ሦስተኛ፥ ጳውሎስ እነዚህ የጸጋ ስጦታዎች እንደ ክርስቶስ ስጦታ መጠን እንደ ተሰጡን ያስረዳል። መንፈሳዊ ስጦታዎች ከእግዚአብሔር የሚመነጩ እንጂ የተፈጥሮ ችሎታዎች ወይም የቅጥር ሥራዎች አይደሉም። ነገር ግን ምንጫቸው ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው። እግዚአብሔር በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ልዩ ስጦታና ድርሻ በመስጠት ስጦታችንን አውቀን እንድናገለግለው ይፈልጋል።
ጳውሎስ ሁሉም ክርስቲያኖች መንፈሳዊ ስጦታዎችን እንደ ተቀበሉ ቢናገርም፥ በኤፌሶን መልእክቱ የመሪነት ስጦታዎችን በተመለከተ ብቻ በብዛት ጽፎአል። (ለምእመናን የተሰጡትን ሌሎች መንፈሳዊ ስጦታዎች ዝርዝር ከ1ኛ ቆሮንቶስ 12፡28-30 አንብብ።) ጳውሎስ ለቤተ ክርስቲያን የተሰጡትን አምስት ዐበይት የአመራር ስጦታዎች ገልጾአል። የአመራር ስጦታዎች ሰዎች በምርጫ ጊዜ የሚወስኗቸው አይደሉም። ነገር ግን እነዚህ ስጦታዎች እግዚአብሔር የሚሰጣቸውና እኛም ለይተን ለቤተ ክርስቲያን የምንጠቀምባቸው ናቸው። እግዚአብሔር የመሪነት ስጦታ የሰጣቸውን ሰዎች ለዚሁ አገልግሎት መምረጥ አለብን። ነገር ግን ስጦታ የሌለውን ሰው ልንመርጥና ከዚያ በኋላ እግዚአብሔር ስጦታውን ይሰጠዋል ብለን ልንጠብቅ አይገባም። በመጀመሪያ፥ ሐዋርያት ተጠቅሰዋል። እዚህ ላይ ጳውሎስ ክርስቶስ ስለ ሾማቸው በኢየሱስ ስለተመረጡት 12ቱና ስለ ራሱ እያሰበ መሆኑ አይጠረጠርም። ነገር ግን እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን ለመመሥረት ስለተጠቀመባቸው አገልጋዮችም እያሰበ ሊሆን ይችላል። ሁለተኛ፥ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለክርስቶስ አካል የማስተላለፍ ኃላፊነት የተሰጣቸው ነቢያት አሉ። ይህ የመሪነት ተግባር አዲስ ኪዳን ከመጻፉ በፊት ለቀድሞይቱ ቤተ ክርስቲያን የተለየ ጠቀሜታ ነበረው። ሦስተኛ፥ ወንጌሉን ለዓለማውያን የማካፈል ስጦታ የተሰጣቸው ወንጌላውያን ነበሩ። አራተኛ፥ የአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናትን ምእመናን መንፈሳዊ ፍላጎቶች የማሟላት ኃላፊነት የተሰጣቸው መጋቢያን ነበሩ። አምስተኛ፥ ሰዎች እግዚአብሔር በሚፈልገው መንገድ እንዲመላለሱ በሚያበረታታ መልኩ የእግዚአብሔርን ቃል የማስተላለፍ ስጦታ የተሰጣቸው መምህራን ነበሩ። (ከግሪኩ መጽሐፍ ቅዱስ የመጋቢነትና የአስተማሪነት ስጦታ አንድ ይሁን ወይም ሁለት የተለያዩ ስጦታዎች መሆናቸውን መረዳቱ አስቸጋሪ ነው።) ክርስቶስ ለቤተ ክርስቲያን እነዚህን የመሪነት ስጦታዎች የሰጠው የክርስቶስ አካል መንፈሳዊ አመራር እንዲኖራት ነው። የአመራር ስጦታዎች ቤተ ክርስቲያንን ለመትከል፥ ለማሳደግና ለጠፉት ወንጌሉን እንድትሰብክ ለማገዝ ይረዳሉ።
የውይይት ጥያቄ፡- ሀ) ከላይ የተጠቀሱት አምስት መንፈሳዊ ስጦታዎች እንዳሏቸው የምታውቋቸውን ሰዎች በምሳሌነት ጥቀስ። ለ) ሰዎቹ መንፈሳዊ ስጦታዎቹ እንዳሏቸው እንዴት ታውቃለህ?
የአመራር ስጦታዎች ዓላማ ምንድን ነው? ብዙውን ጊዜ መሪዎች አገልግሎታቸውን በውል ስለማያውቁ ግራ ይጋባሉ። ከዚህም የተነሣ እግዚአብሔር የሚፈልገውን ከማድረግ ይልቅ የዓለምን የአመራር ስልት ይኮርጃሉ። ብዙ ሽማግሌዎች ወይም መጋቢዎች መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ሥራቸው የሚናገረውን አያውቁም። በኤፌሶን 4፡12-13 ጳውሎስ አንድ የቤተ ክርስቲያን መሪ እግዚአብሔር በሰጠው የመሪነት ስጦታ አማካኝነት ምን ማድረግ እንዳለበት አብራርቷል።
ሀ. መንፈሳዊ መሪዎች «ቅዱሳን አገልግሎትን ለመሥራት ለክርስቶስ አካል ሕንፃ ፍጹማን ይሆኑ ዘንድ» ማዘጋጀት አለባቸው። ብዙውን ጊዜ መሪዎች ቤተ ክርስቲያን ውስጥ መሥራት እንዳለባቸው ያስባሉ። ጳውሎስ ግን ምእመናን የቤተ ክርስቲያኒቱን አገልግሎት ያካሂዱ ዘንድ መሪዎች ሊያሠለጥኗቸው እንደሚገባ አስረድቷል። መሪዎች ምእመናን ከእግዚአብሔር የተቀበሉትን ስጦታ ለይተው እንዲያውቁ ሊረዷቸው ይገባል። ከዚያም በስጦታዎቻቸው አማካኝነት የክርስቶስን አካል ይገነቡ ዘንድ የአገልግሎትን ስፍራዎች ሊሰጧቸው ይገባል።
ለ. መንፈሳዊ መሪዎች ምእመኖቻቸውን በሚያሠለጥኑበት ጊዜ ሕዝቡ ወደ ክርስቶስ ፍጹም ሙላት ይደርሳሉ። በሌላ አገላለጽ፥ በእምነታቸው በመብሰል፥ ስለ ክርስቶስ የጠለቀ እውቀት በማግኘትና በአንድነት በመመላለስ ያድጋሉ። እግዚአብሔር እንደሚፈልግባቸው በመኖር ለወንጌሉ እንደሚገባ ይመላለሳሉ።
አንድ ክርስቲያን በብስለት ማደጉን እንዴት እናውቃለን? ያ ብስለት እንዴት ራሱን ይገልጻል? ጳውሎስ አያሌ ነገሮችን ዘርዝሯል።
1. በሳል ሰው በእምነቱ ይረጋል። አዳዲስ የሐሰት ትምህርቶች ሲመጡ አይናወጥም።
2. በሳል ሰው እውነትን በፍቅር ይናገራል። ይህ ከባድ ስለሆነ፥ ብዙውን ጊዜ ወደ አንደኛው አጽናፍ እናደላለን። አንዳንድ ክርስቲያኖች ብዙም ፍቅር ሳይኖራቸው እውነት ነው ብለው የሚያስቡትን በድፍረት ይናገራሉ። ይህ ብዙውን ጊዜ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የስሜት መጎዳትንና ክፍፍልን ያስከትላል። ሌሎች ክርስቲያኖች በፍቅር ላይ ከማተኮራቸው የተነሣ የሰዎችን ስሜት እንዳይጎዱ በመፍራት እውነትን አይናገሩም። ይህም ሰዎች በተሳሳቱ መንገዶች እንዲመላለሱና የቤተ ክርስቲያን ምስክርነት እንዲጎድፍ ያደርጋል። እግዚአብሔር ስለ እውነት እንድንገደድና በክርስቶስ ወንድሞቻችንና እኅቶቻችን ለሆኑት ወገኖቻችን እንድንናገር ይፈልጋል። ነገር ግን ሌላውን ሰው በሚረዳና በሚያሳድግ መልኩ እውነትን በፍቅር እንድንናገርም ይፈልጋል።
3. በሳል ሰው ከክርስቶስ ጋር የጠለቀ ግንኙነት አለው። ክርስቶስ በነገሮች ሁሉ ንጉሣችን እንደሆነ ተቀብለን በቅርብ ግንኙነት እንመላለሳለን። ክርስቲያኖች ሁሉ ከክርስቶስ ጋር እንዲህ ዓይነት ግንኙነት ሲኖራቸው ሁሉም ክርስቲያን በክርስቶስ አካል ውስጥ የራሱን ድርሻ ያሟላል። የዚህች ዓይነት ቤተ ክርስቲያን ታላቅ ኃይል አላት።
የውይይት ጥያቄ፡- ሀ) አብዛኛዎቹ የቤተ ክርስቲያንህ አባላት መንፈሳዊ ስጦታዎችን የሚያውቁ ይመስልሃል? ካልሆነ፥ ለምን? ለ) በቤተ ክርስቲያንህ የሚገኘው አብዛኛው ሕዝብ በመንፈሳዊ ሕይወቱ የበሰለ ይመስልሃል? ካልሆነ ለምን? ሐ) አንድ የቤተ ክርስቲያን መሪ የቤተ ክርስቲያኑ ምእመናን መንፈሳዊ ስጦታዎቻቸውን እንደሚያውቁ፥ እንደሚጠቀሙና ምእመናን ሁሉ በመንፈሳዊ ብስለት እንደሚያድጉ ለማረጋገጥ ምን ሊያደርግ ይችላል?
(ማብራሪያው የተወሰደው በ ኤስ.አይ.ኤም ከታተመውና የአዲስ ኪዳን የጥናት መምሪያና ማብራሪያ፣ ከተሰኘው መጽሐፍ ነው፡፡ እግዚአብሔር አገልግሎታቸውን ይባርክ፡፡)
ጳውሎስ ሁሉም ክርስቲያኖች መንፈሳዊ ስጦታዎችን እንደ ተቀበሉ ቢናገርም፥ በኤፌሶን መልእክቱ የመሪነት ስጦታዎችን በተመለከተ ብቻ በብዛት ጽፎአል። (ለምእመናን የተሰጡትን ሌሎች መንፈሳዊ ስጦታዎች ዝርዝር ከ1ኛ ቆሮንቶስ 12፡28-30 አንብብ።) ጳውሎስ ለቤተ ክርስቲያን የተሰጡትን አምስት ዐበይት የአመራር ስጦታዎች ገልጾአል። የአመራር ስጦታዎች ሰዎች በምርጫ ጊዜ የሚወስኗቸው አይደሉም። ነገር ግን እነዚህ ስጦታዎች እግዚአብሔር የሚሰጣቸውና እኛም ለይተን ለቤተ ክርስቲያን የምንጠቀምባቸው ናቸው። እግዚአብሔር የመሪነት ስጦታ የሰጣቸውን ሰዎች ለዚሁ አገልግሎት መምረጥ አለብን። ነገር ግን ስጦታ የሌለውን ሰው ልንመርጥና ከዚያ በኋላ እግዚአብሔር ስጦታውን ይሰጠዋል ብለን ልንጠብቅ አይገባም። በመጀመሪያ፥ ሐዋርያት ተጠቅሰዋል። እዚህ ላይ ጳውሎስ ክርስቶስ ስለ ሾማቸው በኢየሱስ ስለተመረጡት 12ቱና ስለ ራሱ እያሰበ መሆኑ አይጠረጠርም። ነገር ግን እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን ለመመሥረት ስለተጠቀመባቸው አገልጋዮችም እያሰበ ሊሆን ይችላል። ሁለተኛ፥ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለክርስቶስ አካል የማስተላለፍ ኃላፊነት የተሰጣቸው ነቢያት አሉ። ይህ የመሪነት ተግባር አዲስ ኪዳን ከመጻፉ በፊት ለቀድሞይቱ ቤተ ክርስቲያን የተለየ ጠቀሜታ ነበረው። ሦስተኛ፥ ወንጌሉን ለዓለማውያን የማካፈል ስጦታ የተሰጣቸው ወንጌላውያን ነበሩ። አራተኛ፥ የአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናትን ምእመናን መንፈሳዊ ፍላጎቶች የማሟላት ኃላፊነት የተሰጣቸው መጋቢያን ነበሩ። አምስተኛ፥ ሰዎች እግዚአብሔር በሚፈልገው መንገድ እንዲመላለሱ በሚያበረታታ መልኩ የእግዚአብሔርን ቃል የማስተላለፍ ስጦታ የተሰጣቸው መምህራን ነበሩ። (ከግሪኩ መጽሐፍ ቅዱስ የመጋቢነትና የአስተማሪነት ስጦታ አንድ ይሁን ወይም ሁለት የተለያዩ ስጦታዎች መሆናቸውን መረዳቱ አስቸጋሪ ነው።) ክርስቶስ ለቤተ ክርስቲያን እነዚህን የመሪነት ስጦታዎች የሰጠው የክርስቶስ አካል መንፈሳዊ አመራር እንዲኖራት ነው። የአመራር ስጦታዎች ቤተ ክርስቲያንን ለመትከል፥ ለማሳደግና ለጠፉት ወንጌሉን እንድትሰብክ ለማገዝ ይረዳሉ።
የውይይት ጥያቄ፡- ሀ) ከላይ የተጠቀሱት አምስት መንፈሳዊ ስጦታዎች እንዳሏቸው የምታውቋቸውን ሰዎች በምሳሌነት ጥቀስ። ለ) ሰዎቹ መንፈሳዊ ስጦታዎቹ እንዳሏቸው እንዴት ታውቃለህ?
የአመራር ስጦታዎች ዓላማ ምንድን ነው? ብዙውን ጊዜ መሪዎች አገልግሎታቸውን በውል ስለማያውቁ ግራ ይጋባሉ። ከዚህም የተነሣ እግዚአብሔር የሚፈልገውን ከማድረግ ይልቅ የዓለምን የአመራር ስልት ይኮርጃሉ። ብዙ ሽማግሌዎች ወይም መጋቢዎች መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ሥራቸው የሚናገረውን አያውቁም። በኤፌሶን 4፡12-13 ጳውሎስ አንድ የቤተ ክርስቲያን መሪ እግዚአብሔር በሰጠው የመሪነት ስጦታ አማካኝነት ምን ማድረግ እንዳለበት አብራርቷል።
ሀ. መንፈሳዊ መሪዎች «ቅዱሳን አገልግሎትን ለመሥራት ለክርስቶስ አካል ሕንፃ ፍጹማን ይሆኑ ዘንድ» ማዘጋጀት አለባቸው። ብዙውን ጊዜ መሪዎች ቤተ ክርስቲያን ውስጥ መሥራት እንዳለባቸው ያስባሉ። ጳውሎስ ግን ምእመናን የቤተ ክርስቲያኒቱን አገልግሎት ያካሂዱ ዘንድ መሪዎች ሊያሠለጥኗቸው እንደሚገባ አስረድቷል። መሪዎች ምእመናን ከእግዚአብሔር የተቀበሉትን ስጦታ ለይተው እንዲያውቁ ሊረዷቸው ይገባል። ከዚያም በስጦታዎቻቸው አማካኝነት የክርስቶስን አካል ይገነቡ ዘንድ የአገልግሎትን ስፍራዎች ሊሰጧቸው ይገባል።
ለ. መንፈሳዊ መሪዎች ምእመኖቻቸውን በሚያሠለጥኑበት ጊዜ ሕዝቡ ወደ ክርስቶስ ፍጹም ሙላት ይደርሳሉ። በሌላ አገላለጽ፥ በእምነታቸው በመብሰል፥ ስለ ክርስቶስ የጠለቀ እውቀት በማግኘትና በአንድነት በመመላለስ ያድጋሉ። እግዚአብሔር እንደሚፈልግባቸው በመኖር ለወንጌሉ እንደሚገባ ይመላለሳሉ።
አንድ ክርስቲያን በብስለት ማደጉን እንዴት እናውቃለን? ያ ብስለት እንዴት ራሱን ይገልጻል? ጳውሎስ አያሌ ነገሮችን ዘርዝሯል።
1. በሳል ሰው በእምነቱ ይረጋል። አዳዲስ የሐሰት ትምህርቶች ሲመጡ አይናወጥም።
2. በሳል ሰው እውነትን በፍቅር ይናገራል። ይህ ከባድ ስለሆነ፥ ብዙውን ጊዜ ወደ አንደኛው አጽናፍ እናደላለን። አንዳንድ ክርስቲያኖች ብዙም ፍቅር ሳይኖራቸው እውነት ነው ብለው የሚያስቡትን በድፍረት ይናገራሉ። ይህ ብዙውን ጊዜ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የስሜት መጎዳትንና ክፍፍልን ያስከትላል። ሌሎች ክርስቲያኖች በፍቅር ላይ ከማተኮራቸው የተነሣ የሰዎችን ስሜት እንዳይጎዱ በመፍራት እውነትን አይናገሩም። ይህም ሰዎች በተሳሳቱ መንገዶች እንዲመላለሱና የቤተ ክርስቲያን ምስክርነት እንዲጎድፍ ያደርጋል። እግዚአብሔር ስለ እውነት እንድንገደድና በክርስቶስ ወንድሞቻችንና እኅቶቻችን ለሆኑት ወገኖቻችን እንድንናገር ይፈልጋል። ነገር ግን ሌላውን ሰው በሚረዳና በሚያሳድግ መልኩ እውነትን በፍቅር እንድንናገርም ይፈልጋል።
3. በሳል ሰው ከክርስቶስ ጋር የጠለቀ ግንኙነት አለው። ክርስቶስ በነገሮች ሁሉ ንጉሣችን እንደሆነ ተቀብለን በቅርብ ግንኙነት እንመላለሳለን። ክርስቲያኖች ሁሉ ከክርስቶስ ጋር እንዲህ ዓይነት ግንኙነት ሲኖራቸው ሁሉም ክርስቲያን በክርስቶስ አካል ውስጥ የራሱን ድርሻ ያሟላል። የዚህች ዓይነት ቤተ ክርስቲያን ታላቅ ኃይል አላት።
የውይይት ጥያቄ፡- ሀ) አብዛኛዎቹ የቤተ ክርስቲያንህ አባላት መንፈሳዊ ስጦታዎችን የሚያውቁ ይመስልሃል? ካልሆነ፥ ለምን? ለ) በቤተ ክርስቲያንህ የሚገኘው አብዛኛው ሕዝብ በመንፈሳዊ ሕይወቱ የበሰለ ይመስልሃል? ካልሆነ ለምን? ሐ) አንድ የቤተ ክርስቲያን መሪ የቤተ ክርስቲያኑ ምእመናን መንፈሳዊ ስጦታዎቻቸውን እንደሚያውቁ፥ እንደሚጠቀሙና ምእመናን ሁሉ በመንፈሳዊ ብስለት እንደሚያድጉ ለማረጋገጥ ምን ሊያደርግ ይችላል?
(ማብራሪያው የተወሰደው በ ኤስ.አይ.ኤም ከታተመውና የአዲስ ኪዳን የጥናት መምሪያና ማብራሪያ፣ ከተሰኘው መጽሐፍ ነው፡፡ እግዚአብሔር አገልግሎታቸውን ይባርክ፡፡)