ኤፍሬም ስዩም
ሰሞነኛ ፡ ሃሣብ
፫
ከ ፡ አንድ በሬው ጋር
የራሱን፡ ትከሻ ፡ አጣምዶ፡ ለሚኖር
ወይም ፡ ለሚቆፍር ፡ ? ፡
የ ፡ አንድ-ገበሬ ፡
አንደኛ ፡ ጥያቄው ፡
ብቸኛም ፡ ጥያቄው ፡
በትከሻው ፡ ፈንታ
ተጣምዶ ሚያርስለት ፡ ''አንድ በሬ ፡ ነበር''።
ምትክ የሌለውን
ብቸኛውን ፡ ልጁን
ደብተሩን ፡ አስቀምጦ ፡ ውጊያ ፡ በማሣደር
ደረቱን ፡ ለቀለህ ፡ ጠጠር ፡ በማስገበር
የትም ፡ ወድቆ ፡ ባይቀር ፡ ? ፡
በአሞራዎች ፡ አንጀት ፡ ወድቆ ፡ ባይቀበር። ?።
ለአንድ ፡ ገበሬ ፡ ብቸኛ ፡ ጥያቄው
አልነበረም ፡ ሥልጣን ፡ በደም ፡ የሚከብር።
አልነበረም ፡ ዙፋን ፡ ሚፀና ፡ ባሻጥር።
አልነበረም ገንዘብ ፡ ናላን ፡ የሚያሰክር።
ግን
አንድ ፡ በሬ ፡ ብቻ፣አንድ ፡ በሬ ፡ ነበር
አንጀትን ፡ በማሰር
የምድርን ፡ በረከት ፡ ቆፍሮ ፡ ለማደር።
ሚበቃውን ፡ ያህል
በመዝራት ፡ ለማፈስ ልጁን ለማስተማር።
ኤፍሬም ሥዩም
16 02 2015 ዓመተ ፍዳ
(በኢትዮጵያውያን ፡ ዘመን ፡ አቆጣጠር)
https://www.facebook.com/ephraimsoliana
@ethio_poem
🟢🟡🔴🟢🟡🔴🟢🟡🔴
ሰሞነኛ ፡ ሃሣብ
፫
ከ ፡ አንድ በሬው ጋር
የራሱን፡ ትከሻ ፡ አጣምዶ፡ ለሚኖር
ወይም ፡ ለሚቆፍር ፡ ? ፡
የ ፡ አንድ-ገበሬ ፡
አንደኛ ፡ ጥያቄው ፡
ብቸኛም ፡ ጥያቄው ፡
በትከሻው ፡ ፈንታ
ተጣምዶ ሚያርስለት ፡ ''አንድ በሬ ፡ ነበር''።
ምትክ የሌለውን
ብቸኛውን ፡ ልጁን
ደብተሩን ፡ አስቀምጦ ፡ ውጊያ ፡ በማሣደር
ደረቱን ፡ ለቀለህ ፡ ጠጠር ፡ በማስገበር
የትም ፡ ወድቆ ፡ ባይቀር ፡ ? ፡
በአሞራዎች ፡ አንጀት ፡ ወድቆ ፡ ባይቀበር። ?።
ለአንድ ፡ ገበሬ ፡ ብቸኛ ፡ ጥያቄው
አልነበረም ፡ ሥልጣን ፡ በደም ፡ የሚከብር።
አልነበረም ፡ ዙፋን ፡ ሚፀና ፡ ባሻጥር።
አልነበረም ገንዘብ ፡ ናላን ፡ የሚያሰክር።
ግን
አንድ ፡ በሬ ፡ ብቻ፣አንድ ፡ በሬ ፡ ነበር
አንጀትን ፡ በማሰር
የምድርን ፡ በረከት ፡ ቆፍሮ ፡ ለማደር።
ሚበቃውን ፡ ያህል
በመዝራት ፡ ለማፈስ ልጁን ለማስተማር።
ኤፍሬም ሥዩም
16 02 2015 ዓመተ ፍዳ
(በኢትዮጵያውያን ፡ ዘመን ፡ አቆጣጠር)
https://www.facebook.com/ephraimsoliana
@ethio_poem
🟢🟡🔴🟢🟡🔴🟢🟡🔴