ኢስላማዊ እውነታ


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


ኢስላማዊ እውነታዎችን የምንገልፅበትና የምናብራራበት ቻላል!

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
ፀሀይ ላይ ምራቅ መትፋት ይቻላል?

https://t.me/islamictrueth


Forward from: የሕያ ኢብኑ ኑህ - Yahya Ibnu Nuhe
ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል ከብሮድካስት ባለስልጣን ፍቃድ አውጥቶ የሚሰራ ህጋዊ ሚዲያ ነው። ይህ ሚዲያ ከተራ ዩቲዩበር እንኳን የማይጠበቅ የበሬ ወለደ ትርክት ዩቲዩቡ ላይ ለጥፏል። ከሰሞኑ በነበሩ ጉዳዮች ቤተ ክርስቲያን ላይ ፍለጠው ቁረጠው ያለ ግለሰብም የለም። የብሮድካስት ባለስልጣን በዚህ አይነት ግጭት ቀስቃሽ ተግባር ላይ እርምጃ እንደሚወስድ እጠብቃለሁ። ዋናው ጉዳይ ግን ነውረኛ ተግባር የፈጸመውን ልጅ ለመከላከል የሚሄዱበት ርቀት ምክንያቱ ምንድን ነው? የሚለው ነው። የተወሰነውን ልንገራችሁ፦

ሚዲያውን ከመመስረት ጀምሮ በበላይ ጠባቂነት እየመሩ የሚገኙት ከሲኖዶሱ ሊቀጳጳሳት መካከል የሆኑት አቡነ ሄኖክ ናቸው። አቡነ ሄኖክ ደግሞ የምዕራብ አርሲ ሀገር ስብከት ሊቀጳጳስ የነበሩ ሰው ናቸው። ታዲያ ይህ ነውረኛ ግለሰብ (እፎይ) ከየት መጣ ብለው ከጠየቁ ደግሞ መልሱ "ከአርሲ" የሚል ነው። ነውሩን ለመከላከል በሚያደርጉት ግብታዊ ጥረት ሳቢያ ብልግናውን መዋቅራዊ እያደረጉት ነው፥ ያሳዝናል።

⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻
https://t.me/Yahyanuhe


እፎይ የቤተክህነት ድጋፍ አለዉ ስንል የነበረዉን መረጃ ዛሬ በይፋ እነሱም አረጋግጠዋል!

ግለሰቡ በግልፅ ስድብና ስርአት በሌለዉ መልኩ ነብዩ ሙሀመድ(ﷺ) መሳደቡን ህዝበ ሙስሊሙን ባስቆጣበት ሰአት ቤተክህነት ጉዳዩን ካማዉገዝ ይልቅ ባንዳንድ ቄሶችና ለማህበሩ ከሚሰሩ ሰዎች የሱን ጉዳይ እንዲደግፉ ሲያደርግ ቆይቷል። በዛሬዉ እለት ደግሞ የሀይማኖት ተቋም መግለጫ በሚሰጥበት ወቅት ለማህበሩ ሚዲያ ጥሪ ቢደረግለትም በቦታዉ አልተገኘም። አንድም የነሱ አካል በመግለጫው ላይ አስተያዬትም ግሳፄም አልሰጡም። መግለጫዉ ተሰጥቶ በሰአታት ዉስጥ ከ16 አመት እና ከዛ በላይ ታትመዉ ገበያ ላይ በወጡ የንፅፅር መፀሀፍን «የፍለጠዉ ግ*ደ*ለ*ዉ ዘመቻ በቤተክርስቲያን ላይ» የዉንጀላ ቪዲዩ ለቀዋል።

እነዚህ ሰዎች እዉነት መፀሀፎቹ ስድብና የፍለጠዉ መሰል ነገሮች ቢሆኑ እስከዛሬ የት ነበሩ? ታትመዉ ገበያ ላይ ሲሸጡ ያዉም በኢኃዲግ ጊዜ ለምን አልታገዱም? አላማቸዉ ግልፅና ግልፅ ነዉ። በየቀኑ ወደ እስልምና የሚመጣዉን ህዝብ ለመግታት ስድብና ማንጓጠጥን አንድ የስልት ዘዴ አድርገዉ ለመያዝ ነዉ። ለዚህም ይረዳቸዉ ዘንድ እራሱ መስዋትነት አድርጓ የመጣን ግለሰብ ጋር ከጓን መሆንን መርጠዋል።

አሁንም ጉዳዩን መንግስት እልባት ካልሰጠዉ ወደ ለየለት ጦርነት የሚከት ክስተት ይፈጠራል።


ለካ «የናንተም አስተማሪዎች ይሳደባሉ!» የሚሉንን ይህንን ነው?

ባይብልም ነብይ ነው ይላል'ኮ ወገን!

እንዲህ አይነት ትግል ነው የገጠመን ወገን!



"ነቢይ ነው!" ካላልንና "ፈጣሪ ነው!" ካልን'ማ ያው የናንተ እምነት ተከታይ ሆን ማለት ነው'ኮ። ኧረ! እያስተዋልን ወገን!

ለማንኛውም ኢየሱስን ነቢይ ማለት አንዱ የእምነታችን አካል ሲሆን ነቢይ መሆኑን ደግሞ ከምታምኑበት ከባይብል የተወሰኑ ጥቅሶችን ላጋራችሁ።

ኢየሱስ ነቢይ እንደነበር ⚡️⚡️ መፅሀፍ ቅዱሳዊ ማስረጃዎችን ብንመለከት‼
====================================

1•"ኢየሱስም ነቢይ ከገዛ ኣገሩና ከገዛ ዘመዶቹ ከገዛ ቤቱም በቀር ሳይከበር ኣይቀርም ኣላቸው"
(ማርቆስ 6:4)

2• "ኢየሱስ ግን ነቢይ ከገዛ ኣገሩና ከገዛ ቤቱ በቀር ሳይከበር ኣይቀርም ኣላቸው"( ማቴዎስ 13:57)

3• "ሕዝቡ እንደ ነቢይ ስላዩት"( ማቴዎስ 14:5)

4• "ሕዝቡም ይህ ከገሊላ ናዝሬት የመጣ ነቢዩ ኢዩሱስ ነው ኣሉ"( ማቴዎስ 21:11)

5• "ሊይዙትም ሲፈልጉት ሳሉ ሕዝቡ እንደ ነቢይ ስላዩት ፈሩአቸው"( ማቴዎስ 21:46)

6• "ታላቅ ነቢይ በኛ መካከል ተነሦቶኣል"( ሉቃስ 7:16)

7• "በእግዚኣብሄርና በሕዝቡ ሁሉ ፊት በስራና በቃል ብርቱ ነቢይ ስለ ነበረው ስለ ናዝሬቱ ስለ ኢየየሱስ" ( ሉቃስ 24:19)

8• "ከዚህ የተነሳ ሰዎቹ ኢየሱስ ያደረገውን ምልክት ባዩ ጊዜ ይህ በእውነት ወደ ኣለም የሚመጣው ነቢይ ነው ኣሉ"( የዬሐንስ ወንጌል 6:14)

9• "ሴቲቱ ጌታ ሆይ ኣንተ ነቢይ እንደ ሆንህ ኣያለሁ"(የዬሐንስ ወንጌል 4:19)

10• "በመካከላቸው መለያየት ሆነ ከዚህም የተነሳ ዕውሩን ኣንተ ዓይኖችህን ስለ ከፈተ ስለ እርሱ ምን ትላለህ? ደግሞ ኣሉት እርሱም ነቢይ ነው ኣለ" ( የዬሐንስ ወንጌል 9:17)

11• "ስለዚህ ከሕዝቡ አያሌ ሰዎች ይህን ቃል ሲሰሙ፦ ይህ በእውነት ነቢዩ ነው አሉ፤"(የዮሀንስ ወንጌል 7:40)




Video is unavailable for watching
Show in Telegram
ኢስላም እንደተጠቃዉ ሌሎቹ ቢጠቁ ኖሮ...

https://t.me/islamictrueth


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
እፎይ አቡ ሀይደርን ለመክሰስ እየተሯራጠ ነዉ!

የአቡ ሀይደር ትምህርቶችን በዉስጥ ላኩልኝ ብሎ እየተማፀነ ነዉ። የሱን ስድብ ህጋዊ ለማድረግ የንፅፅር ትምህርቶችን ወደ ክስ ካመሩ ቀዳሚ የሚታሰሩትና የሚቀፈደዱት ሁሉም የሲኖዶስና የማህበረ ቁዱሳን አባላት በሙሉ እንደሆነ ልታዉቁ ይገባል። ይህንን የምናገረዉ በመፀሀፋቸዉ ላይ በጣም ብዙ ጉዶች ስላሳተሙ ነዉ። መረጃዉ በእጃችን ነዉ።


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
ከቢሊየን በላይ ሙስሊሞች ኑብዩ ሙሀመድ(ﷺ) ትወዳቹሀላቹ እሳቸዉ ግን እናንተ እንደሚወዱ በምን ገለፁ?

እኛ በስርአት ለሚጠይቀን ሰዉ ችግር የለብንም። መጠያየቅን አንጠላም ችግሩ መሰዳደቡ ነዉ። ለማንኛዉም የጥያቄዉን መልስ ከቪዲዩ ታገኛላቹ።

https://t.me/islamictrueth


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
አላህ(ሱ.ወ) በቅዱስ ቁርአን ዉስጥ ነብዩ(ﷺ) ምን ብሎ ነዉ ያወደሳቸዉ?

https://t.me/islamictrueth


ልባቸው በጥ*ላ*ቻ ለታወረ ወገኖች የምንላቸው ነገር ቢኖር፡- ለነቢዩ ሙሐመድ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንኳን ወላጆቻችን ዓለሙ ሁሉ ቤዛ ሆኖ ቢቀርብ አላህ ዘንድ ካላቸው ደረጃ አንድ እጁንም አይሞላም፡፡ ምክንያቱም ይህቺ ምድር ውበቷ እሷንና በላይዋ ላይ ያሉትን የፈጠረውን አንድ አምላክ ስናመልክባት ነው፡፡ ይህ ትምሕርት ደግሞ እሳቸው ነቢይ ሆነው ባይላኩ ኖሮ መች ይገኝ ነበር?፡፡ እኛም በክህደት ጨለማ ተውጠን በአምላክ ፈንታ ሰውን አምልከን የክህደት ጉድጓድ ውስጥ በወደቅን ነበር፡፡ ዓለሙም በጨለመ ነበር፡፡ አልሐምዱ ሊላህ እሳቸውን ነቢይ አድርጎ ለላከልን አላህ፡፡

"ከኢስላም ሌላ ሃይማኖትን የሚፈልግ ሰዉ፣ ፈጽሞ ከርሱ ተቀባይ የለዉም፤ እርሱም በመጨረሻይቱ ዓለም ከከሳሪዎች ነዉ።" (ሱረቱ አሊ-ዒምራን 85)፡፡

ከኡስታዝ አቡ ሀይደር ከበፊት ፁሁፉ የተወሰደ!

https://t.me/islamictrueth


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
እንከባበር!


ረመዳን ከመሆኑ ጋር ብታዳምጡት የበለጠ አጅር የምታገኙበት። አቀራሩም ስለሚያምር የምትረኩበት ስለሆነ ለማበረታትና ለቀጣይ ስራዎች ይመጣ ዘንድ ከምንጩ ከራሱ ከዩትዩብ ቻናሉ እናዳምጥ!!!




Video is unavailable for watching
Show in Telegram
ከመግሪብ ሶላት በኋላ የሚፈፀሙ ተደጋጋሚ ሁለት ስህተቶች 2 ደቂቃ ብቻ

https://t.me/islamictrueth


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
ያለ ሶላት ፆም፣ ሀጅ፣ ዘካና ሌላ መልካም ስራዎች ዋጋ የላቸዉም። በእለተ ቂያማ ከተዉሂድ በኃላ የሰዉ ልጅ የሚጠየቀዉ በሶላቱ ነዉ። ሶላቱ ካማራ መልካም ሆነለት።

https://t.me/islamictrueth


🌙 ረመዳን ሙባረክ🌙

የረመዳን ወር መግቢያ ጨረቃ በመታየቷ ነገ ቅዳሜ የረመዳን የመጀመሪያው ቀን ይሆናል።

ፆሙ የሰላም፣ የአፊያ፣ የኢባዳ ያድርግልን!

https://t.me/islamictrueth


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
አዛኑ እስከሚጨርስ ድረስ የሚጠጡ ፆም መያዧዉ የአዛኑ መጨረሻ ብለዉ በማሰብ(በመጠርጠር) ለሚሉ የተሰጠ መልስ!

በሼይኸ ሱሌይማን አሩሀይሊ

ይሄ ስህተት ነዉ ከፊል አላዋቂዎች አሶላቱ ኸይሩ ሚነ ነዉም እስከሚል ድረስ የሚጠጡ የሚበሉ አሉ ከፊሎቹ ደግሞ አዛን ብሎ እስኪጨርስ ድረስ ይሄ ስህተት ነዉ። ነብያችን ሶለሏሁ አለይሂ ወሰለም ብሉ ጠጡ ኢብን ኡሚ መክቱም አዛን እስከሚያደርግ ድረስ ብለዋል።

አዛን ወሰን አድርገዋል

አዛን ከበፊቱ አይነት አይደለም። ግዴታዉ አዛን ሲል ቶሎ መያዝ ማቆም ነዉ። አዛን እያለ
ሶስት ሁኔታዎች መብላት መጠጣት ይቻላል።

1ኛ) አዛን እያለ ዉሀ መጠጣት ፈልገህ እቃዉን አንስተሃል አዛን አድራጊዉ አሏህ አክበር አለ ጠጣ ጉዳይን እስክትሞላ ድረስ።

2ኛ) አዛን አድራጊዉ አዛን ካለ አፍህ ዉስጥ የጓረስከዉ ካለ ማዉጣት ግዴታ አይሆንብህም ዋጠዉ ፆምህ ትክክል ነዉ አልሀምዱሊላህ።

3ኛ) መድሀኒት አንስተህ አዛን አድራጊዉ አዛን ካለ መድኃኒት መውሰዱ ግድ ከኾነ ዉሰድ። መድሀኒት መዉሰድ እረስተህ አዛን ሲቃረብ ወደ ፍሪጅ ሄድክ ከፍሪጁ ወድሀኒቱን አወጣህ መድሀኒት መዉሰድ ፈለክ ከዚያ ቡሃላ ዉሀ መጠጣት ፈለክ ከዚያ ቡሃላ አዛን ሊል መድሀኒቱን ዉሰድ ዉሀ ጠጣ ፆምህ ትክክል ይሆናል ከዚህ ዉጭ ያለ አይፈቀድም።

Copy

https://t.me/islamictrueth


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
አላህ ለፆመኞች የሚሰጠዉ ምንዳ እኔ ነኝ የምከፍለዉ ነዉ ያለዉ። ማለትም ቁጥሩንም ምን እንደሆነም አልተናገረም!

#ረመዳን
#Remedan

https://t.me/islamictrueth


ጫት ለመተው ላሰበ ሰው እንደ ረመዳን አጋዥ አያገኝም። ረመዳንን መጠቀም ብልሀት ነው። ከተራዊህ መልስ ደሞ ሱስ እንዳይረብሸው መተኛት ይችላል።

ብዙ ሰዎች ጋር የሚተገበር የጾምን አላማ የሳተ አጿጻጿም👉 ለሊት እየቃሙ ቀን መተኛት ነው። ይህ ወሩን የ ኢባዳ ሳይሆን የመቃሚያ ወር ያስመስለዋል። ምንም ሳናሽሞነሙነው ጫት ለሰው ልጅ ጎጂ ነው። ጎጂ ሆኖ ደግሞ ሀላል የለም። የሱሰኞች ሁሉ ራስን ማታለያ ቃላቶች "መተው እችላለሁ" "ባልቅም ግዴለኝም" "ሁለት እንጨት ለጨዋታ/ለሙድ ብቻ ነው" የሚሉት ናቸው። ይህ ማለት denial የሱሰኝነት ምልክት ነው። እያንዳንዱ ሰው ለጫት ባወጣው ገንዘብ አላህ ይጠይቀዋል። ምንም ሸክ የለውም። የጫት ሱስ አደገኝነቱ ከህጻን እስከአዋቂ፣ የተማረ ያልተማረ፣ ከኸለፍ እስከ ሰለፍ፣ ሴት ወንድ ሁሉንም ማጥቃቱ ነው።

ባንድ ወቅት በረመዳን ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ላስተምር ሄጄ አንድ ወንድም ላፈጠርህ ብሎ ያዘኝ። ብዙም ስለማላውቀው ሳቅማማ የሱ ጓደኛ የሆነ ሷሂቤን ነግሮት ካላመጣሀው ብሎት ይዞኝ ሄደ። ለፊጥራ ስገባ ግን የተዘጋጀውን ምግብ አይቼ ድግስ መስሎኝ ነበር። ሆኖም ለኛው ነበር። አፍጥረን ስንጨርስ ልጁ "አንተኮ ባለውለታየ ነህ" አለኝ። እኔም ገርሞኝ "እንዴት የትስ ተገናኝተን" አልኩት። እሱም ባንድ ወቅት ጅማ ዩኒቨርስቲ ልጆችን ስትመክር "ሰባት ሰአት ላይ ቆጪ ጫት ተራ ልትገዙ እየሄዳችሁ ነቢ (ሰአወ) በህይወት ኑሮ መንገድ ላይ አግኝተው ስምህን ጠርተው "የት እየሄድክ ነው ? ቢሉህ ምን ብለህ ትመልሳለህ? ስትል ደነገጥኩ። ከዛ በፊት በጫት ህይወቴ ምስቅልቅል ያለ ነበር። ከዛ ንግግር በኋላ ጫትን ተውኩ ተውኩ። ዱንያ ሁሉ አማረችልኝ አለኝ።

እና እስቲ በዚህ ረመዳን ይህንን የአለም ጤና ድርጅትም ሆነ FDA "ከ ሀሽሾች አንዱ" ያሉትን ቅጠል፣ ሙስሊሙን አለም የቲም ብኩን አድርጎ ያስቀረ የተረገመ ቅጠል፣ የሰውን ግብ ዝቅ ያደረገ፣ ቤተሰብን የበተነ፣ ጤናን ያቃወሰ፣ ወጣቱን ከንቱ አድርጎ ያስቀረ ነጃሳን ለመተው ነይቱ።

አላህ ይርዳችሁ።

Kha Abate



20 last posts shown.