያም ተወለደ ማለት ነው።

▶️፳፯. “ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን የማይወድ ቢኖር የተረገመ ይሁን። ጌታችን ሆይ ና” ይላል (1ኛ ቆሮ.16፥22)። ጌታችን ሆይ ና ማለቱ ዕለተ ምጽአት ይፍጠን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ አዎ። ክርስቶስን የማይወድ ሰው የተረገመ ነው። ከዚህም ጌታችን ሆይ ና የሚለው ለማይመለሱ ሰዎች አምላካዊ ፍርድህ ይፍጠንባቸው ለማለት ነው።

▶️፳፰. “እግዚአብሔርም በቤተ ክርስቲያን አንዳንዶቹን አስቀድሞ ሐዋርያትን ሁለተኛም ነቢያትን ሦስተኛም አስተማሪዎችን" ይላል (1ኛ ቆሮ.12፥28)። ሐዋርያት፣ ነቢያትን እና አስተማሪዎች የተባሉ እነማን ናቸው?

✔️መልስ፦ ሐዋርያት የተባሉ 12ቱ ናቸው። ነቢያት የሚላቸው 72ቱ አርድእት ናቸው። አስተማሪዎች የሚባሉት ከሐዋርያትና ከአርድእት በኋላ የተነሡ እስከ ዕለተ ምጽአት የሚነሡ ጳጳሳት ሊቃውንት ናቸው።

▶️፳፱. “ከዕውቀት ከፍለን እናውቃለንና ከትንቢትም ከፍለን እንናገራለንና” ይላል (1ኛ ቆሮ.13፥9)። የዕውቀት ተከፍሎ እንዴት ነው? ይህ የዕውቀት ተከፍሎ ዶግማ በሆኑ ትምህርቶች አንጻር እንዴት ይታያል?

✔️መልስ፦ የሰው ዕውቀት ውሱን ነው። ተከፍሎ አለበት። ሁሉን የሚያውቅ እግዚአብሔር ብቻ ነው። በዶግማዊ ዕውቀቶችም ለመዳን የሚያስፈልገውን እርሱ ስለእርሱ የገለጸልንን ያህል ብቻ እናውቃለን። ከዚያ በላይ ያለውን ባለማወቅ ሆነን ዕውቀትን ሁሉ ለእርሱ ሰጥተን እግዚአብሔር ያውቃል እንላለን። ወነኀድግ ዘንተ መካነ ለእግዚአብሔር እንዲል። ለምሳሌ እግዚአብሔር እንዳለ እናውቃለን። እንዴት እንደሚኖር ግን አናውቅም። ከኅሊና በላይ፣ ከመመርመር በላይ ነውና።

▶️፴. 1ኛ ቆሮ.13 ስለ ፍቅር በስፋት ይናገራል። ለመሆኑ ይህ ፍቅር ምን ዓይነት ፍቅር ነው? እንዴትስ ይገለጻል?

✔️መልስ፦ ፍቅር የሚባለው እግዚአብሔርን መውደድና ቢልንጀራን መውደድ ተብሎ ይከፈላል። እግዚአብሔርን መውደድ አድርጉ ያለንን በማድረግ ይገለጣል። ባልንጀራን መውደድ ለእኛ ሊደረግልን የምንፈልገውን መልካም ነገር ለሌሎች በማድረግ ይገለጣል። እንዲሁም በእኛ ሊደረግብን የማንፈልገው ነገር በሌሎችም እንዳይደረግ በመመኘት ይገለጣል።

▶️፴፩. “ዛሬስ በመስተዋት በድንግዝግዝ እንደምናይ ነን በዚያን ጊዜ ግን ፊት ለፊት እናያለን (1ኛ ቆሮ.13፥12)። በዚያን ጊዜ የተባለው መቼ ነው? የሰው ልጅ ፍጹም የሚሆንበት ጊዜ አለ ወይ?

✔️መልስ፦ የሰው ልጅ ፍጹም ተብሎ ሲቀጸልለት አንጻራዊ ፍጹም ነው። ከዚህም በዚያን ጊዜ የተባለው ከወጣኒነት ተለይቼ ፍጹም በሆንኩ ጊዜ ማለት ነው።

▶️፴፪. “ለኬፋም ታየ በኋላም ለአሥራ አንዱ” ይላል (1ኛ ቆሮ.15፥5)። ኬፋ ማን ነው? አሥራ አንዱ እነማን ናቸው?

✔️መልስ፦ ኬፋ የተባለ ጴጥሮስ ነው። አሥራ አንዱ ያላቸው ሌሎች ሐዋርያት ናቸው።

▶️፴፫. “ሴቶች በማኅበር ዝም ይበሉ። ሕግ ደግሞ እንደሚል እንዲገዙ እንጂ እንዲናገሩ አልተፈቀደላቸውምና" ይላል (1ኛ ቆሮ.14፥34)። እንዴት ይተረጎማል? ዘመን አመጣሽ ፌሚኒስት ነን የሚሉ ሰዎቾ ይህን ጥቅስ ሴቶችን የበታች ያደርጋል ይላሉና።

✔️መልስ፦ ሴቶች በማኅበር ማለት በጉባኤ ዝም ይበሉ ማለት ነው። እግዚአብሔር ያዘዘውን ማድረግ የበላይ ያደርጋል እንጂ የበታች አያደርግም። የእግዚአብሔርን ቃል የሚቃወም ሰው እምነት አልባ ሰው ነው። እግዚአብሔር ለሁሉ የሚሻለውን ነገር ተናግሯል። በተፈጥሮምኮ ሴትና ወንድ ይለያያል። ነገር ግን ለሁሉ የሚጠቅመውን አደረገ እንጂ አላበላለጠም። በቅድስና ከፍጥረታት ሁሉ በላይ የሆነች ድንግል ማርያም ናት። ሰውን የሚያበላልጠው ሥራው ነው።

▶️፴፬. “ለሴት በማኅበር መካከል መናገር ነውር ነውና። ምንም ሊማሩ ቢወዱ በቤታቸው ባሎቻቸውን ይጠይቁ" ይላል (1ኛ ቆሮ.14፥35)። ሴቶች በማኀበር ተቀምጠው መማር የተለከለ ነው እንዴ?

✔️መልስ፦ በማኅበር መካከል (በቤተ ክርስቲያን) አይናገሩ ተባለ እንጂ አይማሩ አልተባለም። ነገር ግን በትምህርቱ ያልገባቸውን መጠየቅ ከፈለጉ ባሎቻቸውን ይጠይቁ ማለት ነው።

▶️፴፭. "የሚበሰብሰውም የማይበሰብሰውን አይወርስም" ይላል (1ኛ ቆሮ.15፥50)። እንዴት ይተረጎማል? ቀጥሎ ዝቅ ብሎ “ይህ የሚበሰብሰው የማይበሰብሰውን ሊለብስ ይህም የሚሞተው የማይሞተውን ሊለብስ ይገባዋልና" ይላል። ይህ እንዴት ይታረቃል?


▶️፲. 1ኛ ቆሮ.11፥34 ላይ “ማንም የራበው ቢኖር ለፍርድ እንዳትሰበሰቡ በቤቱ ይብላ" ሲል ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ ከቁጥር 33 ጀምረን ስንመለከተው ለመብላት በተሰበሰባችሁ ጊዜ ይላል። ከሰዎች ጋር ለመብላት ለመሰብሰብ የፈለገ ሰው ቢኖርና ያ ሰው የራበው ቢሆን አስቀድሞ ከቤቱ በልቶ ይምጣ ማለት ነው። ይኸውም በወንድሞች መካከል ሳስቶ በደል እንዳይሆንበት ነው።

▶️፲፩. 1ኛ ቆሮ.11፥7 ላይ "ወንድ የእግዚአብሔር ምሳሌና ክብር ስለ ሆነ መከናነብ አይገባውም" ሲል መከናነብ ከእግዚአብሔር ምሳሌ እና ክብር ጋር ምን ያገናኘዋል?

✔️መልስ፦ ወንድ ልጅ በእግዚአብሔር አምሳል ስለተፈጠረ የእግዚአብሔር መልክ (Image of God) ነኝ ለማለት ተገልጦ ይሄዳል። የተከናነበ ሰው የምን ምሳሌ እንደሆነ አይታወቅምና። የሰው መልኩ የሚታየውም ካልተከናነበ ነውና። ታዲያ ሴትስ የእግዚአብሔር መልክ አይደለች ለምን አትከናነብም ቢሉ የተገኘችው ከጎን አጥንት ነው። አጥንት ደግሞ የተሸፈነ ነውና ትሸፈን ተብሏል።

▶️፲፪. “ራሱን ተከናንቦ የሚጸልይ ወይም ትንቢት የሚናገር ወንድ ሁሉ ራሱን ያዋርዳል” ይላል (1ኛ ቆሮ.11፥4)። ይህ መከናነብ ከመነኵሴዎች ቆብ እና ከጥምጥም ምን ይለየዋል? ደግሞም በጸሎት ጊዜ ምእመናን ባርኔጣ ወይም ቆብ እንዲያደርጉ አይፈቀድላቸውም እና ይህ በቤተክርስቲያናችን ሥርዓት እንዴት ይታያል?

✔️መልስ፦ መነኮሳት ቆብ እንዲያደርጉ ሥርዓት የሠራላቸው ራሱ እግዚአብሔር ነው። በመጽሐፈ መነኮሳት እንደተገለጸው መልአክ ለእንጦንስ አሳይቶታል። ቆብ ክርስቶስ በመስቀል በተሰቀለ ጊዜ ያደረጉለት የአክሊለ ሦክ ምሳሌ ነው። ጥምጥምም በዚህ መልኩ የሚተረጎም ነው። በነገረ ማርያም እንደተገለጸው ሐዋርያት የድንግል ማርያምን መጎናጸፊያ ተካፍለው በራሳቸው ያደርጉት ነበር። ጥምጥም የዚህ ምሳሌ ነው። ባርኔጣ ግን ሃይማኖታዊ መሠረት ያለው አይደለም። ስለሆነም ከአክሊል፣ ከጥምጥም፣ ከአስኬማ፣ ከቆብ ውጭ ሌላ ልብስ በራሳችን አድርገን መከናነብ አይገባንም ማለት ነው።

▶️፲፫. 1ኛ ቆሮ.14፥7 ስለ ቋንቋ፣ ትንቢት እና በትርጉም ስለማስተማር በሚናገርበት አንቀጽ መሰንቆ፣ ክራርና እምቢልታን ያነሣል። በክራር ማመስገን ይቻላልን?

✔️መልስ፦ የአማርኛው ትርጉም አሳስቶት እንጂ ክራር ሳይሆን በገና ነው የሚለው። እንግሊዘኛው flute (ዋሽንት) or harp (በገና) ይላል። እንጂ በገና (lyre) አይልም። ግእዙንም ብናየው መሰንቆሁኒ ወእንዚራሁኒ ይላል። እንዚራ ደግሞ በገና ነው። ማስረጃው "ወዳዊትሰ የአነዝር በእንዚራ ቅድመ ታቦተ እግዚአብሔር" የሚለው ነው (2ኛ ሳሙ.6፥14)። ዳዊት ሀብተ በገና እንጂ ሀብተ ክራር ነበረው አልተባለምና። በቀኖና ደረጃ በሲኖዶሰ ከተወሰነ በክራር መዘመር ይቻላል። እስካልተቀነነ ድረስ ግን በራሳችን ጉልበት በክራር ካልዘመርን ማለት ተገቢ አይደለም።

▶️፲፬. 1ኛ ቆሮ.11፥31 ላይ "እኛ በራሳችን ብንፈርድ ኖሮ ባልተፈረደብንም ነበር" ይላል። በራሳችን ብንፈርድ የሚለው እንዴት ይተረጎማል?

✔️መልስ፦ በበደልነው በደል ራሳችንን መውቀስና በራሳችን መፍረድ ይገባናል ማለት ነው። በራሳችን ኃጢአት ንስሓ ካልገባን በሰማይ እግዚአብሔር ይፈርድብናል ማለት ነው።

▶️፲፭. 1ኛ ቆሮ.12፥3 ላይ "በመንፈስ ቅዱስም ካልሆነ በቀር ኢየሱስ ጌታ ነው ሊል አንድስ እንኳ እንዳይችል አስተዋቃችኋለሁ" ይላል። በቃል በመናገር ነውን? ከሆነ የማያምኑም ይላሉና እንዴት ይታያል?

✔️መልስ፦ በቃል በመናገር ብቻ አይደለም። መንፈስ ቅዱስ አድሮበት ካልሆነ በቀር በክርስቶስ አምኖ፣ ክርስቶስን የባሕርይ አምላክ ነው ብሎ ኢየሱስ ጌታ ነው የሚል የለም ማለት ነው። በክርስቶስ አምነው፣ ተጠምቀው፣ ምግባር ትሩፋት ሠርተው ኢየሱስ ጌታ ነው የሚሉት በመንፈስ ቅዱስ ነው ማለት ነው። ሳያምኑ ኢየሱስ ጌታ ነው የሚሉ ካሉ ግን በመንፈስ ቅዱስ ነው አይባልም። ቅዱስ ጳውሎስ ይህንን የተናገረው ለአማኞች ብቻ እንደሆነ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደሚከተለው ገልጾታል። If “no one can say that Jesus is Lord except by the Holy Spirit”, What can we say about those who have called His name without having the Spirit? Here, it is befitting of us to understand that Paul was not speaking about the Catechumen who were not yet baptized, but about the believers and the nonbelievers. (St. John Chrysostom)

▶️፲፮. 1ኛ ቆሮ.13፥10 ላይ "ፍጹም የሆነ ሲመጣ ግን ያ ተከፍሎ የነበረው ይሻራል" ሲል እንዴት ይተረጎማል?

✔️መልስ፦ ፍጹም የሆነ ሲመጣ ተከፍሎ የነበረው ይሻራል። ፍጹም ዕውቀት ከጥርጣሬ ያድናልና። በአጭሩ ጥርጣሬ (ጥቂት ዕውቀት) በፍጹም ዕውቀት ይሻራል ለማለት ነው። ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ ይህንን እንደሚከተለው ገልጾታል። Although everyone of us perpetually seek more knowledge; Yet it remains “a knowledge in part” in all issues, compared to “the perfect knowledge”; until the time for the perfect to come, and that which is in part will be done away. (St. Basil the Great)

▶️፲፯. 1ኛ ቆሮ.14፥2 ላይ "በቋንቋ የሚናገር ለእግዚአብሔር እንጂ ለሰው የሚናገር አይደለም። የሚናገረውን የሚሰማው የለምና" ሲል እንዴት ይተረጎማል?

✔️መልስ፦ የሚሰሙት ሰዎች በማያውቁት ቋንቋ የሚናገር ሰው ለሰሚዎች የሚናገር ሳይሆን ለእግዚአብሔር ብቻ ይናገራል ማለት ነው። ለምሳሌ ግእዝ ቋንቋን መስማት ለማይችሉ ምእመናን ግእዝ ብንጠቅስ በዚያ ሰዓት ግእዙን የሚያውቀው ተናጋሪውና እግዚአብሔር ብቻ ናቸው ማለት ነው።

▶️፲፰. 1ኛ ቆሮ.14፥14 ላይ "በማላውቀው ቋንቋ የምጸልይ ከሆንሁ ቃሌ ብቻ ይጸልያል። ልቤ ግን ባዶ ነው" ይላል። ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ ሰው ትርጉሙን በማያውቀው ቃል የሚጸልይ ከሆነ አፉ ብቻ ይናገራል እንጂ ልቡ ትርጉሙን አያውቀውም ማለት ነው። እንዲሁሞ ሞሥጢሩን ሳያውቅ የሚጸልይ ሰው አነብናቢ ብቻ ይሆናል ማለት ነው።

▶️፲፱. 1ኛ ቆሮ.14፥31 ላይ "እያንዳንዳችሁ ትንቢት ልትናገሩ ትችላላችሁና" ይላል። ትንቢት መናገር ለክርስቲያን ሁሉ የተሰጠ ነውን?

✔️መልስ፦ ከዚህ ትንቢት ተብሎ የተገለጸው ትምህርት ነው። ሁሉም ያወቀውን መንፈሳዊ ዕውቀት ለሌላው ማሳወቅ ይችላል ለማለት ነው። ክርስቲያን ሁሉ ቢያንስ ጥቂት መንፈሳዊ ዕውቀት ይኖረዋልና ያችን ማሳወቅ ይችላል ማለት ነው።

▶️፳. 1ኛ ቆሮ.15፥52 ላይ "ሙታንም የማይፈርሱ ሆነው ይነሣሉ እኛም እንለወጣለን" ይላል። በትንሣኤ ዘጉባኤ ጊዜ እንለወጣለን ማለቱ ነው?

✔️መልስ፦ መለወጥ ያለው ይታመም የነበረው ሰውነት በእግዚአብሔር ቸርነት የማይታመም ይሆናል ለማለት ነው እንጂ ወደ ሌላ አካልነት ይለወጣል ማለት አይደለም። ያው የነበረው አካል የማይታመም ሆኖ ይኖራል ማለት ነው። ይዘነው የምንነሣው ይህንኑ ሥጋ ነው።

▶️፳፩. 1ኛ ቆሮ.15፥56 ላይ "የሞት መውጊያ ኃጢአት ናት። የኃጢአትም ኃይሏ ኦሪት ናት" ሲል እንዴት ይተረጎማል?


✝️ የጥያቄዎች መልስ ክፍል 261 ✝️

▶️፩. 1ኛ ቆሮ.11፥24 ላይ "ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ” ይላል። በወንጌልም ይሁን በመልእክታት ይህን ለመታሰቢያ አድርጉት ከማለት ውጭ ሌላ የተባለ ነገር ባይኖርም ቤተክርስቲያናችን ግን ይህ አማናዊው ነው። ለድህነት የሚያበቃ እንዲሁም ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መሥዋዕት የሆነን ክርስቶስን በየቀኑ እንደምትሠዋው ትሰብካለች። ይህ አዲስ እና እንግዳ ትምህርት አይሆንምን?

✔️መልስ፦ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ በግልጽ የተጻፈ ጉዳይ አዲስ ትምህርት የሚሆንበት መጽሐፍ ቅዱስ ለማያነብ ነው። በወንጌልም በመልእክታትም ለመታሰቢያዬ አድርጉት ከሚለው በተጨማሪ የተነገሩ ተያያዥ ጉዳዮች አሉና። ሥጋው አማናዊ ለመሆኑማ በወንጌል ራሱ ክርስቶስ ይህ ሥጋዬ ነው ይህ ደሜ ነው ብሎ በግልጽ ቋንቋ ነግሮናል (ማቴ.26፥26)። በዮሐንስ ወንጌልም ሥጋዬን የበላ የዘለዓለም ሕይወትን ያገኛል ብሏል (ዮሐ.6፥54-57)። ስለዚህ በየዕለቱ የምንፈትተው የምንሠዋው መሥዋዕት በዕለተ ዓርብ የተቆረሰውንና የፈሰሰውን ሥጋውን ደሙን ነው። በመልእክተ ጳውሎስ ለመታሰቢያዬ አድርጉት ማለቱ ስትሠዉ የክርስቶስን መሰቀሉን፣ መሞቱን፣ መነሣቱን እያሰባችሁ አቅርቡት ማለት ነው። ለዚያ ነው በቅዳሴ ንዜኑ ሞተከ ወትንሣኤከ ቅድስተ እያልን እያሰብን የምንቀበለው። ይህም 1ኛ ቆሮ.11፥26 ላይ ተገልጿል። "አምጣነ ትበልዕዎ ለዝንቱ ኅብስት ወትሰትይዎ ለዝንቱ ጽዋዕ ሞቶ ለእግዚእነ ትዜንዉ እስከ አመ ይመጽእ" እንዲል።

▶️፪. 1ኛ ቆሮ.11፥3 ላይ "የክርስቶስም ራሱ እግዚአብሔር ነው" ሲል እንዴት ይተረጎማል?

✔️መልስ፦ በዚህ ጊዜ ራስ የሚለው መገኛ ተብሎ ይተረጎማል። የሴት ራስ ወንድ ነው ማለት ሴት ከወንድ መገኘቷን ያመለክታል። የወንድ ራስ ክርስቶስ ነው ማለት ሰው የተገኘው ከወልደ እግዚአብሔር ክርስቶስ ፈጣሪነት የተነሣ ነው ማለት ነው። የክርስቶስ ራስ እግዚአብሔር ነው ማለት ወልድ ክርስቶስ ከአብ አካል ዘእምአካል ባሕርይ ዘእምባሕርይ የተገኘ ነው ማለት ነው። በባሕርይ ወንድ እና ሴት አንድ ሆነው ሳለ ሴት ከወንድ በመገኘቷ ወንድ ለሴት ራሷ ተብሏል። እንዲሁ አብና ወልድ አንድ ባሕርይ ያላቸው ቢሆንም ወልድ ከዘመን ሳያንስ ከአብ በመገኘቱ አብ የወልድ ራሱ ተብሏል።

▶️፫. 1ኛ ቆሮ.11፥14-16 ላይ "ወንድ ልጅ ጸጕር ቢያስረዝም ነውር ይሆንበታል" ይላል። አንዳንድ ገዳማውያን እና መነኵሴዎች ጸጕራቸውን ያስረዝማሉ (ጌታን እና ዮሐንስ መጥምቅን ምሳሌ በማድረግ)። ስለዚህ ወንድ ልጅ ጸጕር ቢያስረዝም ችግር የለውም ያሉኝን ሰዎች አግኝቻለሁና እርስዎ ስለዚህ ጉዳይ ምን ይላሉ?

✔️መልስ፦ ወንድ ልጅ ጸጕሩን ካሳደገ ነውር ይሆንበታል ማለት ለወንድ ጸጕርን ማስረዘም ኃጢአት ነው ማለት ነው። መነኮሳት፣ ገዳማውያን፣ ዮሐንስ መጥምቅ ማስረዘማቸው ግን ራሳቸውን ለእግዚአብሔር የለዩ በመሆናቸው ነው። ለእግዚአብሔር ራሱን የለየ (ናዝራዊ) ጸጕሩን እንዳይላጭ ሥርዓት አለና ነው። "ራሱን ለመለየት ስእለት ባደረገበት ወራት ሁሉ በራሱ ላይ ምላጭ አይደርስም። ለእግዚአብሔር የተለየበት ወራት እስኪፈጸም ድረስ የተቀደሰ ይሆናል። የራሱንም ጠጕር ያሳድጋል" እንዲል (ዘኍ.6፥5)። ክርስቶስም ጸጕሩን ማሳደጉ ለናዝራውያን አብነት ለመሆን ነው። ያልመነኮሰ፣ ገዳማዊ ያልሆነ ሰው ግን ጸጕሩን ማሳደግ አይገባውም።

▶️፬. "ሴትም ራሷን ባትሸፍን ጠጕሯን ደግሞ ትቆረጥ። ለሴት ግን ጠጕሯን መቆረጥ ወይም መላጨት የሚያሳፍር ከሆነ ራሷን ትሸፍን" ይላል (1ኛ ቆሮ.11፥6)። ራሷን እንድትሸፍን የታዘዘችው ለሁልጊዜ ነው ወይስ ለጸሎት ብቻ ነው?

✔️መልስ፦ በጸሎት ጊዜም በሌላው ጊዜም ነው። የተከለከለበት ምክንያት ጸጕርን ማሳየት አመንዝራነት ስለሆነ ነው። ፍትሐ ነገሥት ላይ አንቀጽ 11 ስለሕዝባውያን በሚናገርበት አንቀጽም ይህንኑ ገልጾታል።

▶️፭. ፩ኛ ቆሮ.፲፬፥፳፬-፳፭ ላይ "ዅሉ ትንቢት ቢናገሩ ግን የማያምን ወይም ያልተማረ ሰው ቢገባ በዅሉ ይወቀሳል። በዅሉም ይመረመራል። በልቡም የተሰወረ ይገለጣል። እንዲሁም እግዚአብሔር በእውነት በመካከላቸው ነው ብሎ እየተናገረ በፊቱ ወድቆ ለእግዚአብሔር ይሰግዳል" ይላል። ከፍ ብሎ ፳፪ ላይ ደግሞ "ትንቢት ግን ለሚያምኑ እንጂ ለማያምኑ አይደለም" ይላል። ይህ እንዴት ይታረቃል?

✔️መልስ፦ ትንቢት መናገር የሚለው ማስተማርን ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ትምህርትን ትንቢት፣ መምህርን ነቢይ ስለሚለው ነው። ተርጉሞ ማስተማር የሚገባ ለሚያምኑ ነው እንጂ ለማያምኑ አይደለም። የተቀደሰውን ለውሾች አትስጡ ስለሚል መልካሙን ትምህርት ለሚያምኑ እንጂ ለማያምኑ መንገር አይገባምና። ትምህርትን ያልተማረ ሰው ቢናገረው ተሳስቶ እንደሚነቀፍ ለመግለጽ ዅሉ ትንቢት ቢናገሩ ግን የማያምን ወይም ያልተማረ ሰው ቢገባ በዅሉ ይወቀሳል ተብሏል። አዋቂዎች ቢያስተምሩ ግን ያላመኑትን አሳምነው ለእግዚአብሔር እንዲሰግዱ ያደርጓቸዋል ማለት ነው።

▶️፮. ፩ኛ ቆሮ.፲፬፥፳፪ ላይ "እንግዲያስ በልሳኖች መናገር ለማያምኑ ምልክት ነው እንጂ ለሚያምኑ አይደለም። ትንቢት ግን ለሚያምኑ እንጂ ለማያምኑ አይደለም" ይላል። ከዚህ ልሳን ወይም ቋንቋ የተባለ ምንድን ነው? በልሳን መናገር እንዴት ያለ ነው?

✔️መልስ፦ በልሳን መናገር ማለት ሐዋርያት በዕለተ ጰራቅሊጦስ በብዙ ቋንቋ እንደተናገሩት ሁሉ በብዙ ቋንቋ መናገር ነው። በብዙ ቋንቋ መናገር ለማያምኑ ምልክት እንዲሆን ነው። ይኸውም ይህን ሁሉ ቋንቋ መናገራቸው እግዚአብሔር ቢገልጥላቸው ነው እንጂ ብለው ያላመኑት እንዲያምኑ ነው። Speaking with tongues is not for the Christians who received the evangelic Truth, but for the non-Christians, to let them realize the call of God in their own language, unknown before by the apostles. (Fr Tadros Jacob Malaty). ትንቢት የሚለው ተርጉሞ ማስተማር ነው። በደንብ ተርጉሞ ማስተማር ለሚያምን ሰው ነው። ለማያምን ሰው ግን ተርጉመን ብናስተምርም መሳለቂያ ስለሚያደርገው አይገባም ተብሏል።

▶️፯. 1ኛ ቆሮ.14፥19 ላይ “ነገር ግን ሌሎችን ደግሞ አስተምር ዘንድ በማኅበር እልፍ ቃላት በልሳን ከመናገር ይልቅ አምስት ቃላት በአእምሮዬ ልናገር እወዳለሁ” ይላል። አምስት የተባሉ ምንድን ናቸው?

✔️መልስ፦ በእልፍ አንጻር ይተረጎማል። ከዚህ እልፍ ሲል ብዙ ማለት እንደሆነ ሁሉ አምስት ማለቱ ደግሞ ጥቂት ማለት ነው። ስለዚህ ጥቂት ቃላትን ልናገር እወዳለሁ ማለት ነው። እንዲሁም በትርጓሜ አምስት ያለው አምስቱን አዕማድ እንደሆነ ተገልጿል። ምሳሌ በሚመስል ነገር ይመሰላልና።

▶️፰. “ሥራ የሞላበት ትልቅ በር ተከፍቶልኛልና ተቃዋሚዎችም ብዙ ናቸው” ይላል (1ኛ ቆሮ.16፥9)። ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ ሥራ የሞላበት ትልቅ በር የተባለው እግዚአብሔር የገለጠለት ትምህርትና የሰማዕያን ጆሮ ነው። ተቃዋሚዎች ብዙ ናቸው ያለው ከእግዚአብሔር የተገለጠልኝን ትምህርት እንዳላስተምርና ብዙዎች እንዳያምኑ የሚቃወሙኝ ብዙ ናቸው ማለት ነው።

▶️፱. 1ኛ ቆሮ.13፥5 ላይ “ፍቅር የራሱንም አይፈልግም" ሲል ምን ማለቱ ነው?

✔️መልስ፦ የራሱንም አይፈልግም ማለት ለራሴ ብቻ አይልም ማለት ነው። ይኸውም ለሌላውም ያስባል እንጂ ማለት ነው። ግእዙ አጉልቶ ገልጾታል። "ወኢየኀሥሦ ተድላ ለባሕቲቱ" እንዲል።


✔️መልስ፦ አዎ ሰው የማይችለውን ፈተና አይፈተንም። ነገር ግን በመጽሐፈ መነኮሳት እንደተገለጸው ሰው ሲታበይ ትዕቢት ጥሩ እንዳልሆነ እንዲረዳ ከባድ ፈተና ሊታዘዝበት ይችላል። ይህም ቢሆን ግን ሰውየው በረድኤተ እግዚአብሔር ታምኖ እንዲያሸንፍ የሚችለውን እንጂ የማይችለውን አይፈተንም።

▶️፲፫. 1ኛ ቆሮ.10፥25 ላይ "ደግሞም በሥጋ ገበያ የሚሸጡትን ሁሉ ከኅሊና የተነሣ ሳትመራመሩ ብሉ" ይላል። ከቤት ውጭ (ሆቴል) ስንመገብ ሳንጠራጠር መመገብ አለብን ማለት ነው? ሆቴሉ የሌላ ቤተ እምነት ከሆነስ?

✔️መልስ፦ ሳንጠራጠር ባርከን፣ አቡነ ዘበሰማያት ብለን ከበላን ምንም ችግር አይደርስብንም። እየተጠራጠርን ግን መብላት አይገባንም። ለምሳሌ የሌላ እምነት ሰዎች ብቻ የሚኖሩበት ሀገር የሄደ ሰው ከገበያ ገዝቶ ባርኮ ቢበላው ይችላል።

▶️፲፬. 1ኛ ቆሮ.6፥12 ላይ "ኹሉ ተፈቅዶልኞል በእኔ ላይ አንዳች ነገርኳ አይሰለጥንብኝም" ይላል። ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ሙሉ ነጻነትን ሰጥቷቸዋል። ከዚህ ቅዱስ ጳውሎስ ሁሉ ተፈቅዶልኛል ማለቱ ለዚህ ነው። ነገር ግን ሰው ሁሉ ተፈቅዶልኛል ብሎ የማይጠቅመውን ነገር ማድረግ እንደሌለበት ያመለክታል።

▶️፲፭. 1ኛ ቆሮ.10፥12 ላይ "እንደቆመ የሚመሰለው እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ" ይላል። ግልጽ ያድርጉልን?

✔️መልስ፦ እንደቆመ የሚመስለው ማለት በሃይማኖት በምግባር ጸንቼ እየኖርኩ ነው ብሎ የሚያስብ ሰው በትዕቢት እንዳይወድቅ ያለሁት በረድኤተ እግዚአብሔር ነው ብሎ በትሕትና ይጠበቅ ማለት ነው።

▶️፲፮. 1ኛ ቆሮ.9፥11 ላይ "እኛ መንፈሳዊን ነገር የዘራንላችሁ ከሆን የእናንተን የሥጋዊን ነገር እኛ ብናጭድ ትልቅ ነገር ነውን" ሲል ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ መንፈሳዊ ትምህርትን ለሚያስተምሩ መምህራን ሥጋዊ ምግብን መመገብ እንደሚገባ ያመለክታል። ለሚያገለግል ደሞዙ ይገባዋል። ይደልዎ አስቡ ለዘይትቀነይ እንዳለ ጌታ (ሉቃ.10፥7)። ስለዚህ መንፈሳዊ ነገርን የሚያስተምሩ መምህራን ሥጋዊ ነገርን (ደመዎዝን) ቢጠይቁ ትልቅ ነገር አይደለም። የተገባ ነው እንጂ ማለት ነው።

▶️፲፯. "ወንጌልን ብሰብክ እንኳ የምመካበት የለኝም። ግድ ደርሶብኝ ነውና ወንጌልንም ባልሰብክ ወዮልኝ" ይላል (1ኛ ቆሮ.9፥16)። የምመካበት የለኝም ሲል ከምን አንጻር ነው?

✔️መልስ፦ ቅዱስ ጳውሎስ ወንጌልን ቢሰብክ እንኳ ወንጌልን እንዲሰብክ ታዝዞ ያደረገው ስለሆነ የምመካበት አይደለም ብሏል። የታዘዝነውን መፈጸም አያስመካምና።

▶️፲፰. “ቅዱሳን በዓለም ላይ እንዲፈርዱ አታውቁምን" ይላል (1ኛ ቆሮ.6፥2)። ቅዱሳን የተባሉ እነማን ናቸው? ዓለም የተባሉትስ እነማን ናቸው? ከክርስቶስ ውጭ ፈራጅ አለ ወይ?

✔️መልስ፦ ከዚህ ቅዱሳን የተባሉ ካህናት ናቸው። ካህናት ከእግዚአብሔር በተቀበሉት ሰማያዊ ክህነታቸው በምድር ያሰሩት በሰማይ የታሰረ፣ በምድር የፈቱት በሰማይ የተፈታ ስለሆነ በዓለም ላይ ይፈርዳሉ ተብሏል። በዚህ አግባብ ዓለም የተባለ ሰው ሁሉ ነው። እንደ አብ እንደ መንፈስ ቅዱስ በባሕርይው የሚፈርድ ክርስቶስ ብቻ ነው። የቅዱሳን ፍርድ በጸጋ ከክርስቶስ የተገኘ ነው። ስለዚህ ፍርድ የባሕርይና የጸጋ ተብሎ ይከፈላል። በሌላ መልኩ ቅዱሳን የተባሉ ቅዱሳን ሁሉ ናቸው። ቅዱሳን በሠሩት መልካም ሥራ ለኃጥኣን ትምህርትን ይሰጣሉ። ቅዱሳንን አይተው መልካም ሥራን የማይሠሩ ሰዎች ካሉ ግን ይህ ያስፈርድባቸዋል ማለት ነው።

▶️፲፱. “መብል ለሆድ ነው ሆድም ለመብል ነው። እግዚአብሔር ግን ይህንም ያንም ያጠፋቸዋል። ሥጋ ግን ለጌታ ነው እንጂ ለዝሙት አይደለም። ጌታም ለሥጋ ነው” ይላል (1ኛ ቆሮ.6፥13)። ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ መብል ለሆድ ነው ማለት ሆድ የሚኖረው ምግብን ሲበላ ነው ማለት ነው። ሆድም ለመብል ነው ማለት ምግብም ተበልቶ በጊዜያዊነት የሚቀመጥ በሆድ ነው ማለት ነው። እግዚአብሔር ግን መብልንም ሥጋንም ያሳልፋቸዋል። ሥጋ ለጌታ ነው እንጂ ለዝሙት አይደለም ማለት ሥጋ ጌታን ለማገልገል ተፈጥሯል እንጂ ዝሙት ሊሠራበት አልተፈጠረም ማለት ነው። ጌታም ለሥጋ ነው ማለት ጌታም ሥጋችንን ያከብረዋል ማለት ነው።

▶️፳. “በሚስት ታስረህ እንደ ሆንህ መፋታትን አትሻ። በሚስት አልታሰርህ እንደ ሆንህ ሚስትን አትሻ" ይላል (1ኛ ቆሮ.7፥27)። ሚስትን አትሻ የሚለው እንዴት ይተረጎማል?

✔️መልስ፦ በሚስትህ ታስረህ እንደሆነ መፋታትን አትሻ ማለት አግብተህ ከሆነ ሚስትህን አትፍታ፣ ሴቷም ባልን አግብተሽ ከሆነ ባልሽን አትፍቺ ማለት ነው። በሚስት አልታሰርክ እንደሆነ ሚስትን አትሻ ማለት ካላገባህና በድንግልና ጸንተህ መኖር የምትችል ከሆነ በድንግልና ኑር ማለት ነው። ድንግልናውን ጠብቆ መኖር የሚችል ሰው ሳያገባ መኖር ይችላል። ምኞት (ፍትወት) የሚያስቸግረው ሰው ካለ ግን በሥርዓት አግብቶ ይኑር ማለት ነው። በክርስትና ሕይወት የጋብቻ ሕይወትም፣ የምንኩስና ሕይወትም ይፈቀዳል።


© በትረ ማርያም አበባው

✝️የዩቲዩብ ቻናሌ:- We belong to Christ ንሕነ ዘክርስቶስ https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

🌻የፌስቡክ ገጼ Betremariam Abebaw https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።


✝️ የጥያቄዎች መልስ ክፍል 260 ✝️

▶️፩. "እኔም ደግሞ የእግዚአብሔር መንፈስ በእኔ ላይ ያለ ይመስለኛል" ይላል (1ኛ ቆሮ.7፥40)። ቁጥር 26 ላይም "እንዲህ ይመስለኛል" ይላል። ለምንድን ነው በእርግጠኝነት "ነው" ብሎ ያልጻፈው?

✔️መልስ፦ ይመስለኛል ብሎ መናገሩ ስለትሕትና ነው። ጳውሎስ የእግዚአብሔር መንፈስ እንዳለው አስቀድሞም በሐዋ. ሥራ 13፥9 ላይ ተገልጿልና።

▶️፪. "ከማያምኑ ሰዎች አንዱም ቢጠራችሁ ልትሄዱም ብትወዱ ከሕሊና የተነሣ ሳትመራመሩ የሚያቀርቡላችሁን ሁሉ ብሉ። ማንም ግን ይህ ለጣዖት የተሠዋ ነው ቢላችሁ ከዚያ ካስታወቃችሁና ከሕሊና የተነሣ አትብሉ" ይላል (1ኛ ቆሮ.10፥27-28)። ከዚህ ጥቅስ አንጻር ሙስሊም ያረደውን (ከሙስሊም ቤት) ሥጋ መብላት የተከለከለ ነው?

✔️መልስ፦ በሐዲስ ኪዳን ሰው ካልተጠራጠረ ከሌላ ቤተ እምነት ሰዎች ቤት ሄዶም ያቀረቡለትን ማናቸውም ምግብ (ሥጋ ይሁንም አይሁንም) አቡነ ዘበሰማያትን ደግሞ ሳይጠራጠር ቢበላው ምንም ችግር የለውም። ሌሎች እርሱን አይተው የሚሰናከሉበት ከሆነ ግን ስለሌሎች ሲል በኦሪት የተፈቀደውንም እንኳ ሳይቀር ሊተወው ይገባል ተብሏል። በሀገራችን በአፄ ቴዎድሮስ ጊዜ ንጉሠ ነገሥቱ ለሙስሊሞችና ለክርስቲያኖች አንድ በሬ ሰጥተው አርዳችሁ ብሉ አሏቸው። ከዚያ በሬውን ሙስሊሞች አረዱትና ሥጋውን ለክርስቲያኖች አካፈሏቸው። የተከፈለውን ሥጋ የቦሩ ሜዳ መምህር የነበሩት መምህር አካለ ወልድ እንደገና ባርከው ክርስቲያኖችም እንዲበሉት አድርገዋል ይባላል። በዚህም ምክንያት አጼ ቴዎድሮስ "መማር እንደ አካልዬ" ብለዋል ይባላል።

▶️፫. “ከወንድሞች ወገን ያላመነች ሚስት ያለችው ቢኖር እርሷም ከእርሱ ጋር ልትቀመጥ ብትስማማ አይተዋት” ይላል (1ኛ ቆሮ.7፥12)። ይህ እንዴት ይተረጎማል? አንዴ ተጋብተናል መፋታት የለብንም። እኔ ባንቺ አንተ ደግሞ በእኔ ተቀድሰናል። ልጆቻችን መበተን የለባቸውም። ደግሞ መጽሐፍ ቅዱስ ያዝዛል የሚሉ አሉና እንዴት ይታያል?

✔️መልስ፦ ይህ የተነገረው በመጀመሪያ ተመሳሳይ እምነት ኖሯቸው ተጋብተው ኖረው በኋላ ባል ወደ ክርስትና ቢመለስና ሚስት ባትመለስ ወይም ሚስት ተመልሳ ባል ባይመለስ ነገር ግን የሚዋደዱ ከሆነ አይፋቱ ለማለት ነው። ይኸውም ያላመነ ሰው ያመነች ሚስት ካለችውና እርሷን ከወደዳት ቆይቶ ወደ እርሷ እምነት ይሳባልና ነው። ወይም ያላመነች ሴት ያመነ ባል ካላት እርሱን ከወደደችው ቆይቶ ወደ እምነት ይሳባልና ነው። መጀመሪያውንም የተለያየ እምነት ያላቸው ሰዎች እንዲጋቡ ግን መጽሐፍ አይፈቅድም። By the rest he means those, one of whom received the Christian faith while the other did not. It would be up to the non-believer party to remain or to depart. Here he is speaking about marriage before receiving the Christian faith, and one party receives it and not the other. (Fr Tadros Jacob Malaty)

▶️፬. 1ኛ ቆሮ.6፥11 ላይ "በአምላካችንም መንፈስ ታጥባችኋል፣ ተቀድሳችኋል፣ ጸድቃችኋልም" ይላል። ጸድቃችኋልም ሲል እንዴት ይተረጎማል?

✔️መልስ፦ ታጥባችኋል የሚለው ተጠምቃችኋል ለማለት ነው። ተቀድሳችኋል ማለቱ ልጅነትን አግኝታችሁ ከብራችኋል ማለት ነው። ጸድቃችኋል ማለት ሥጋውን በልታችሁ፣ ደሙን ጠጥታችሁ የክርስቶስ አካሎች አማኞች፣ እውነተኞች ሆናችኋል ማለት ነው።

▶️፭. 1ኛ ቆሮ.7፥12 "ሌላውን ግን ከራሴ እናገራለሁ። ከጌታችንም አይደለም" ይላል። ከጌታችንም አይደለም ሲል እንዴት ይተረጎማል?

✔️መልስ፦ ጳውሎስ ከዚህ የተናገረው በወንጌል ስላልተጻፈ ከራሴ እናገራለሁ አለ እንጂ ሐሳቡ ከእግዚአብሔር የተገኘ ነው። ከጌታችን አይደለም ማለቱ ጌታ በዚህ ምድር ሲመላለስ በወንጌል ተጽፎ ካለውና ካስተማረው አይደለም ለማለት ነው።

▶️፮. “ሳይናወጥ በልቡ የጸና ግን ግድ የለበትም። የወደደውን እንዲያደርግ ተፈቅዶለታል። ድንግልናውንም በልቡ ይጠብቅ ዘንድ ቢጸና መልካም አደረገ” ይላል (1ኛ ቆሮ.7፥37)።
የወደደውን እንዲያደርግ ተፈቅዶለታል ሲል ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ የወደደውን እንዲያደርግ ተፈቅዶለታል ማለት ማግባት ቢፈልግ ያግባ፣ በድንግልናው ጸንቶ መኖርን ቢወድድ በድንግልናው ይኑር ማለት ነው።

▶️፯. “የትዳር ጉዳይ ይቅርና በመላእክት እንኳ እንድንፈርድ አታውቁምን” ይላል (1ኛ ቆሮ.6፥3)። ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ እግዚአብሔር ለሐዋርያት በትዳር ጉዳይ ፍርድ መስጠት እንዲችሉ ብቻ አላደረጋቸውም። በተሰጣቸው የክህነት መዓርግ በሚገባ ነገር መላእክትን ሳይቀር የመገዘት ሥልጣን የተሰጣቸው ናቸው ለማለት ነው። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ መልአከ ሞትን ለአሥር ዓመት ገዝቶት እንደነበረ።

▶️፰. “የሚያለቅሱም እንደማያለቅሱ ደስ የሚላቸውም ደስ እንደማይላቸው" ይላል (1ኛ ቆሮ.7፥30)። መምህር ይህን ጥቅስ ያብራሩልን እስኪ?

✔️መልስ፦ በሞት ወይም በዳግም ምጽአት አሁን በዚህ ምድር ስለኃጢአታቸው የሚያለቅሱ ሰዎች በኋላ እንደማያለቅሱ ይሆናሉ ማለት በቀኙ ቁመው መንግሥተ ሰማያትን ወርሰው ደስ ብሏቸው ይኖራሉና። ዛሬ በዚህች ምድር ኃጢአትን በመሥራት ተድላ ደስታ የሚያደርጉ ሰዎች ደግሞ በሞት ወይም በዳግም ምጽአት ጊዜ ደስ እንደማይላቸው ይሆናሉ ማለት በግራው ቆመው በገሀነም ሲሰቃዩ ይኖራሉና ነው።

▶️፱. 1ኛ ቆሮ.6፥18 ላይ "ኃጢአት የሚሠራ ሰው ሁሉ ከሥጋው ውጭ ይሠራልና። ዝሙትን የሚሠራ ግን ራሱ በሥጋው ላይ ኃጢአት ይሠራል" ይላል። ዝሙትን ከሌላው ኃጢአት እንደሚለይ ይናገራል። እንዴት ይታያል?

✔️መልስ፦ ዝሙት በራስ አካል የሚፈጸም፣ የራስን አካል የሚያቆሽሽ ክፉ ሥራ ስለሆነ ነው። ሌላው ኃጢአት ለምሳሌ ግድያን ብንመለከት በጎራዴ፣ በሰይፍና በመሳሰሉት ከአካል ውጭ በሆኑ ነገሮች ይፈጸማል። ዝሙት ግን በራስ አካል የሚፈጸም ኃጢአት ነው። ሰዎች በጋብቻ አንድ ሆነው የሚደርጉት ግንኙነት ግን ከዝሙት አይቆጠርም።

▶️፲. 1ኛ ቆሮ.9፥21 ላይ "ሕግ ለሌላቸው ሕግ እንደሌለው ሆንሁላቸው" ይላል። ትርጉሙን ቢያብራሩልን ።

✔️መልስ፦ ቅዱስ ጳውሎስ ሕግ የሌላቸው የተባሉ አሕዛብን ወደ ሕገ ወንጌል ለመመለስ ወደ አሕዛብነት ሳይለወጥ አሕዛብን መስሎ ከእነርሱ ጋር ይኖርና ወደ ሕገ ወንጌል ይመልሳቸው ነበርና ይህንን ለመግለጽ ነው።

▶️፲፩. 1ኛ ቆሮ.10፥2 ላይ "ሁሉንም ሙሴ በደመናና በባሕር አጠመቃቸው" ይላል። እንዴት ይተረጎማል?

✔️መልስ፦ ለጊዜው ሙሴ በረድኤተ እግዚአብሔር በደመና ከልሎ፣ ባሕር ከፍሎ አሻገራቸው ማለት ነው። ፍጻሜው ግን ባሕሩ የጥምቀት፣ ደመናው የመንፈስ ቅዱስ ምሳሌ ነው ማለት ነው። The cloud is the grace of the Holy Spirit, while the sea refers to baptism. (Theodoret, Bishp of Cyrus)

▶️፲፪. 1ኛ ቆሮ.10፥13 ላይ "በምትችሉት መከራ ነው እንጂ በማትችሉት መከራ ትፈተኑ ዘንድ ያልተዋችሁ እግዚአብሔር የተመሰገነ ነው" ይላል። ሰው በሚችለው መጠን ነው ማለት ነው የሚፈተነው? ፈተና ሲደራረብ እንዴት መቀበል አለብን?


💝 አንደኛ ቆሮንቶስ ክፍል ፫ 💝

💝ምዕራፍ ፲፩፦
-ጳውሎስ እኔ ክርስቶስን እንደምመስል እኔን ምሰሉ እንዳለ
-ወንድ ልጅ ራሱን ተከናንቦ መጸለይ እንደማይገባው
-ሴት ስትጸልይ ራሷን መሸፈን እንደሚገባት
-ሴት ራሷን ባትሸፍን ጸጕራን ትቆረጥ መባሉ
-ወንድ ጸጕሩን ቢያስረዝም ነውር እንደሚሆንበት
-ሳይገባው የክርስቶስን ሥጋና ደም የተቀበለ ፍዳ እንዳለበት

💝ምዕራፍ ፲፪፦
-በመንፈስ ቅዱስ ካልሆነ ኢየሱስ ጌታ ነው የሚል እንደሌለ
-መንፈስ አንድ ቢሆንም ጸጋ ግን ልዩ ልዩ እንደሆነ
-ሁላችንም የክርስቶስ አካል እንደሆንን

💝ምዕራፍ ፲፫፦
-እምነት ሁሉ ኖሮን ፍቅር ከሌለን ከንቱ እንደሆንን
-ፍቅር እንደሚታገሥ፣ ቸርነትን እንደሚያደርግ፣ እንደማያስቀና፣ እንደማያስመካ፣ በደልን እንደማይቆጥር፣ ከእውነት ጋር ደስ ይለዋል እንጂ ከዐመፃ ጋር ደስ እንደማይለው፣ ለዘወትር እንደማይወድቅ
-እምነት፣ ፍቅር፣ ተስፋ ጸንተው ይኖራሉ መባሉ

💝ምዕራፍ ፲፬፦
-በልሳን ስለመናገር መገለጹ
-ለክፋት ነገር እንደ ሕፃናት መሆን በአእምሮ ግን መብሰል እንደሚገባ መነገሩ
-እግዚአብሔር የሰላም አምላክ እንጂ የሁከት አምላክ እንዳልሆነ
-ሴቶች በማኅበር ዝም ይበሉ መባሉ
-ለሴት በማኅበር መካከል መናገር ነውር እንደሆነ
-ሁሉ በአግባብና በሥርዓት ይሁን እንደተባለ

💝ምዕራፍ ፲፭፦
-ጳውሎስ ራሱን ጭንጋፍ ማለቱ
-ስለክርስቶስ ትንሣኤ መነገሩ
-ክርስቶስ ላንቀላፉት በኵራት ሆኖ ከሙታን እንደተነሣ
-ክፉ ባልንጀርነት መልካሙን አመል እንደሚያጠፋ
-ሞት ድል በመነሣት እንደተዋጠ
-ስለ ትንሣኤ ሙታን መነገሩ

💝ምዕራፍ ፲፮፦
-ለቅዱሳን (ለምእመናን) ገንዘብ ማዋጣት እንደሚገባ
-ንቁ በሃይማኖት ቁሙ፣ ጎልምሱ፣ ጠንክሩ መባሉ
-ሁሉ በፍቅር ይሁን መባሉ
-በተቀደሰ አሳሳም እርስ በእርሳችሁ ሰላምታ ተሰጣጡ እንደተባለ

💝የዕለቱ ጥያቄዎች💝
፩. ከሚከተሉት ውስጥ ትክክል ያልሆነው የቱ ነው?
ሀ. ወንዶች ሲጸልዩ ራሳቸውን መሸፈን አለባቸው
ለ. ሴቶች ሲጸልዩ ራሳቸውን መሸፈን አለባቸው
ሐ. ሴት ራሷን ባትሸፍን ጸጕሯን መቆረጥ እንዳለባት
መ. ለወንድ ልጅ ጸጕርን ማስረዘም ነውር ነው
፪. ስለፍቅር ትክክል የሆነው የቱ ነው?
ሀ. ፍቅር አያስመካም አያስታብይም
ለ. ፍቅር አያስቀናም በደልንም አይቆጥርም
ሐ. ፍቅር ከዐመፃ ጋር ደስ አይለውም
መ. ሁሉም
፫. ቅዱስ ጳውሎስ ስለራሱ ምን ብሎ ተናገረ?
ሀ. ከሐዋርያት የማንስ ነኝ
ለ. ጭንጋፍ ነኝ
ሐ. ሀ እና ለ
መ. መልስ የለም

https://youtu.be/qTPZ6QqXbM0?si=_1f9Pc3uhN6S_ArM


ከተለያዩ መንፈሳዊ ኮሌጆችና ጉባኤ ቤቶች የተመረቃችሁ ክቡራን መምህራን እንኳን ደስ አላችሁ። ታላቅ ደስታ ነው። ክቡራን መምህራን
፩. Aemero Zewdea
፪. አባ አትናቴዎስ ወልደ ጎርጎርዮስ
፫. Yared Zera-buruk
የማውቃችሁም የማላውቃችሁም ሁላችሁም እንኳን ደስ አላችሁ።


በዛሬው ዕለት ከመምህር መዝገበ ቃል ገብረ ሕይወት ተምራችሁ የተመረቃችሁ የሰቆጣ ወለህ ነቅዐ ሕይወት የትርጓሜ ጉባኤ ቤት መምህራን እንኳን ደስ አላችሁ።

ዓይናማ የአራቱ ጉባኤያት መምህራን እየመጡ ነው። መምህር ሰሎሞን ላመስግን አራተኛውን ጉባኤ ዛሬ በመመረቅ የአራቱ ጉባኤያት መምህር ሆነዋል።

©Photo credit፦ Hailemariam Zewdu


✔️መልስ፦ የእግዚአብሔርን ጥልቅ ነገር የሚያውቅ ራሱ እግዚአብሔር ነው። መንፈስ ቅዱስም ራሱ እግዚአብሔር በመሆኑ ስለአብ ስለወልድ ሁሉን ያውቃል ማለት ነው። በጥቂቱ ለድኅነት ያህል ስለእግዚአብሔር እናውቅ ዘንድ ደግሞ ለእኛ ለሰው ልጆችም መንፈስ ቅዱስ በጸጋ ገለጠልን ማለት ነው።

▶️፳፭. “መንፈሳዊ ሰው ግን ሁሉን ይመረምራል ራሱ ግን በማንም አይመረመርም” ይላል (1ኛ ቆሮ.2፥15)። ሁሉን ይመረምራል ሲባል እስከ ምን ድረስ ነው? በማንም አይመረመርም የሚለውስ እንዴት ነው?

✔️መልስ፦ መንፈሳዊ ሰው ሁሉን ይመረምራል ማለት እግዚአብሔር በሰጠው የጸጋ ዕውቀት አምላካዊ ምሥጢራትን ሳይቀር ያውቃል ማለት ነው። በሰዎች ላይም በጸጋ ይፈርዳል ማለት ነው። እርሱ ግን በማንም አይመረመርም ማለት በእርሱ ላይ የሚፈርድበት ግን የለም ማለት ነው። መንፈሳዊ ከሆነ አይፈረድበትምና።

▶️፳፮. 1ኛ ቆሮ.2፥16 ላይ "እኛ ግን የክርስቶስ ልብ አለን" ሲል ምን ማለት ነው? ክርስቶስ ልብ አለው ተብሎ ይነገርለታል እንዴ?

✔️መልስ፦ እኛ የክርስቶስ ልብ አለን ማለት ለክርስቶስ አካላዊ ባሕርያዊ ሕይወቱ መንፈስ ቅዱስ እንዳለው ለእኛ ደግሞ በጸጋ አለን ማለት ነው። ልብ ያለው መንፈስ ቅዱስ ነው። ክርስቶስ ሰው እንደመሆኑ ሰብኣዊ ልብ አለው። አምላክ እንደመሆኑ ደግሞ አካላዊ ልቡ አብ ነው።

▶️፳፯. “እኔ ምንም እንኳ በሥጋ ከእናንተ ጋር ባልሆን በመንፈስ ከእናንተ ጋር ነኝ" ይላል (1ኛ ቆሮ.5፥3-4)። በመንፈስ ከእናንተ ጋር ነኝ የሚለው እንዴት ነው?

✔️መልስ፦ በመንፈስ ከእናንተ ጋር ነኝ በአካል ባልገኝም ማለት በልቡናዬ በሐሳቤ ግን ከእናንተ ጋር ነኝ ማለቱ ነው።

▶️፳፰. “በውጭ ባሉ ሰዎች ላይ መፍረድ ምን አግዶኝ? በውስጥ ባሉ ሰዎች ላይ እናንተ አትፈርዱምን" ይላል (1ኛ ቆሮ.5፥12)። የውጭና የውስጥ ሰዎች የተባሉት እነማን ናቸው?

✔️መልስ፦ የውጭ የተባሉ በሃይማኖት የማይመስሉን ሰዎች ናቸው። የውስጥ የተባሉ በሃይማኖት የሚመስሉን ሰዎች ናቸው።

▶️፳፱. “የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነውና” ይላል (1ኛ ቆሮ.1፥18)። ይህ መስቀል የእንጨት መስቀል ወይስ ሕማማተ መስቀልን ያመለክታል?

✔️መልስ፦ ሁለቱንም ያመለክታል። ሕማማተ መስቀልንም መስቀል ይለዋል። ዕፀ መስቀልንም መስቀል ይለዋል። ከዚህ የመስቀሉ ቃል ማለቱ በመስቀሉ የተደረገው ነገር ሁሉ መከራው፣ የአይሁድ ንግግርና የመሳሰለውን ያመለክታል። ይህ ሁሉ ግን ከዕፀ መስቀል ተለይቶ የሆነ ስላልሆነ ዕፀ መስቀልንም ያመለክታል ማለታችን ስለዚህ ነው።

▶️፴. 1ኛ ቆሮ.3፥17 የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እኛው ራሳችን ከሆንን የሕንፃ ቤተ መቅደስ በሐዲስ ኪዳን መኖር ለምን አስፈለገ? በሐዲስ ኪዳን የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ቦታ (በሰው እጅ የተሠራ ሕንፃ) ሊሆን ይችላል?

✔️መልስ፦ የሕንፃ ቤተመቅደስ መኖር ያስፈለገበት ምክንያት እኛ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ለመሆን መጠመቅ፣ መቁረብና የመሳሰሉ ምሥጢራትን መፈጸም ይጠበቅብናልና እነዚህ ደግሞ የሚከናወኑበት ቦታ በማስፈለጉ ነው። ሐዋርያት እንኳ እኛ ቤተ መቅደስ ነን ብለው ወደሕንፃ ቤተ መቅደስ ከመሄድ አልተከለከሉም። "ጴጥሮስና ዮሐንስም በጸሎት ጊዜ በዘጠኝ ሰዓት ወደ መቅደስ ይወጡ ነበር" እንዲል (የሐዋ. ሥራ 3፥1)። በዛሬው ቀን ማለትም ሰኔ 20 እና ሰኔ 21 ቀን ሕንፀተ ቤተክርስቲያን ብለን የምናከብርበት ምክንያት ራሱ ጌታ ሐዋርያትን ይዞ የሐዲስ ኪዳን ሕንፃ ቤተክርስቲያንን ሠርቶ ሥሩ ያለበት ቀን በመሆኑ ነው።


© በትረ ማርያም አበባው


✝️የዩቲዩብ ቻናሌ:- We belong to Christ ንሕነ ዘክርስቶስ https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

🌻የፌስቡክ ገጼ Betremariam Abebaw https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።


✔️መልስ፦ ጳውሎስ እኔ ተከልኩ ማለቱ እኔ መጀመሪያ አስተማርኳችሁ ማለቱ ነው። አጵሎስ አጠጣ መባሉ ደግሞ አጵሎስ ደጋግሞ አስተማራችሁ ማለት ነው። እግዚአብሔር አሳደገ ማለቱ ክብርን፣ ፍጹምነትን፣ ልጅነትን ግን እግዚአብሔር ይሰጣል እንጂ እኛ አንሰጥም ማለቱ ነው።

▶️፱. 1ኛ ቆሮ.1፥23 ላይ "እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን። ለአይሁድ ማሰናከያ ለአሕዛብም ስንፍና ነውና" ሲል ለአይሁድ ማሰናከያ ለአሕዛብም ስንፍና ነውና ሲል እንዴት ይተረጎማል?

✔️መልስ፦ ለአይሁድ ማሰናከያ ነው ማለት አይሁድ ስላላመኑበት የተሰናከሉበት ነው ማለት ነው። ለአሕዛብ ስንፍና ነው ማለት አሕዛብ አምላክ እንዴት ይሰቀላል? እንዴት ይራባል እያሉ ለምን ተሰቀለና ለምን ተራበ የሚለውን ባለማወቅ ይሳለቃሉ ማለት ነው። በመስቀል ተሰቅሎ ማዳን በአሕዛብ ዘንድ እንደ ስንፍና እንደ ሞኝነት ነው የሚታይ ለማለት ነው።

▶️፲. 1ኛ ቆሮ.1፥18 ላይ "የመስቀሉ ነገር በሚጠፉ ሰዎች ዘንድ ስንፍና ነውና" ሲል እንዴት ይተረጎማል?

✔️መልስ፦ የመስቀሉ ነገር ማለት ክርስቶስ በመስቀል ተሰቅሎ የፈጸመው የቤዛነት ሥራ ለአላዋቂዎች ሽንፈት (ሞኝነት) ይመስላቸዋል ማለት ነው። በዚህም ምክንያት ስለማያምኑበት በነፍስ በሥጋ ይጠፋሉ ማለት ነው።

▶️፲፩. 1ኛ ቆሮ.1፥27 ላይ "የዚህን ዓለም ሰነፎች መረጠ" ሲል እንዴት ይተረጎማል?

✔️መልስ፦ በዚህ ዓለም እሳቤ ሰነፎች ይባሉ የነበሩ ሐዋርያትን መረጠ ማለት ነው። ከመመረጣቸው በፊት በዘመናቸው ጠቢባን የሚያሰኙ እንደ ገዢነት፣ የፍልስፍና ዕውቀት፣ ባለሥልጣን አልነበሩምና። ይህን ደግሞ የዘመኑ ጠቢባን ነን ባዮች ከስንፍና ይቆጥሩት ስለነበር በእነርሱ አጠራር ሰነፎች ይባሉ የነበሩ ሐዋርያትን መረጠ ማለቱ ነው።

▶️፲፪. 1ኛ ቆሮ.3፥1 ላይ "ክርስቶስን በማመን ሕፃናት እንደ መሆናችሁ እንጂ እንደ መንፈሳውያን ላስተምራችሁ አልቻልሁም" ሲል እንዴት ይተረጎማል?

✔️መልስ፦ ሕፃናት እንደመሆናችሁ ማለት ወጣንያን እንደመሆናችሁ የወጣኒ ትምህርትን አስተማርኳችሁ እንጂ እንደ መንፈሳውያን ማለት እንደ ፍጹማን የፍጹማንን ትምህርት አላስተማርኳችሁም ማለቱ ነው።

▶️፲፫. 1ኛ ቆሮ.4፥8 ላይ "እኛም ከእናንተ ጋር እንድንነግሥ ብትነግሡ አግባብ በሆነ ነበር" ሲል እንዴት ይተረጎማል?

✔️መልስ፦ ቅዱስ ጳውሎስ ከዚህ እያሳሰበ ያለው ሕዝቡ እውነትን ይዘው በነፍሳዊ ክብር እንዲነግሡ ነው። ከእናንተ ጋር እንድንነግሥ ማለቱ ስለትሕትና ነው። The apostle Paul wishes that they would reign in truth; As, once they reach the kingdom, they would become a crown of his rejoice in the presence of our Lord Jesus Christ.

▶️፲፬. 1ኛ ቆሮ.5፥7 ላይ "ለአዲስ ቡሆ ትሆኑ ዘንድ አሮጌውን እርሾ ከእናንተ አርቁ ገና ቂጣ ናችሁና" ሲል እንዴት ይተረጎማል?

✔️መልስ፦ አሮጌው እርሾ ያለው የቀድሞ የተሳሳተ ትምህርታቸውን ነው። ስለዚህ አዲስ ትምህርት ወንጌልን ትፈጽሙ ዘንድ የቀድሞውን የስሕተት ትምህርት፣ የስሕተት አምልኮ፣ ክፉ ልማድ ተዉ ማለት ነው።

▶️፲፭. 1ኛ ቆሮ.3፥2 ላይ "ወተትን ጋትኋችሁ ጽኑ መብልም ያበላኋችሁ አይደለሁም ገና አልጠነከራችሁምና" ይላል። በወተትና ጽኑ መብል የተመሰሉ እነማን ናቸው?

✔️መልስ፦ ወተት ያለው የወጣኒ ትምህርት ነው። ጽኑ መብል የተባለ ለፍጹማን የሚሰጥ የፍጹማን ትምህርት ነው።

▶️፲፮. 1ኛ ቆሮ.1፥19 ላይ "የጥበበኛዎችን ጥበብ አጠፋለኹ። የአስተዋዮችንም ማስተዋል እጥላለኹ ተብሎ ተጽፏልና" ይላል። ቀደም ብሎ ይህ የተጻፈው በየትኛው መጽሐፍ ክፍል ላይ ነው?

✔️መልስ፦ ይህ የሚገኘው በትንቢተ ኢሳይያስ ነው (ኢሳ.29፥14)።

▶️፲፯. 1ኛ ቆሮ.1፥21 ላይ "በእግዚአብሔር ጥበብ ምክንያት ዓለም እግዚአብሔርን በጥበቧ ስላላወቀች በስብከት ሞኝነት የሚያምኑትን ሊያድን የእግዚአብሔር በጎ ፈቃድ ሆኗልና" ይላል። በስብከት ሞኝነት ማለት ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ የስብከት ሞኝነት የተባለው ክርስቶስ ለእኛ ቤዛ ሆኖ ተራበ፣ ተጠማ፣ ተሰቀለ፣ ደከመ፣ ሞተ እያሉ ማስተማር ነው። ይህ ትምህርት ለአሕዛብ እንደሞኝነት የሚታይ ስለሆነ የስብከት ሞኝነት ተብሏል።

▶️፲፰. 1ኛ ቆሮ.4፥5 ላይ "ጌታ እስከሚመጣ ጊዜው ሳይደርስ አንዳች አትፍረዱ" ይላል። ጊዜው ያለው የትኛው ጊዜ ነው?

✔️መልስ፦ ያ ጊዜ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጻድቃንን በቀኙ ኃጥኣንን በግራ አቁሞ ለሁሉ እንደየሥራው የሚፈርድበት ትንሣኤ ዘጉባኤ (ዳግም ምጽአት) ነው።

▶️፲፱. 1ኛ ቆሮ.4፥10 ላይ "እናንተ የከበራችኹ ናችኹ እኛ ግን የተዋረድን ነን" ይላል። እናንተ እና እኛ የተባሉት እነማን ናቸው?

✔️መልስ፦ ከዚህ ጳውሎስ እኛ ያለው እንደእርሱ በማስተማር የነበሩትን ነው። እናንተ የሚላቸው ደግሞ ተሰባኪዎችን ማለትም ለጊዜው የቆሮንቶስ ሰዎችን ነው።

▶️፳. 1ኛ ቆሮ.4፥20 ላይ "የእግዚአብሔር መንግሥት በኃይል እንጂ በቃል አይደለምና" ይላል። በቃል አይደለም ሲል ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ በቃል ብቻ አይደለም ማለቱ ነው። የእግዚአብሔር መንግሥት ወንጌል ድውያንን በመፈወስ፣ ሙታንን በማስነሣት እና ልዩ ልዩ ተአምራትን በመሥራት ትገለጻለች እንጂ በቃል ብቻ አትነገርም ማለት ነው። ወንጌልን በቃል የሚናገሯት ብቻ ሳይሆን በሕይወትም የሚኖሯት መሆን አለባቸው ለማለት ነው። Preaching the kingdom of God is not enough for salvation, but it is befitting of man to walk the path that befits the kingdom. (Theodoret, Bishop of Cyrus)

▶️፳፩. 1ኛ ቆሮ.5፥1 ላይ "በአጭር ቃል በእናንተ መካከል ዝሙት እንዳለ ይወራል። እንደዚያም ያለ ዝሙት በአሕዛብስ እንኳን የማይገኝ ነው" ይላል። በአሕዛብም የማይገኝ ሲል ምን ለማለት ነው?

✔️መልስ፦ ከዚህ የቆሮንቶስ ሰዎች ልጅ ከአባቱ ሚስት (ከእንጀራ እናቱ) ጋር የሚተኛ ሆኗል። ይህን የመሰለ ክፉ ዝሙት ደግሞ አሕዛብ እንኳ አያደርጉትም ነበርና ነው። ፍሬ ሐሳቡ ልጅ ከአባቱ ሚስት መድረስ አይገባውም የሚል ነው።

▶️፳፪. 1ኛ ቆሮ.4፥13 ላይ "እስከ አሁን ድረስ የዓለም ጥራጊ የሁሉም ጉድፍ ሆነናል" ይላል። ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ ጉድፍና ጥራጊ የተናቀ ነው። በዘመናቸው የነበሩ ሰዎች ሐዋርያትን ይንቋቸው፣ ይሰድቧቸው፣ ያዋርዷቸው ስለነበር ይህንን በምሳሌያዊ አገላለጽ ለመግለጽ የዓለም ጥራጊ፣ የሁሉ ጉድፍ ሆነናል ብለዋል።

▶️፳፫. “ወደ ልጁ ወደ ጌታችን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ኅብረት የጠራችሁ እግዚአብሔር የታመነ ነው" ይላል (1ኛ ቆሮ.1፥9)። ወደ ክርስቶስ የጠራችሁ እግዚአብሔር ሲል ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ የክርስቶስ አካል እንድንሆን በሐዋርያት፣ በሊቃውንት፣ በመምህራን አድሮ በትምህርት የሚጠራን እግዚአብሔር ነው። ክርስቶስ የእግዚአብሔር አብ የባሕርይ ልጅ እንደሆነ እኛም የእግዚአብሔር የጸጋ ልጆች እንሆን ዘንድ ጠራን ማለት ነው።

▶️፳፬. "መንፈስም የእግዚአብሔርን ጥልቅ ነገር ስንኳ ሳይቀር ሁሉን ይመረምራልና ለእኛ እግዚአብሔር በመንፈሱ በኩል ገለጠው" ይላል (1ኛ ቆሮ.2፥10)። ምን ማለት ነው?


✝️ የጥያቄዎች መልስ ክፍል 259 ✝️

▶️፩. መጀመሪያ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች የተላከው መልእክት ምክንያተ ጽሕፈቱ ምን ነበር?

✔️መልስ፦ ሊቃውንት ብዙ ምክንያት እንደነበረው ገልጸዋል። ትዕቢተኞች መምህራን ተነሥተው ስለነበር ለእነርሱ ተግሣጽ፣ የቆሮንቶስ ሰዎች እርስ በእርሳቸው ይጣሉ ስለነበር ለእነርሱ ምክር፣ በብሕትውና ምክንያት ሚስቶቻቸውን ሊፈቱ የነበሩ ሰዎች ስለነበሩ ባልና ሚስት መፋታት እንደሌለባቸው ለመንገር፣ ለሌላው መሰናክል እንዳይሆኑ ለጣዖት የተሠዋን እንዳይበሉ ለመግለጽና ስለሌሎችም ምክንያቶች ጽፎላቸዋል።

▶️፪. 1ኛ ቆሮ.1፥25 ላይ "የእግዚአብሔርም ስንፍና ከሰው ይልቅ ይጠበባልና" ይላል። የእግዚአብሔር ስንፍና ሲል እንዴት ይተረጎማል?

✔️መልስ፦ እግዚአብሔር በባሕርይው ስንፍና የለበትም። ከዚህ የእግዚአብሔር ስንፍና ተብሎ የተገለጸው በማያምኑ ሰዎች የሚነገረው ንግግር ነው። በመስቀል ተሰቅሎ ሰውን ማዳን ባላዋቂ ሰዎች ዘንድ እንደ ስንፍና ይታያል። ነገር ግን ይህ በሰዎች ዘንድ እንደ ስንፍና የሚታየው ነገር በሰዎች ዘንድ ጥበብ ከሚባለው ይበልጣል ማለት ነው። ምክንያቱም ክርስቶስ በመስቀል ተሰቅሎ ሰውን አድኖበታል። ሰውን ለዘለዓለማዊ ክብር አብቅቶበታል። የሰው ጥበብ ግን ለዘለዓለማዊ ክብር አያበቃምና ነው። Fr Tadros Jacob Malaty እንደሚከተለው ገልጸውታል። God’s plan for salvation by the cross, which seems to some people as foolishness; or by Christ’s crucifixion, which seems as weakness is the secret of the believers’ wisdom and strength. What seem as foolishness is more wisdom than the wisdom of men; which, in itself, is unable to comprehend; And what seems as weakness, is stronger than the strength of men; that turns humans into heavenly creatures, the earth into heaven, and the weakness into strength.

▶️፫. 1ኛ ቆሮ.4፥14 ላይ "እኔ ለሁላችሁ ቤዛችሁ ነኝ" ሲል እንዴት ይተረጎማል?

✔️መልስ፦ ቤዛችሁ ነኝ ማለት እናንተን ለማስተማር ስለእናንተ የምደክም መምህራችሁ ነኝ ማለቱ ነው። ቤዛ በብዙ ይተረጎማል። ምሥጢሩ ሞትክነትን ፈንታነትን አይለቅም። ጳውሎስ ስለእነርሱ ጥቅም ብሎ ማስተማሩን ቤዛነት ብሎታል። የፍጡራን ቤዛነት የጸጋ ቤዛነት ነው።

▶️፬. 1ኛ ቆሮ.3፥23 ላይ "ሁሉ የእናንተ ነው። እናንተም የክርስቶስ ናችሁ። ክርስቶስም የእግዚአብሔር ነው" የሚለው እንዴት ይተረጎማል?

✔️መልስ፦ እናንተ የክርስቶስ ናችሁ ማለት እኛ ምእመናን የክርስቶስ ቤተሰቦች ነን ማለት ነው። ክርስቶስ የእግዚአብሔር ነው ማለት ክርስቶስ የእግዚአብሔር አብ የባሕርይ ልጅ ነው ማለት ነው።

▶️፭. 1ኛ ቆሮ.1፥17 ላይ "ለማጥመቅ ክርስቶስ አልላከኝምና" ሲል ምን ለማለት ነው? ማጥመቅ ከሐዋርያዊ አገልግሎት አንዱ አይደለም ወይ? ቅዱስ ጳውሎስ ሰለምን ይህን አለ?

✔️መልስ፦ ማጥመቅም ከሐዋርያዊ አገልግሎቶች አንዱ ነው። ጳውሎስም ቁጥር 14 ላይ ቀርስጶስንና ጋይዮስን እንዳጠመቀ ተገልጿል። ስለዚህ ጳውሎስ ማጥመቅም ይችል ነበር። ከዚህ ለማጥመቅ አልላከኝም ማለቱ ከማጥመቅ ለበለጠ ለስብከት ተላክሁ እንጂ ማለቱ ነው። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅም ይህንኑ ይነግረናል። Preaching the gospel is a task designated for a few; Whereas baptism could be done by anyone in priesthood. (St. John Chrysostom)

▶️፮. 1ኛ ቆሮ.1፥14 ላይ "ከቀርስጶስና ከጋይዮስ በቀር ከእናንተ ወገን ሌላ ስላላጠመቅሁ እግዚአብሔርን አመሰግነዋለሁ" ሲል ምን ለማለት ነው?

✔️መልስ፦ ከዚህ ቅዱስ ጳውሎስ ከቀርስጶስና ከጋይዮስ ውጭ ባለማጥመቁ እግዚአብሔርን አመስግኗል። ምክንያቱም በወቅቱ አንዳንዶች በጳውሎስ ስም አምነው በጳውሎስ ስም የሚጠመቁ መስሏቸው ነበር። መጠመቅ ደግሞ በክርስቶስ ስም በእግዚአብሔር ስም ነው እንጂ በፍጡር ስም አይደለምና። The apostle thanks God that He did not allow him to baptize anyone other than those whom he mentioned by name; lest anyone should say that he had baptized in his own name. He was keen, as much as possible, not to baptize more, so as not to be accused of forming a group bound to his name. (Fr Tadros Jacob Malaty)

▶️፯. 1ኛ ቆሮ.3፥15 ላይ ያለውን ቃል [የተቃጠለበት በእሳት (through fire) ይድናል] የሚለውን ይዘው አንድ ሰባኪ በአለማወቅ (by ignorance) የስሕተት ትምህርት ቢያስተምር ከእግዚአብሔር ምሕረት የተነሣ ይድናል ሲሉ (Adam Clarke) ሎሎች ደግሞ ይድናል (መንግሥተ ሰማያት ይገባል ግን አክሊል ወይም ሽልማት (reward) አያገኝም ይላሉ። አንዳንዶችም through fire የሚለውን ይዘው ይህ ሰው በpurgatory ይድናል ይላሉ (Ambrosiaster and Augustine). እርስዎ ስለእነዚህ ሰዎች ምን ይላሉ? በተለይ ስለ አክሊል የሚናገሩትን ትኩረት አድርገው ቢመልሱልኝ።

✔️መልስ፦ Purgatory በካቶሊካውያን ዘንድ ያለ አስተምህሮ ነው። በእኛ ዘንድ ኢዘከረ ሠለስተ ዓለማተ ብለን ከገሀነም ካልገቡ መንግሥተ ሰማያት፣ ከመንግሥተ ሰማያት ካልገቡ ገሀነም ነው። መካነ ንስሓ የሚፈጸምበት ሦስተኛ ቦታ አለ አንልም። ስለዚህ ከዚህ አውግስጢኖስና አምብሮሲያስተር የተናገሩት በእኛ ዘንድ ተቀባይነት የለውም። Adam Clarke እና ሌሎችም መንግሥተ ሰማያት ይገባል ግን አክሊል አያገኝም ያልከውም በእኛ አስተምህሮ ድጋፍ የለውም። መንግሥተ ሰማያት ከመግባት የበለጠ ሽልማት የለምና። የጻድቃን ሽልማታቸው መንግሥተ ሰማያት ናትና። አክሊል የሚባለው ክብር ነው። መንግሥተ ሰማያት የገባ ሰው ሁሉ ደግሞ በማያቋርጥ ክብር ይኖራል። ይህንንም መተርጉማን ተወስኮ ዘነሳእያን (አንድም ዘነሳሕያን) ይሉታል። በማወቅም ይሁን ባለማወቅ አንድ ሰው የስሕተት ትምህርትን ካስተማረ ኃጢአት ሆኖ ይቆጠርበታል (በአእምሮ አው በኢያእምሮ እንዲል ካህን)። የት ይገባል ለሚለው ግን ፍርዱ የእግዚአብሔር ስለሆነ አናውቀውም። ሰባኪው እውነተኛ ትምህርት አስተምሮ ከነበረ የመልካም ትምህርቱን ዋጋ ያገኛል። When a teacher teaches what is true; Those who follow him would be like gold or silver, purified and glitter, as though by fire; while those who do not follow him would be burned; but the teacher himself would not be harmed; and he will have his reward anyway. (Theodoret, Bishop of Cyrus)

▶️፰. 1ኛ ቆሮ.3፥6 ላይ "እኔ ተከልሁ። አጵሎስም አጠጣ። ነገር ግን እግዚአብሔር አሳደገ" ሲል እንዴት ይተረጎማል?


Forward from: በትረማርያም አበባው Betremariam Abebaw
ለልጅዎ የግእዝ ስም ማውጣት ከፈለጉ እነሆ
ግእዝ__አማርኛ
፩) መዓርዒር__ጣፋጭ
፪) አሜር__ፀሐይ
፫) አርያም_ሰማይ
፬) አምኃ_እጅ መንሻ
፭) ብሥራት___የምስራች
፮) ሰሎሜ_ሰላም
፯) አሜን__እውነት/ይሁንልኝ
፰) ሠዊት__እሸት
፱) ጸገየ___አበበ
፲) አስካል____ፍሬ
፲፩) ልዑል____ከፍ ያለ
፲፪) ሣህሉ____ይቅርታው
፲፫) ቀጸላ_አክሊል
፲፬) ሐመልማል___የለመለመ
፲፭) ከሃሊ_የሚችል ቻይ
፲፮) ጸዳሉ_መብራቱ
፲፯) ፈትለ ወርቅ____የወርቅ ፈትል
፲፰) ፊደል_ፊደል
፲፱) ማኅተም____ማተሚያ
፳) ሥዩም__የተሾመ ሹም
፳፩) ስብሐት____ምስጋና
፳፪) ስቡሕ_ምስጉን
፳፫) ተቅዋም_መቅረዝ
፳፬) ንጹሕ_የነጻ
፳፭) ሰላማ__ሰላም
፳፮) አዳም__ያማረ
፳፯) ዳግም_የደገመ
፳፰) ግሩም_ተፈሪ
፳፱) ጥዑም____የሚጣፍጥ
፴) ፍጹም__የተቀባ
፴፩) ይኄይስ____ተሻለ
፴፪) ሐዳስ/ሐዲስ___አዲስ
፴፫) ሕዳሴ__መታደስ
፴፬) ሰንኮሪስ_መምህር
፴፭) መቅደስ_ማመስገኛ
፴፮) ሞገስ__ባለሟል የተወደደ
፴፯) ትዕግሥት_መቻል
፴፰) ንጉሥ__የነገሠ
፴፱) ወራሲ__ወራሽ
፵) ውዳሴ__ምስጋና
፵፩) ጌራወርቅ____የወርቅ ዘውድ
፵፪) ማኅደር_ማደሪያ
፵፫) ምሕረት_ይቅርታ
፵፬) መሓሪ__ይቅር ባይ
፵፭) ሠምረ__ወደደ
፵፮) ሥሙር_ተወዳጅ
፵፯) ሥምረት____መወደድ
፵፰) ነጸረ__ተመለከተ
፵፱) ምሥጢሩ____ምሥጢሩ
፶) መራሒ____መሪ
፶፩) ፍሥሓ_ደስታ
፶፪) አእመረ____አወቀ
፶፫) አእምሮ____እውቀት
፶፬) ፍቅር__መውደድ
፶፭) ክቡር__የከበረ
፶፮) ደብሩ__ተራራው
፶፯) ተግባር_ሥራ
፶፰) ረቂቅ__ረቂቅ
፶፱) መብረቁ____መብረቁ
፷) ነጸብራቅ__ነጸብራቅ

፷፩) ይባቤ___እልልታ
፷፪) ጥበቡ___ብልሃቱ
፷፫) መሠረት__መሠረት
፷፬) ብሑት___ስልጡን
፷፭) ትሕትና___ትሕትና
፷፮) ተከሥተ__ተገለጠ
፷፯) ሃይማኖት_ሃይማኖት
፷፰) በየነ__ፈረደ
፷፱) መኰንን____ገዢ
፸) በጽሐ__ደረሰ
፸፩) መስፍን____የሚገዛ
፸፪) ምስፍና____ግዛት
፸፫) ክርስቲያን____ክርስቲያን
፸፬) ወሰን__ድንበር
፸፭) መዋዒ_አሸናፊ
፸፮) ትንሣኤ_መነሳት
፸፯) ነቅዐ ሕይወት_የሕይወት ምንጭ
፸፰) ገዛኢ__ገዢ
፸፱) ምሕርካ ክርስቶስ___የክርስቶስ ምርኮ
፹) ባራኪ____የሚባርክ
፹፩) መልአክ____አለቃ
፹፪) በረከት____በረከት
፹፫) ህላዌ_መኖር
፹፬) ኂሩት_ቸር የሆነች
፹፭) ልባዌ_ማስተዋል
፹፮) ቤዛዊት_ያዳነች የምታድን
፹፯) ስርጋዌ____ሽልማት
፹፰) ስርጉት____የተሸለመች
፹፱) ተስፋ_ተስፋ
፺) ኬንያ__ብልሃተኛ
፺፩) ኖላዊ__ጠባቂ
፺፪) መርዓዊ____ሙሽራ
፺፫) ማዕዶት____መሻገሪያ
፺፬) ወልታ____መከታ/ጋሻ
፺፭) ሐዋዝ____ያማረ
፺፮) ግእዛን____ነጻነት
፺፯) ሕሊና____ሕሊና
፺፰) ማኅሌት____ምስጋና
፺፱) ኅሩይ__ምርጥ
፻) ሲሳይ__ምግብ
፻፩) ሠናይ____ያማረ
፻፪) ፈታሒ____የሚፈርድ
፻፫) ሐሴት____ደስታ
፻፬) ትርሲት_ሽልማት
፻፭) ተዋናዪ_ተጫዋች
፻፮) ዐቢይ___ከፍ ያለ
፻፯) ትውፊት_ስጦታ
፻፰) ኃያል_የበረታ
፻፱) ጽጌ__አበባ
፻፲) ፍሬሕይወት____የሕይወት ፍሬ
፻፲፩) ምዕዳን_ምክር
፻፲፪) ንኡድ___ያማረ
፻፲፫) ነገደ___ሄደ
፻፲፬) ነጎድጓድ____ነጎድጓድ
፻፲፭) ጸዓዳ_ነጭ
፻፲፮) ሠረጸ_በቀለ
፻፲፯) ደምፀ____ተሰማ
፻፲፰) ሮሐ_ወለወለ/አራገበ/አናፈሰ
፻፲፱) ናርዶስ_ሽቱ
፻፳) እፀ ሕይወት___የሕይወት እንጨት

© በትረማርያም አበባው (በነገራችን ላይ በትረ ማርያም ማለት የማርያም ወገን ማለት ነው። በትር ወገን ተብሎ እንደሚተረጎም አስተውል)


🌻የፌስቡክ ገጼ Betremariam Abebaw https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:-
ንሕነ ዘክርስቶስ
https://www.youtube.com/@edenawizechristos ነው።


Forward from: በትረማርያም አበባው Betremariam Abebaw
Reposted

_ ስም____ትርጉም
1 ፊላታዎስ፦የአምላክ ወዳጅ
2 ሮብዓም፦ሕዝብ ይብዛ
3 ቴዎድሮስ፦የእግዚአብሔር ስጦታ
4 ሮቤል፦እነሆ ወንድ ልጅ
5 ማራናታ፦ጌታ ሆይ ና
6 ቤቴል፦የእግዚአብሔር ቤት
7 ቄርሎስ፦የተመረጠ ምርጥ
8 እስጢፋኖስ፦አክሊል
9 ሳውል/ሳኦል፦ከእግዚአብሔር የተለመነ
10 ሴዴቅያስ፦የእግዚአብሔር ጽድቅ
11 ፊቅጦር፦ኀዘኔን አራቀልኝ
12 ንፍታሌም፦ታጋይ የሚታገል
13 ዮርዳኖስ፦ወራጅ
14 ዮአስ፦እግዚአብሔር ሰጥቷል
15 ገነት፦የአትክልት ስፍራ
16 ፊልድልፍያ፦የወንድማማች ፍቅር
17 ዲና፦ፈረደ
18 ማኑሄ፦እረፍት
19 መልሕቅ፦ከብረት የተሠራ የመርከብ ማቆሚያ
20 ራማ፦ከፍታ
21 ኤርምያስ፦እግዚአብሔር ከፍ ያደርጋል
22 ሐና፦ ስጦታ
23 ሕርያቆስ፦ኅሩይ
24 ፊልጶስ፦ወንድም ወዳጅ
25 ቶማስ፦ፀሐይ
26 ጎርጎርዮስ:-ንቁሕ የተጠበቀ
27 ማትያስ፦ፀሐይ
28 ቀሌምንጦስ፦ግንብ
29 አቤል፦በግ ወይም ደመና
30 ኖኅ፦ደስታ
31 ሴም፦ተሾመ
32 ይሥሐቅ፦ደስታ አንድም
33 ሙሴ፦የውሃ ልጅ
34 አሮን፦የእግዚአብሔር ተራራ
35 ጌዴዎን፦እግዚአብሔር ኃያል ነው
36 እሴይ፦ዋጋየ
37 አሚናዳብ፦መንፈስቅዱስ
38 ዳዊት፦የተወደደ ልበ አምላክ
39 ዕንባቆም፦ጠቢብ አዋቂ አስተዋይ
40 ሄኤሜን፦ምኞቴን አገኘሁ
41 አሞጽ፦እግዚአብሔር ጽኑ ነው
42 ዮናስ፦ርግብ
43 ሐጌ፦የእግዚአብሔር መልእክተኛ
44 ራኄል፦በግዕት
45 ዕዝራ፦ረዳቴ
46 ሔርሜላ፦ከክብር ዘመድ የተገኘች
47 መርቆሬዎስ፦የአባት ወዳጅ
48 ኤጲፋንዮስ፦ምስጢር ገላጭ
49 ሜሮን፦የተባረከ ሽቱ
50 ሱላማጢስ፦ሰላማዊት
51 ሶምሶን፦ፀሐይ
52 ብንያም፦የቀኝ እጄ ልጅ
53 ማርታ፦እመቤት
54 ሊዲያ፦ፈራሂተ እግዚአብሔር
55 ኤፍሬም፦ፍሬያማ ፍሬው
56 ኤፍራታ፦ክብርት የተከበረች
57 ታዴዎስ፦ተወዳጅ
58 ኢየሩሳሌም፦የሰላም ሀገር
59 ሄኖስ፦ሰው
60 ሰሎሜ፦ሰላም
61 ሩሐማ፦ምሕረት
62 ዮዳሔ፦እግዚአብሔር ያውቃል
63 ቴዎፍሎስ፦የእግዚአብሔር ወዳጅ
64 ኑኃሚን፦ደስታየ
65 ናትናኤል፦የእግዚአብሔር ስጦታ
66 አዛሄል፦እግዚአብሔር ያያል
67 ኢዮስያስ፦እግዚአብሔር ይደግፋል
68 ኢዩኤል፦እግዚአብሔር አምላክ ነው
69 በርናባስ፦የመጽናናት ልጅ
70 ሶፎንያስ፦እግዚአብሔር ሰውሯል/ጠብቋል
71 ሕዝቅኤል፦እግዚአብሔር ብርታትን ይሰጣል
72 ኬልቅያስ፦እድል ፈንታየ እግዚአብሔር
73 ሳሙኤል፦እግዚአብሔር ሰማኝ
74 ሚኪያስ፦ እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው!
75 ሆሴዕ፦እግዚአብሔር ያድናል
76 ሔዋን፦የሕያዋን ሁሉ እናት
77 ሕዝቅያስ፦እግዚአብሔር ኃይሌ ነው
78 መልከጼዴቅ፦የሰላም ንጉሥ
79 ሚልኪያስ፦መልእክተኛየ
80 ሣራ፦ልዕልት
81 ስምዖን፦ሰማ
82 ብንያም፦የቀኝ እጄ ልጅ
83 ናሆም፦መጽናናት ማለት ነው።
84 ናታን፦ እግዚአብሔር ሰጥቷል
85 አልዓዛር፦ትርጉሙ እግዚአብሔር ረድቷል
86 አስቴር፦ኮከብ
87 አቤሜሌክ፦የንጉሥ አገልጋይ
88 አቤሴሎም፦አባቴ ሰላም ነው
89 አብድዩ፦የእግዚአብሔር አገልጋይ
90 አብራም፦ታላቅ አባት
91 አብርሃም፦የብዙዎች አባት
92 አኪያ፦እግዚአብሔር ወንድሜ ነው
93 አክዐብ፦የአባት ወንድም
94 ባሮክ፦ቡሩክ
95 አዳም፦መልካሙ
96 ኢሳይያስ፦ እግዚአብሔር ደኅንነት ነው
97 ባርቅ፦መብረቅ
98 ኢያሱ፦እግዚአብሔር አዳኝ ነው
99 ኢዮሳፍጥ፦እግዚአብሔር ፈርዷል
100 ኢዮራም፦እግዚአብሔር ከፍ ከፍ አለ
101 ኢዮርብዓም፦ሕዝቡ እየበዛ ይሄዳል
102 ቤተልሔም፦የእንጀራ ቤት
103 ኢዮአስ፦እግዚአብሔር ሰጥቷል
104 ኢዮአቄም፦እግዚአብሔር አቆመ
105 ኢዮአብ፦እግዚአብሔር አባት ነው
106 ኢዮአታም፦እግዚአብሔር ፍጹም ነው
107 ኢዮአካዝ፦እግዚአብሔር ይዟል
108 ኤልሳዕ፦እግዚአብሔር ደኅንነት ነው
109 ኤልያስ፦እግዚአብሔር አምላክ ነው
110 ኤልያቄም፦እግዚአብሔር ያስነሳል
111 ኤዶም፦ቀይ/የገነት ሌላ ስም ነው
112 እስራኤል፦ከእግዚአብሔር ጋር ይታገላል ያሸንፍማል
113 ኤልሳቤጥ፦እግዚአብሔር መሐላየ ነው
114 ኤልሻዳይ፦ሁሉን ቻይ አምላክ
115 ሀሌሉያ፦እግዚአብሔርን አመስግኑ
116 ሰሎሞን፦ሰላማዊ
117 ኬብሮን፦ኅብረት
118 አዛርያስ፦እግዚአብሔር ረድቷል
119 ኤደን፦ደስታ
120 ዖዝያን፦እግዚአብሔር ኃይሌ ነው
121 ዘካርያስ፦እግዚአብሔር ያስታውሳል
122 ይሳኮር፦ ዋጋዬ
123 ይዲድያ፦በእግዚአብሔር የተወደደ
124 ዮሐናን፦እግዚአብሔር ጸጋ ሰጪ ነው
125 ዮሐንስ፦እግዚአብሔር ጸጋ ነው
126 ዮሴፍ፦ይጨምር
127 ዮናስ፦ርግብ
128 ዮናታን፦እግዚአብሔር ሰጥቷል
129 ዮአኪን፦እግዚአብሔር ያቆማል
130 ዮካብድ፦እግዚአብሔር ክብር ነው
131 ምናሴ፦ማስረሻ
132 ዮፍታሔ፦እግዚአብሔር ይከፍታል
133 ዲቦራ፦ንብ
134 ዳንኤል፦እግዚአብሔር ፈራጅ ነው
135 ጎዶልያስ፦እግዚአብሔር ታላቅ ነው
136 ጽዮን፦አምባ
137 ጳውሎስ፦ብርሃን ማለት ነው።
138 ሴት፦ምትክ ማለት ነው።
139 ጴጥሮስ፦አለት ማለት ነው።
140 ሄኖክ፦ታደሰ ማለት ነው።


ምንጭ:-ቅዱሳት መጻሕፍት ከመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት እንዲሁም የአንድምታ ትርጓሜ መጻሕፍት

© በትረ ማርያም አበባው


✝️የዩቲዩብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

🌻የፌስቡክ ገጼ Betremariam Abebaw https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።


የግእዝ ቋንቋ ትምህርትን በነጻ ይማሩ
ትምህርቱ ከሐምሌ 07 እስከ ነሐሴ 30 ድረስ ከሰኞ እስከ ዓርብ በተጠቀሰው ጊዜና ቦታ ይሰጣል።

በአካል መማር ለምትፈልጉ በተጠቀሰው ስልክ ደውላችሁ መመዝገብ ትችላላችሁ።




💚 አንደኛ ቆሮንቶስ ክፍል ፪ 💚

💚ምዕራፍ ፮፦
-ቅዱሳን በዓለም ላይ እንደሚፈርዱ
-ዐመፀኞች፣ ተሳዳቢዎች፣ ሌቦች፣ ጣዖትን አምላኪዎች የእግዚአብሔርን መንግሥት እንደማይወርሱ
- ሁሉ ቢፈቀድልንም ሁሉ ግን እንደማይጠቅም
-ሥጋችን የክርስቶስ አካል እንደሆነ
-ከዝሙት መሸሽ እንደሚገባ
-በሥጋችን እግዚአብሔርን ማክበር እንደሚገባን

💚ምዕራፍ ፯፦
-ባል ለሚስቱ የሚገባትን እንዲያደርግላት ሚስትም ለባሏ እንዲሁ እንድታደርግ መነገሩ
-በምኞት ከመቃጠል ማግባት እንደሚሻል
-ራሱን መግዛት ያልቻለ እንዲያገባ
-በሐዲስ ኪዳን መገረዝም አለመገረዝም ሕግ እንዳልሆነ

💚ምዕራፍ ፰፦
-ፍቅር እንደሚያንጽ
-ሌላው ከሚሰናከል የተፈቀደልንንም መተው እንደሚገባ

💚ምዕራፍ ፱፦
- ጳውሎስ ወንጌልን ባልሰብክ ወዮልኝ ብሎ እንደተናገረ
-ጳውሎስ አይሁድን ለመሳብ እንደ አይሁዳዊ እንደሆነ፣ ሕግ ያለው ሲሆን ሕግ እንደሌላቸው እንደሆነ
-ታገኙ ዘንድ ሩጡ እንደተባለ

💚ምዕራፍ ፲፦
-እስራኤላውያን ከጥም አውጥቶ ያረካ መንፈሳዊ ዓለት ክርስቶስ እንደሆነ መነገሩ
-እንደ ቆመ የሚመስለው እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ መባሉ
-እግዚአብሔር ከሚቻለን በላይ እንደማይፈትነን
-ጣዖትን ከማምለክ መሸሽ እንደሚገባ
-የባልንጀራችንን ጥቅም እንጂ የራሳችንን ጥቅም ብቻ በመፈለግ እንዳንኖር
-የምናደርገውን ሁሉ ስለእግዚአብሔር ክብር ማድረግ እንዲገባን

💚 የዕለቱ ጥያቄዎች 💚
፩. ከሚከተሉት ውስጥ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም ከተባሉት መካከል የሆነው የቱ ነው?
ሀ. ዐመፀኞችና ሴሰኞች
ለ. ጣዖትን አምላኪዎች
ሐ. ተሳዳቢዎችና ሌቦች
መ. ሁሉም
፪. ከሚከተሉት ውስጥ "ባል ለሚስቱ የሚገባትን ያድርግላት እንደዚሁም ደግሞ ሚስቲቱ ለባልዋ" የሚለው ኃይለ ቃል የሚገኝበት ጥቅስ የትኛው ነው?
ሀ. ፩ኛ ቆሮ.፮፥፮
ለ. ፩ኛ ቆሮ.፰፥፪
ሐ. ፩ኛ ቆሮ.፯፥፫
መ. ፩ኛ ቆሮ.፱፥፬

https://youtu.be/gAJOsbrZ6Eo?si=S5tJWIsMkqSxM6OJ

20 last posts shown.