እንኳን አደረሳችሁ።
በጉጉት የሚጠበቀው ታላቁ ጾም መጥቷል። ይህ ጾም እንደ ስሙ ዐቢይ (ታላቅ) ነው። በኦርትዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን 7 የአዋጅ አጽዋማት ቢኖሩም፣ የሰባቱ ራስ ግን ይህ ጾም ነው። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቆመ ሳይቀመጥ የጾመው ቀን ነውና ጾመ ኢየሱስም ይባላል። የሚጾሙት ዕለታትም ከሌሎቹ አጽዋማት ይልቃሉ።
ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ታላቁን ጾም በሳምንታት ከፋፍሎ ስያሜ የሰጠው ሲሆን፣ የመጀመሪያው ሳምንት ዘወረደ ይባላል። ዘወረደ ማለት የወረደ ማለት ነው። በዚህ ሳምንት የክርስቶስ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ከድንግል ማርያም ተወልዶ ሰው መሆኑ ይነገርበታል።
ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ጾመ ድጓ በተባለው ድርሰቱ "ዘወረደ እምላእሉ አይሑድ ሰቀሉ ወሚመ ኢያእመሩ እግዚአ ኩሉ ዘየሐዩ በቃሉ፤ ከሰማየ ሰማያት የወረደውን አይሑድ ሰቀሉት፤ በቃሉ ብቻ ዓለምን የሚያድን የሁሉ ጌታ መሆኑን ፈጽሞ አላወቁምና" በማለት ይጀምረዋል። እነሆ ዘወረደ ተጀምሯል።
©
በጉጉት የሚጠበቀው ታላቁ ጾም መጥቷል። ይህ ጾም እንደ ስሙ ዐቢይ (ታላቅ) ነው። በኦርትዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን 7 የአዋጅ አጽዋማት ቢኖሩም፣ የሰባቱ ራስ ግን ይህ ጾም ነው። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቆመ ሳይቀመጥ የጾመው ቀን ነውና ጾመ ኢየሱስም ይባላል። የሚጾሙት ዕለታትም ከሌሎቹ አጽዋማት ይልቃሉ።
ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ታላቁን ጾም በሳምንታት ከፋፍሎ ስያሜ የሰጠው ሲሆን፣ የመጀመሪያው ሳምንት ዘወረደ ይባላል። ዘወረደ ማለት የወረደ ማለት ነው። በዚህ ሳምንት የክርስቶስ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ከድንግል ማርያም ተወልዶ ሰው መሆኑ ይነገርበታል።
ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ጾመ ድጓ በተባለው ድርሰቱ "ዘወረደ እምላእሉ አይሑድ ሰቀሉ ወሚመ ኢያእመሩ እግዚአ ኩሉ ዘየሐዩ በቃሉ፤ ከሰማየ ሰማያት የወረደውን አይሑድ ሰቀሉት፤ በቃሉ ብቻ ዓለምን የሚያድን የሁሉ ጌታ መሆኑን ፈጽሞ አላወቁምና" በማለት ይጀምረዋል። እነሆ ዘወረደ ተጀምሯል።
©