🎤✨ድምፀ ተዋህዶ✨🎤


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Music


ድምጻችን ለተዋህዶ ሐይማኖታችን ለኢትትዮጲያ አገራችን

የእግዚአብሔር ሰላም የእናታች የቅድስት ድንግል ማርያም ምልጃና ፀሎት የመላእክት ጥበቃና የቅዱሳን በረከት ከናንተ
ጋር ይሁን አሜን!
📣ለማስታወቂያ ሥራ👉 @Mane_tekel21

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Music
Statistics
Posts filter


ከ17 ደቂቃ ቦኃላ ይጠፋል


የ 200 ብር ካርድ የሚያስሸልም ጥያቄ!

በኢትዮጵያ በጣም አስቸጋሪ የነበረዉ  ረሀብ መች አመተምህረት ነበረ




ብፁዕ አቡነ ድሜጥሮስ በኩዌት ከኢፌዴሪ አምባሳደር ሰኢድ ሙሀመድ  ጋር ተወያዩ !

መጋቢት 18 ቀን 2017 ዓ.ም [ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ]

የሊባኖስ የተባበሩት አረብ ኤምሬትና የመካከለኛው ምሥራቅ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ድሜጥሮስ በኩዌት ከኢፌዴሪ አምሳደር ሰይድ ሙሀመድ ጋር ስለ ኩዌት ደብረ ምሕረት አቡነ ተክለሃይማኖት ወቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን ከኩዌት መንግሥት ሕጋዊ እውቅና ስለሚያገኝበት ሁኔታ ከሚመለከተው አካል ጋር በመተባበር እንዴት መስራት እንዳለባቸው ተወያይተዋል ።

መ/ሐ/ አባ ታዴዎስ በቤተ ክርቲያኒቱና በኤምባሲው መካከል ያለውን ጠንካራ ግንኙነት ገልጸው ለአገልግሎታችን መሳካት ክቡር አምባሳደር ሰይድ ሙሀመድ ለቤተክርስቲያኒቱ እያደረጉ ላለው ትብብር አመስግነዋል ።

© ማዕዶት

✨✨✨✨✨✨
✝️#ድምፀ_ተዋህዶ✝️
✨✨✨✨✨✨


የኦርየንታል አብያተ ክርስቲያናት ጉባኤ በጀርመን በርሊን መካሄድ ጀመረ ! 

መጋቢት 18 ቀን 2017 ዓ.ም [ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ]

በኦርየንታል አብያተ ክርስቲያናትና በጀርመን ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር በሚል ዓላማ በጀርመን ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን የተዘጋጀው የኦርየንታል አብያተ ክርስቲያናት ጉባኤ መጋቢት 17 ቀን 2017 ዓ. ም በህንድ ማላንካራን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ የመክፈቻ ጸሎት በጀርመን ዋና ከተማ በርሊን ተጀመረ።

እስከ መጋቢት 19 ቀን 2017 ዓ. ም በሚካሄደው በዚህ ጉባኤ በውጭው ዓለም በተለይ በጀርመን ያሉ የኦርየንታል አብያተ ክርስቲያናት አባላት እናት ቤተ ክርስቲያናቸውን በመደገፍ ረገድ ያላቸውን ሚና አስመልክቶ የየራሳቸውን ተሞክሮ የሚያቀርቡበትና ውይይት የሚደረግበት ነው። በመኾኑም በጉባኤው የአምስት አኀት አብያተ ክርስቲያናት ተወካዮች የተገኙ ሲኾን፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖትን በመወከል ብፁዕ አቡነ ዲዮናስዮስ የጀርመንና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ተገኝተዋል። 

ጉባኤውን በጸሎት የከፈቱት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ ማርቶማ ማቴዎስ 3ኛ የህንድ ማላንካራ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ የጉባኤውን አስፈላጊነት በማውሳት ፤ ለአዘጋጆቹ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በተመሳሳይም ከሮማ ካቶሊክ፣ ከምሥራቅ ኦርቶዶክስ፣ ከጀርመን ወንጌላዊት አብያተ ክርስቲያናት ተወካዮች በጉባኤው በመገኘት መልእክት አስተላልፈዋል።

©የጀርመንና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሚድያ

✨✨✨✨✨✨
✝️#ድምፀ_ተዋህዶ✝️
✨✨✨✨✨✨


የምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት ከዚጊቲ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ የጻድቁን በዓል አክብረው በመመለስ ላይ በመኪና አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የአንድ ሚሊዮን ብር  የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ ወሰነ !


መጋቢት 15 ቀን 2017 ዓ.ም [ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ/ ኢትዮጵያ]

ሀገረ ስብከቱ በመግለጫው መግቢያ "በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሥርዓት መሠረት  መጋቢት 5/2017 ዓ.ም  የጻድቁ አባታችን  አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዓመታዊ ክብረ በዓል በገሞጎፋ ዞን ሀገረ ስብከት ስር በሚገኘው  ዚጊቲ ደብረ ሰላም አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤ/ክ  ለማክበር ከሻሸመኔ እና ከአጎራባች ከተሞች ምእመናን  ከክብረ በዓሉን አክብረወው መጋቢት 6 ቀን 2017 ዓ/ም  በመመለስ ላይ እያሉ በወላይታ ዞን ልዩ ስሙ በዴሳ  በተባለ ቦታ ላይ  መንፈሳውያን ተሳላሚዎች  ይዞ ሲንቀሳቀስ የነበረው መኪና  የመገልበጥ  አደጋ ደርሶበት አሰቃቂ የሞት አደጋና  ከፍተኛ የአካል  ጉዳት መድረሱን ከሻሸመኔ ከተማ ከንቲባ ጽ/ቤት ከተሰጠው መግለጫ፤ ከጉዳቱ የተረፉ አካላት  ከተጎጂ ቤተሰብ ከሰጡት ማስረጃ ፤ እንዲሁም ከማኅበራዊ ሚዲያ  ማረጋገጥ ተችሏል፡፡" በማለት ሁነቱን ያስታወሰ ሲሆን በዚህም በደረሰው አደጋ የሰዎች ሕይወት መጥፋትና የአካል ጉዳት በደረሰባቸው ምዕመናን የተሰማውን ልባዊ ሐዘን ገልጧል፡፡

በሞት የተለዩ 13 ወገኖች ክብራቸውን በሚመጥን መንገድ እንደ ቤተክርስቲያን ሥርዓት ጸሎተ ፍትሐት ተደርጎ የቀብር ሥነ-ሥርዓታቸውን የሀገረ ስብከቱ የሥራ ኃላፊዎችና ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ የሟች ቤተሰቦችና ወዳጆች፣ የኃዘኑ ተካፋይ የሆኑ ሁሉ በተገኙበት በሻሸመኔ ከተማ ባሉ አራት አድባራት ላይ መፈጸሙን በማውሳት ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው 19 የሚሆኑ ታማሚዎች በወላይታ ሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታል  በፅኑ ሕሙማን ክፍል የሕክምና ድጋፍ  እየተደረገላቸው እንደሚገኙ መታወቁን አክሏል፡፡

ሀገረ ስብከቱ የአስተዳደር ጉባኤው አስቸኳይ ስብሰባ በመጥራት፤ የአድባራትና ገዳማት የአብያተ ክርስቲያናት አስተዳዳሪዎች፣ ምክትል ሊቃነ መናብርት፣  የሰ/ት ቤት እና የማኅበራት ተወካዮች  ልዩ ልዩ አካላት እንዲሁም ከተጎጂ ቤተሰብ  ጋራ ውይይት በማድረግ ተጎጂዎችን ለመርዳት ያስችል ዘንድ ሁሉን ያሳተፈ የጋራ ውሳኔንም አስተላልፏል፡፡

ከውሳኔዎቹም መካከል፡-

1ኛ. እንደ ቅድስት ቤተክርስቲያናችን ሥርዓት ላረፉት ዐሥራ ሦስት ወገኖች  የጋራ ጸሎተ ፍትሐት ለማድረግ ፣ በሕይወተ ሥጋ ያሉት ቅዱስ አምላክ እንዲምራቸቸው በጸሎት ማሰብ፣ 

2ኛ. ጠቅላላ የሀገረ ስብከት ሠራተኞች ሙሉ የአንድ ወር ደመወዛቸውን ጨምሮ ከሀገረስብከቱ የውስጥ ገቢ 1,000,000 (አንድ ሚሊየን ብር) ለተጎጂዎች ለመለገስ፣
3ኛ. የወረዳ ቤተክህነት ሠራተኞችን ሙሉ የአንድ ወር ሙሉ ደመወዝ

4ኛ. በሀገረ ስብከቱ ሥር የሚገኙ አድባራትና የገዳማት አብያተ ክርስቲያናት ጠቅላላ ሠራተኞች የአንድ ወር ደመወዛቸውን ለመለገስ፣

5ኛ. አድባራትና የገዳማት አብያተ ክርስቲያናት እንደ ተቋም ለመርዳት መወሰኑን በመግለጫው አሳውቋል፡፡

ከዚህም በተጨማሪ ሀገረ ስብከቱ ለከተማው ከንቲባ ጽ/ቤት ባቀረበው መሠረት የሻሸመኔ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት ከተጎጂዎች መካከል በኪራይ ቤት ያሉ  የመኖሪያ ቤት የሌላቸውን በመለየት የመኖሪያ ቤት ለመሥጠት ቃል የገባ ሲሆን ከዚህም ሌላ የከንቲባ አስተዳዱሩ ጽ/ቤት ሠራተኞችም በጉባኤ በመወሰን የገንዘብ ድጋፍ እንደሚያደርጉ የከተማው ከንቲባ አቶ አዳነ ተ/ጊዮርጊስ  ገልጸዋል፡፡

የሀገረ ስብከቱ አስተዳደር ጉባኤ አባላት፣ የሀገረ ስብከቱ  የየክፍል ኃላፊዎች፣ የአድባራት እና ገዳማት አስተዳዳሪዎች  ምክትል ሊቃነ መናብርትና የሰ/ት/ቤት ተወካዮች፣ የማህበረ ቅዱሳን አባላትና፣ በጎ አድራጊ ባለሃብቶች እንዲሁም ልዩ ልዩ አካላትን  በመሰብሰብ  ስለ ተፈጠረው ችግር በቀጣይ ምን መሥራት እንዳለብን እና በምን አይነት መንገድ የሟች ቤተሰቦችንና በፅኑ ሕሙማን ክፍል በሕክምና  የሚረዱ ወገኖቻችንን  መደገፍ እደሚገባ የሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዜና ማርቆስ የጉጅ ምዕራብ ጉጂ ቦረና ሊበንና የምዕራብ አርሲ አህጉረስብከት ሊቀ ጳጳስ የቅዱስ ሲኖዶስ አባል
መመሪያ መስጠታቸውንም ጨምረው በመግለጫው ላይ አስታውቀዋል፡፡

ከሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት፤ ከሻሸመኔ ከተማ አስተዳደር፣ ከአድባራትና ገዳማት አብያተ ክርስቲያናት፣ ከሰ/ት/ቤት ወጣቶች ፡ ከማኅበረ ቅዱሳን፣ በአካባቢው ከሚገኙ እድሮችና እቁቦች፣ ከሀገር ሽማግሌዎች፣ ከአባ ገዳዎች፣ እንዲሁም ሃዳ ሲንቄዎችን ያካተተ ኮሚቴ የተዋቀረ ሲሆን ይህም ኮሚቴ ለተጎጂዎች አስፈላጊውን እርዳታ ለማድረስ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት በመክፈት ገቢ የሚያሰባበስብ መሆኑን በስተመጨረሻ በመግለጫው ላይ አሳውቋል፡፡


ኦ ሚካኤል ኦ ሚካኤል ኦ መተንብል
ካህነ አርያም ትሰመይ ቢጸ ሱራፌል
ዘእምርኡሳን ረሑስ ወዘእምልዑላን ልዑል
ጊዜ ጸዋእኩከ ቅረበነ በምህረት ወሳህል።



📣ሚካኤል ይላል አንደበቴ 📣
ስለጸና በስሙ ጉልበቴ
ታሪክ ሰርቷል ያኔ በሕይወቴ✝️

አሜን አሜን በእዉነት ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል በተራዳዒነቱ  ከሁላችን አይለየን✝️⛪️
✨✨✨✨✨✨
✝️#ድምፀ_ተዋህዶ✝️
✨✨✨✨✨✨


"ትሑት ሰው ምንጊዜም ቢሆን የእርሱን ድካም ስለሚያውቅና የእግዚአብሔርን እርዳታ ስለሚሻ የእግዚአብሔር ኃይል በእርሱ ላይ ያድራል። በክንዱ ሳይመካ በእግዚአብሔር እርዳታ ስለተመካም ያሸንፋል።"

ብጹእ አቡነ ሺኖዳ

✨✨✨✨✨✨
✝️#ድምፀ_ተዋህዶ✝️
✨✨✨✨✨✨


Forward from: 🙏ኦርቶዶክሳዊ ዝማሬ🙏
Video is unavailable for watching
Show in Telegram
በጣም አስደንጋጭ መረጃ አስቸኳይ መረጃ ‼️


ይድረስ ለጠቅላይ ቤተ ክህነት ይድረስ ለማህበረ ቅዱሳ ይድረስ ለሰንበት ትምህርት ቤት ማዳረጃ እና መምሪያ።

እስከመቼ ዝምታ ነገሩ ከእቅበት እምነት ሳይሆን በቤተክርስቲያናችን በሀገረ እና በዘር ላይ ያነጣጠረ ጭፍን ጥላቻ ሲሰበክ በአደባባይ እንዴት ዝም ይባላል?

አሁንም እንደዚህ አይነት ዘርን እና ሃይማኖትን ያነጣጠረ ጠብ እና አመጽ ቀስቃሽ አደገኛ የሆነ መልእክት እየተላለፈ አሁን ሁሉም የሚመለከት አካላት ይድረስልን ይህ በማሕበረሰባችን ያለውን ትስስር አደጋ ላይ የሚጥል ጸያፍ እና አስደንጋጭ የሆነ መልእክት ልትቃወሙት ይገባል። በሃይማኖት ሰበብ የጥላቻን እና የህዝብን ሉዐላዊነት አደጋ ላይ የሚጋርጥ መልእክት የምታዮት ሰዎች በሙሉ ይህ የቤተ ክርስቲያን ጉዳይ በሀገራችነ‍እ ሉዓላዊነት ለዘመናት ተከባብረው ዜጎች የሚኖሩባት ሀገረን አደጋ ላይ የሚጥ አፀያፊ ጽንፈኛ አስተሳሰብነ‍እ ሁሉም የሃይማኖት አባቶች ሁሉም የእምነት ተቋማት እና የህግና የመንግስት አካላት ልታወግዙ እና ልታስቆሙ ይገባል ።

ስለዚህ ይህንን መልእክት የምታዩት ቢያንስ ለ20 ሰው ሼር በማረግ ለመንግስት እና የህግ አካላት ተጨማሪም ሀይማኖቶች ጉባኤ እንድታደርሱልን ስንል እንጠይቃለን !!!

እፎይ እና ጰልድዮስ እውነት አላቸው።
ትክለኛ የቴሌግራም ቻናላቸው ነው ተቀላቀል አንተ ባለማህተብ ክርስቲያን የሆንክ
👇👇👇👇
@Efoyewnetalew
@Efoyewnetalew

#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ


“እኔም እልሃለሁ፥ አንተ ጴጥሮስ ነህ፥ በዚችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ፥ የገሃነም ደጆችም አይችሉአትም።”
  ማቴዎስ 16፥18
ሐዋርያት 12
ÂŻÂŻÂŻÂŻÂŻÂŻÂŻÂŻÂŻÂŻ
¹⁶ ጴጥሮስ ግን ማንኳኳቱን አዘወተረ፤ ከፍተውም አዩትና ተገረሙ።
¹⁷ ግን ዝም እንዲሉ በእጁ ጠቅሶ ጌታ ከወኅኒ እንዴት እንዳወጣው ተረከላቸውና፦ ይህን ለያዕቆብና ለወንድሞች ንገሩ አላቸው። ወጥቶም ወደ ሌላ ስፍራ ሄደ።

#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ


Forward from: 🙏ኦርቶዶክሳዊ ዝማሬ🙏
ወንድማችን እፎይ የ63+ ሚሊዮን ኦርቶዶክሳዊያን አደራ ነው ይህ ይሰመርበት !!

ጌታ ኢየሱስ ይጠብቀው ጸልዩለት፣ ብዙኀናችን አብሮነታችንን እናሳየው !!


✝️ለባለ ማህተቦች✝️ሼር ያድርጉ↗️

✨✨✨✨✨✨✨
✝️#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ✝️
✨✨✨✨✨✨✨


💓የፍቅር ሳይኮሎጂ💓 የስሞን መጀመሪያ ፊደል ይምረጡ እና ይዝናኑ😂




ከ17 ደቂቃ ቦኃላ ይጠፋል


የ 200 ብር ካርድ የሚያስሸልም ጥያቄ!

በኢትዮጵያ በጣም አስቸጋሪ የነበረዉ  ረሀብ መች አመተምህረት ነበረ




5+5×5-5 = ?


የ1000 ብር ካርድ ሊለቀቅ ነው 9 ደቂቃ ብቻ ነው የቀራው። ቶሎ ከስር JOIN ሚለውን ነክታቹ JOIN REQUEST ላኩ 🏃‍♀️🏃‍♂️




በአዲስ አበባ አገልጋዮች ሞባይል ስልክ ይዘው ወደ ቤተ ክርስቲያን እንዳይገቡ ተከለከሉ‼️

በኢኦተቤ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አገልጋዮች በቅዳሴና ለሌሎች መንፈሳዊ አገልግሎት ሰዓት ሞባይል ስልክ ይዘው ወደ ቤተ ክርስቲያን እንዳይገቡ መከልከሉን አስታውቋል።

ሀገረ ስብከቱ ለሁሉም ገዳማትና አድባራት በላከው የመመሪያ ደብዳቤ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በሚከናወኑ  የጸሎተ ቅዳሴና ሌሎች መንፈሳዊ አገልግሎቶች የእጅ ሞባይል ስልክ ይዞ መግባት በጥብቅ መከልከሉን ይገልጻል።

የገዳማትና አድባራት አስደዳሪዎችና ሰበካ ጉባኤያት ጥብቅ ክትትል በማድረግ መመሪያውን እንዲያስፈጽሙ ታዘዋል።

መረጃው ከሀገረ ስብከቱ ሚዲያ ክፍል የተገኘ ነው።

✨✨✨✨✨✨
✝️#ድምፀ_ተዋህዶ✝️
✨✨✨✨✨✨


🗓ትጾማለህን?
በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

☦️ትጾማለህን❓ እንግዲያውስ በሥራህ አረጋግጥልኝ!
በምን ዓይነት ሥራ ካልከኝ?
☦️ደሃውን ካየህ እዘንለት (ቸርነትን አድርግለት)!
☦️የተጣላኸውን ካየህ ታረቀው!
☦️ጓደኛህ ክብርን ሲያገኝ ካየህ አትቅናበት!
☦️መልከኛ ሴት ካየህ እለፋት!
☦️አፍህ ብቻ ከምግብ አይከልከል፤ አይንህም፣ ጆሮህም፣ እግርህም፣ እጆችህም፣ ሁሉም  የሰውነትህ ክፍሎች ይጹሙ።

እጆችህ ከንጥቂያና ስግብግብነት (ንፉግነት) ይጹሙ። እግሮችህ የማይገቡ ትእይንቶችን ለመመልከት ከመንደርደር ይጹሙ። አይኖችህ ውብ መልኮች ላይ ያልተገቡ እይታዎችን መቼም መች ከማሳረፍ መከልከልን ይማሩ እና ቁንጅና ላይ ከመጠመድ ይጹሙ።

ማየት ለዐይን ምግብ ስለሆነ ያልተገባ እና የተከለከለን እይታ ካደረግህ ጾምህን ያፈርሰዋል፣ የነፍስህንም ሙሉ ደህንነት ያነዋውጣል፤ ነገር ግን የተገባና ጥንቁቅ ከሆነ ጾምህን ያስጌጣታል።

የተከለከለውን በዓይን እየነካህ ነገር ግን በጾም ምክንያት ከማያረክስ ምግብ መጾሙ ከንቱ ከሆኑ ነገሮች መካከል ይቆጠራል። ሥጋን አትበላም አይደል? ስለዚህ በዐይኖችህ አማካኝነት ፍትወትን አትመገብ። ጆሮም ይጹም።

የጆሮ ጾም ክፉ ወሬን እና ሐሜትን አለመቀበልን ያካትታል። “ሐሰተኛ ወሬ አትቀበል” እንዲል። (ዘጸ. 23፥1)   አፍም እንዲሁ ከመጥፎ እና ከጥላቻ ንግግሮች ይጹም።  ከአዕዋፋትና አሳዎች ብንከለከል ነገር ግን ወንድማችንን ብንበላው ምን ይጠቅመናል? ክፉ ተናጋሪ የወንድሙን ሥጋ ይበላል የባልንጀራውንም ሰውነት ይነክሳልና።


✨✨✨✨✨✨
✝️#ድምፀ_ተዋህዶ✝️
✨✨✨✨✨✨


Forward from: 🙏ኦርቶዶክሳዊ ዝማሬ🙏
🗓☦️​​ዘወረደ

የመጀመሪያ የዐቢይ ጾም መግቢያ እሁድ ዘወረደ ይባላል ደግሞም ጾመ ሕርቃል ይባላል፡፡ «ዘወረደ» ማለት «የወረደ» ማለት ነው፡፡ አምላክ ሰው ሆነ፤ ሰው አምላክ ሆነ ማለት ነው። ይህም ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ለማዳንና ፍቅሩን ሊገልጽልን ከሰማያት መውረዱን ከድንግል ማርያም የእኛን ሥጋ መዋሐዱን የሚያዘክር፤ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ከቅድስት ድንግል ማርያም መወለዱን የሚያመላክት፣ የሚታወስበት፣ የሚነገርበት የዐቢይ ጾም አንደኛው ሳምንት ነው፡፡ ዮሐ.3-13
ďťż
እግዚአብሔር አምላክ ለአዳም በገባዉ ቃልኪዳን መሰረት “ የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ልጁን ላከ”ገላ 4፥4 እንዳለ ሐዋርያዉ ቅዱስ ጳዉሎስ ፡ የጠፋዉን አዳም ፍለጋ ከአባቱ እሪና ሳይጎድል ሳይለይ ከሰማይ መዉረዱን የምናዘክርበት በዓል ነዉ።

ይህ ጾም የጾም መግቢያ የመጀመሪያ ሳምንት የምንጾመው ጾም ሲሆን ሕርቃል የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ለአዳም “ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ በመልዕልተ መስቀል ተሰቅየ አድንኃለሁ” ብሎ ለአዳም ቃል ገባለት ፡፡ ዘፍ. ፫ ፥ ፲፭ ይህ ኪዳነ አዳም ይባላል የቃል ኪዳን ሁሉ መሠረት ነው፡፡


ሁለቱን ኪዳናት (ብሉይ ወሐዲስ) በፅኑዕ ተስፋ ያስተሳሰረ የረጅም ዘመናት የድኅነት ሰንሰለት ነው ፡፡ ዘወረደ እርቀ አዳም ፤ ተስፋ አበው ፤ ትንቢተ ነቢያት ፤ ሱባኤ ካህናት መፈፀሙ ፤ ኪዳነ አዳም መሲህ መወለዱ የሚነገርበት የፍቅር አዋጅ ነው። እኛም በዚህ በዐብይ ፆም የለመነውና የጠየቅነው ነገር ሁሉ ከኃጢአት በስተቀር እንዲከናወንልን ፆምን ገንዘባችን እናድርግ።

ጾም ጸሎታችን የቅዱሳን አምላክ እግዚአብሔር ይቀበልልን አሜን፡

✝️ለባለ ማህተቦች✝️ሼር ያድርጉ↗️

✨✨✨✨✨✨✨
✝️#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ✝️
✝️#ድምፀ_ተዋህዶ ✝️
✨✨✨✨✨✨✨

20 last posts shown.

152 856

subscribers
Channel statistics
Popular in the channel

"ትሑት ሰው ምንጊዜም ቢሆን የእርሱን ድካም ስለሚያውቅና የእግዚአብሔርን እርዳታ ስለሚሻ የእግዚአብሔር ኃይል በእርሱ ላይ ያድራል። በክንዱ ሳይመካ በእግዚ...
“እኔም እልሃለሁ፥ አንተ ጴጥሮስ ነህ፥ በዚችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ፥ የገሃነም ደጆችም አይችሉአትም።”   ማቴዎስ 16፥18 ሐዋርያት 12...
በጣም አስደንጋጭ መረጃ አስቸኳይ መረጃ ‼️ ይድረስ ለጠቅላይ ቤተ ክህነት ይድረስ ለማህበረ ቅዱሳ ይድረስ ለሰንበት ትምህርት ቤት ማዳረጃ እና መምሪያ።...
ወንድማችን እፎይ የ63+ ሚሊዮን ኦርቶዶክሳዊያን አደራ ነው ይህ ይሰመርበት !! ጌታ ኢየሱስ ይጠብቀው ጸልዩለት፣ ብዙኀናችን አብሮነታችንን እናሳየው !!...
ኦ ሚካኤል ኦ ሚካኤል ኦ መተንብል ካህነ አርያም ትሰመይ ቢጸ ሱራፌል ዘእምርኡሳን ረሑስ ወዘእምልዑላን ልዑል ጊዜ ጸዋእኩከ ቅረበነ በምህረት ወሳህል። ...