💝 አንደኛ ቆሮንቶስ ክፍል ፫ 💝
💝ምዕራፍ ፲፩፦
-ጳውሎስ እኔ ክርስቶስን እንደምመስል እኔን ምሰሉ እንዳለ
-ወንድ ልጅ ራሱን ተከናንቦ መጸለይ እንደማይገባው
-ሴት ስትጸልይ ራሷን መሸፈን እንደሚገባት
-ሴት ራሷን ባትሸፍን ጸጕራን ትቆረጥ መባሉ
-ወንድ ጸጕሩን ቢያስረዝም ነውር እንደሚሆንበት
-ሳይገባው የክርስቶስን ሥጋና ደም የተቀበለ ፍዳ እንዳለበት
💝ምዕራፍ ፲፪፦
-በመንፈስ ቅዱስ ካልሆነ ኢየሱስ ጌታ ነው የሚል እንደሌለ
-መንፈስ አንድ ቢሆንም ጸጋ ግን ልዩ ልዩ እንደሆነ
-ሁላችንም የክርስቶስ አካል እንደሆንን
💝ምዕራፍ ፲፫፦
-እምነት ሁሉ ኖሮን ፍቅር ከሌለን ከንቱ እንደሆንን
-ፍቅር እንደሚታገሥ፣ ቸርነትን እንደሚያደርግ፣ እንደማያስቀና፣ እንደማያስመካ፣ በደልን እንደማይቆጥር፣ ከእውነት ጋር ደስ ይለዋል እንጂ ከዐመፃ ጋር ደስ እንደማይለው፣ ለዘወትር እንደማይወድቅ
-እምነት፣ ፍቅር፣ ተስፋ ጸንተው ይኖራሉ መባሉ
💝ምዕራፍ ፲፬፦
-በልሳን ስለመናገር መገለጹ
-ለክፋት ነገር እንደ ሕፃናት መሆን በአእምሮ ግን መብሰል እንደሚገባ መነገሩ
-እግዚአብሔር የሰላም አምላክ እንጂ የሁከት አምላክ እንዳልሆነ
-ሴቶች በማኅበር ዝም ይበሉ መባሉ
-ለሴት በማኅበር መካከል መናገር ነውር እንደሆነ
-ሁሉ በአግባብና በሥርዓት ይሁን እንደተባለ
💝ምዕራፍ ፲፭፦
-ጳውሎስ ራሱን ጭንጋፍ ማለቱ
-ስለክርስቶስ ትንሣኤ መነገሩ
-ክርስቶስ ላንቀላፉት በኵራት ሆኖ ከሙታን እንደተነሣ
-ክፉ ባልንጀርነት መልካሙን አመል እንደሚያጠፋ
-ሞት ድል በመነሣት እንደተዋጠ
-ስለ ትንሣኤ ሙታን መነገሩ
💝ምዕራፍ ፲፮፦
-ለቅዱሳን (ለምእመናን) ገንዘብ ማዋጣት እንደሚገባ
-ንቁ በሃይማኖት ቁሙ፣ ጎልምሱ፣ ጠንክሩ መባሉ
-ሁሉ በፍቅር ይሁን መባሉ
-በተቀደሰ አሳሳም እርስ በእርሳችሁ ሰላምታ ተሰጣጡ እንደተባለ
💝የዕለቱ ጥያቄዎች💝
፩. ከሚከተሉት ውስጥ ትክክል ያልሆነው የቱ ነው?
ሀ. ወንዶች ሲጸልዩ ራሳቸውን መሸፈን አለባቸው
ለ. ሴቶች ሲጸልዩ ራሳቸውን መሸፈን አለባቸው
ሐ. ሴት ራሷን ባትሸፍን ጸጕሯን መቆረጥ እንዳለባት
መ. ለወንድ ልጅ ጸጕርን ማስረዘም ነውር ነው
፪. ስለፍቅር ትክክል የሆነው የቱ ነው?
ሀ. ፍቅር አያስመካም አያስታብይም
ለ. ፍቅር አያስቀናም በደልንም አይቆጥርም
ሐ. ፍቅር ከዐመፃ ጋር ደስ አይለውም
መ. ሁሉም
፫. ቅዱስ ጳውሎስ ስለራሱ ምን ብሎ ተናገረ?
ሀ. ከሐዋርያት የማንስ ነኝ
ለ. ጭንጋፍ ነኝ
ሐ. ሀ እና ለ
መ. መልስ የለም
https://youtu.be/qTPZ6QqXbM0?si=_1f9Pc3uhN6S_ArM