ዐቂዳህ
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
3፥103 የአሏህን ገመድ ሁላችሁም ያዙ። وَاعْتَصِمُوا بِحَبْلِ اللَّهِ جَمِيعًا
"ዐቂዳህ" عَقِيدَة የሚለው ቃል "ዐቀደ" عَقَدَ ማለትም "ቋጠረ" "ያዘ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "መቋጠር" "መያዝ" ማለት ነው፥ "ዐቃኢድ" عَقَائِد ደግሞ "ዐቂዳህ" عَقِيدَة ለሚለው ብዙ ቁጥር ነው፦
113፥4 “በየተቋጠሩ” ክሮች ላይ ተፊዎች ከኾኑት ደጋሚ ሴቶችም ክፋት፡፡ وَمِن شَرِّ ٱلنَّفَّٰثَٰتِ فِى ٱلْعُقَدِ
እዚህ አንቀጽ ላይ "የተቋጠሩ" ለሚለው የገባው ቃል "ዑቀድ" عُقَد እንደሆነ ልብ አድርግ! ለምሳሌ፦ የጋብቻ ቃል ኪዳን "ዑቅደቱን ኒካህ" عُقْدَةُ النِّكَاح ተብሎ ይጠራል፦
2፥237 ለእነርሱም መወሰንን በእርግጥ የወሰናችሁላቸው ስትኾኑ ሳትነኳቸው በፊት ብተፈቷቸው ካልማሩዋችሁ ወይም ያ "የጋብቻው ውል" በእጁ የኾነው ባልየው ካልማረ በስተቀር የወሰናችሁት ግማሹ አላቸው፡፡ وَإِن طَلَّقْتُمُوهُنَّ مِن قَبْلِ أَن تَمَسُّوهُنَّ وَقَدْ فَرَضْتُمْ لَهُنَّ فَرِيضَةً فَنِصْفُ مَا فَرَضْتُمْ إِلَّا أَن يَعْفُونَ أَوْ يَعْفُوَ الَّذِي بِيَدِهِ عُقْدَةُ النِّكَاحِ
እዚህ አንቀጽ ላይ "የጋብቻው ውል" ለሚለው የገባው ቃል "ዑቅደቱን ኒካህ" عُقْدَةُ النِّكَاحعُقَد ነው፥ ስለዚህ አንድ ሰው እኔን፡- "ዐቂዳህ" ምንድነው? ብሎ ቢጠይቀኝ ጥያቄው፡- በልብህ አምነህ የያዝከው እና የቋጠርከው ምንድነው? ማለቱ ነው።
ይህ ቋንቋዊ ፍቺው ሲሆን "ዐቂዳህ" عَقِيدَة ሸሪዓዊ ፍቺው ደግሞ "አንቀጸ እምነት" "ዶግማ" ማለት ነው፥ "ዶግማ" δόγμα የሚለው ቃል የግሪክ ቃል ሲሆን "መሠረት" "መርሕ" "አንቀጸ እምነት"creed" ማለት ነው፦
ሡነን አድ ዳርሚይ መጽሐፍ 1 ሐዲስ 231
ዐብዱር ረሕማን ኢብኑ አባን እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ":እንዲህ አሉ፦ "የሙሥሊም ልብ በሦስት ጉዳይ "አያምንም" ጀነት የሚገባበት ቢሆን እንጂ፥ እኔም፦ "ምንድን ናቸው? አልኩኝ። እርሳቸው፦ "ለአሏህ ብሎ በኢኽላስ መሥራት፣ ለአሚር ቅን ምክር መስጠት እና ጀመዓን አጥብቆ መያዝ"። عَنْ عَبْدِ الرَّحْمَنِ بْنِ أَبَانَ رَسُولِ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ :" لَا يَعْتَقِدُ قَلْبُ مُسْلِمٍ عَلَى ثَلَاثِ خِصَالٍ إِلَّا دَخَلَ الْجَنَّةَ "، قَالَ : قُلْتُ : مَا هُنَّ؟، قَالَ : إِخْلَاصُ الْعَمَلِ لِلَّهِ، وَالنَّصِيحَةُ لِوُلَاةِ الْأَمْرِ، وَلُزُومُ الْجَمَاعَةِ،
እዚህ ሐዲስ ላይ "የዕተቂዱ" يَعْتَقِدُ የሚለው "ዩእሚኑ" يُؤْمِنُو በሚል የመጣ ነው፥ ቁርኣን ላይ "ኢማን" إِيمَان የሚለው "ኢዕቲቃድ" اِعْتِقَاد ማለት ነው፦
5፥89 አሏህ በመሐላዎቻችሁ በውድቁ አይዛችሁም፥ ግን መሐላዎችን "ባሰባችሁት" ይይዛችኋል፡፡ لَا يُؤَاخِذُكُمُ اللَّهُ بِاللَّغْوِ فِي أَيْمَانِكُمْ وَلَـٰكِن يُؤَاخِذُكُم بِمَا عَقَّدتُّمُ الْأَيْمَانَ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ባሰባችሁት" ለሚለው የገባው ቃል "ዐቀድቱም" عَقَّدتُّم ሲሆን "በወጠናችሁት" ማለት ነው፥ "ዐቅድ" عَقْد ማለት በልብ ውስጥ ያለ "ውጥን" ማለት ሲሆን በልብ ውስጥ የሚቀመጥ ውጥን ደግሞ እምነት ነው።
አርካኑል ኢማን "ዐቀዲይ" عَقَدِيّ ወይም "ዐቃኢዲይ" عَقَائِدِيّ ናቸው፥ "ዐቀዲይ" عَقَدِيّ ወይም "ዐቃኢዲይ" عَقَائِدِيّ ማለት "ዶግማዊ"dogmatic" ማለት ነው። "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه ማለት "ከአሏህ በስተቀር በሐቅ የሚመለክ አምላክ የለም" ማለት ነው፥ "ኢማን" إِيمَٰن ማለት "እምነት" ማለት ሲሆን የኢማን ትልቁ ቅርንጫፍ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" ማለት ነው፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 1, ሐዲስ 60
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ “የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ "ኢማን ከሰባ ወይም ከስልሳ በላይ ቅርንጫፎች አሉት፥ ትልቁ ቅርንጫፍ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" ማለት ነው"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم “ الإِيمَانُ بِضْعٌ وَسَبْعُونَ أَوْ بِضْعٌ وَسِتُّونَ شُعْبَةً فَأَفْضَلُهَا قَوْلُ لاَ إِلَهَ إِلاَّ اللَّهُ
"ነፍይ" نَفْي ማለት “ማፍረስ” ማለት ሲሆን ነፍይ “ላ ኢላሀ” لَا إِلَـٰهَ ነው፥ “ኢስባት” إِثْبَات ማለት “ማጽደቅ” ማለት ሲሆን ኢስባት “ኢለል ሏህ” إِلَّا اللّٰه ነው፦
2፥256 “በጣዖት የሚክድ እና በአሏህ የሚያምን ሰው ለእርሷ መበጠስ የሌላትን ጠንካራ ገመድ በእርግጥ ያዘ”፡፡ فَمَن يَكْفُرْ بِالطَّاغُوتِ وَيُؤْمِن بِاللَّهِ فَقَدِ اسْتَمْسَكَ بِالْعُرْوَةِ الْوُثْقَىٰ لَا انفِصَامَ لَهَا
“ላ ኢላሀ” لَا إِلَـٰهَ በጣዖት መካድ ሲሆን “ኢለል ሏህ” إِلَّا اللّٰه በአሏህ ማመን ነው፥ ከአርካኑል ኢማን አንዱ የሆነው የመጀመሪያው እና ዋናው "አመንቱ ቢላህ" آمَنْتُ بِاللَّه ነው። "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه የሚለውን ጠንካራ የአሏህን ገመድ መያዝ "ዐቂዳህ" عَقِيدَة ይባላል፦
3፥103 የአሏህን ገመድ ሁላችሁም ያዙ። وَاعْتَصِمُوا بِحَبْلِ اللَّهِ جَمِيعًا
"ያዙ" የሚለው ይሰመርበት! ይህ ገመድ ሰዎች ከጀሀነም እሳት ጉድጋድ አፋፍ ላይ እያሉ ተንጠንጥለው የሚድኑበት ገመድ ነው፦
3፥103 በእሳት ጉድጓድ አፋፍም ላይ ነበራችሁ፥ ከእርስዋም አዳናችሁ፡፡ وَكُنتُمْ عَلَىٰ شَفَا حُفْرَةٍ مِّنَ النَّارِ فَأَنقَذَكُم مِّنْهَا
አርካኑል ኢሥላም "ዐቂዲያህ" عَقِيدِيَّة ወይም "ዐቃዒዲያህ" عَقَائِدِيَّة ናቸው፥ "ዐቂዲያህ" عَقِيدِيَّة ወይም "ዐቃዒዲያህ" عَقَائِدِيَّة ማለት "ዶግማውያን"dogmatism" ማለት ነው። ከአርካኑል ኢሥላም አንዱ የሆነው የመጀመሪያው እና ዋናው "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه ነው፥ ሙሉ ሁለንተናውን ለአሏህ የሰጠ ሙሥሊም ጠንካራ ገመድን በእርግጥ ያዘ፦
31፥22 እርሱ መልካም ሠሪ ሆኖ ፊቱን ወደ አሏህ የሚሰጥም ሰው ጠንካራ ገመድን በእርግጥ ያዘ፡፡ وَمَن يُسْلِمْ وَجْهَهُ إِلَى اللَّهِ وَهُوَ مُحْسِنٌ فَقَدِ اسْتَمْسَكَ بِالْعُرْوَةِ الْوُثْقَىٰ
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
3፥103 የአሏህን ገመድ ሁላችሁም ያዙ። وَاعْتَصِمُوا بِحَبْلِ اللَّهِ جَمِيعًا
"ዐቂዳህ" عَقِيدَة የሚለው ቃል "ዐቀደ" عَقَدَ ማለትም "ቋጠረ" "ያዘ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "መቋጠር" "መያዝ" ማለት ነው፥ "ዐቃኢድ" عَقَائِد ደግሞ "ዐቂዳህ" عَقِيدَة ለሚለው ብዙ ቁጥር ነው፦
113፥4 “በየተቋጠሩ” ክሮች ላይ ተፊዎች ከኾኑት ደጋሚ ሴቶችም ክፋት፡፡ وَمِن شَرِّ ٱلنَّفَّٰثَٰتِ فِى ٱلْعُقَدِ
እዚህ አንቀጽ ላይ "የተቋጠሩ" ለሚለው የገባው ቃል "ዑቀድ" عُقَد እንደሆነ ልብ አድርግ! ለምሳሌ፦ የጋብቻ ቃል ኪዳን "ዑቅደቱን ኒካህ" عُقْدَةُ النِّكَاح ተብሎ ይጠራል፦
2፥237 ለእነርሱም መወሰንን በእርግጥ የወሰናችሁላቸው ስትኾኑ ሳትነኳቸው በፊት ብተፈቷቸው ካልማሩዋችሁ ወይም ያ "የጋብቻው ውል" በእጁ የኾነው ባልየው ካልማረ በስተቀር የወሰናችሁት ግማሹ አላቸው፡፡ وَإِن طَلَّقْتُمُوهُنَّ مِن قَبْلِ أَن تَمَسُّوهُنَّ وَقَدْ فَرَضْتُمْ لَهُنَّ فَرِيضَةً فَنِصْفُ مَا فَرَضْتُمْ إِلَّا أَن يَعْفُونَ أَوْ يَعْفُوَ الَّذِي بِيَدِهِ عُقْدَةُ النِّكَاحِ
እዚህ አንቀጽ ላይ "የጋብቻው ውል" ለሚለው የገባው ቃል "ዑቅደቱን ኒካህ" عُقْدَةُ النِّكَاحعُقَد ነው፥ ስለዚህ አንድ ሰው እኔን፡- "ዐቂዳህ" ምንድነው? ብሎ ቢጠይቀኝ ጥያቄው፡- በልብህ አምነህ የያዝከው እና የቋጠርከው ምንድነው? ማለቱ ነው።
ይህ ቋንቋዊ ፍቺው ሲሆን "ዐቂዳህ" عَقِيدَة ሸሪዓዊ ፍቺው ደግሞ "አንቀጸ እምነት" "ዶግማ" ማለት ነው፥ "ዶግማ" δόγμα የሚለው ቃል የግሪክ ቃል ሲሆን "መሠረት" "መርሕ" "አንቀጸ እምነት"creed" ማለት ነው፦
ሡነን አድ ዳርሚይ መጽሐፍ 1 ሐዲስ 231
ዐብዱር ረሕማን ኢብኑ አባን እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ":እንዲህ አሉ፦ "የሙሥሊም ልብ በሦስት ጉዳይ "አያምንም" ጀነት የሚገባበት ቢሆን እንጂ፥ እኔም፦ "ምንድን ናቸው? አልኩኝ። እርሳቸው፦ "ለአሏህ ብሎ በኢኽላስ መሥራት፣ ለአሚር ቅን ምክር መስጠት እና ጀመዓን አጥብቆ መያዝ"። عَنْ عَبْدِ الرَّحْمَنِ بْنِ أَبَانَ رَسُولِ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ :" لَا يَعْتَقِدُ قَلْبُ مُسْلِمٍ عَلَى ثَلَاثِ خِصَالٍ إِلَّا دَخَلَ الْجَنَّةَ "، قَالَ : قُلْتُ : مَا هُنَّ؟، قَالَ : إِخْلَاصُ الْعَمَلِ لِلَّهِ، وَالنَّصِيحَةُ لِوُلَاةِ الْأَمْرِ، وَلُزُومُ الْجَمَاعَةِ،
እዚህ ሐዲስ ላይ "የዕተቂዱ" يَعْتَقِدُ የሚለው "ዩእሚኑ" يُؤْمِنُو በሚል የመጣ ነው፥ ቁርኣን ላይ "ኢማን" إِيمَان የሚለው "ኢዕቲቃድ" اِعْتِقَاد ማለት ነው፦
5፥89 አሏህ በመሐላዎቻችሁ በውድቁ አይዛችሁም፥ ግን መሐላዎችን "ባሰባችሁት" ይይዛችኋል፡፡ لَا يُؤَاخِذُكُمُ اللَّهُ بِاللَّغْوِ فِي أَيْمَانِكُمْ وَلَـٰكِن يُؤَاخِذُكُم بِمَا عَقَّدتُّمُ الْأَيْمَانَ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ባሰባችሁት" ለሚለው የገባው ቃል "ዐቀድቱም" عَقَّدتُّم ሲሆን "በወጠናችሁት" ማለት ነው፥ "ዐቅድ" عَقْد ማለት በልብ ውስጥ ያለ "ውጥን" ማለት ሲሆን በልብ ውስጥ የሚቀመጥ ውጥን ደግሞ እምነት ነው።
አርካኑል ኢማን "ዐቀዲይ" عَقَدِيّ ወይም "ዐቃኢዲይ" عَقَائِدِيّ ናቸው፥ "ዐቀዲይ" عَقَدِيّ ወይም "ዐቃኢዲይ" عَقَائِدِيّ ማለት "ዶግማዊ"dogmatic" ማለት ነው። "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه ማለት "ከአሏህ በስተቀር በሐቅ የሚመለክ አምላክ የለም" ማለት ነው፥ "ኢማን" إِيمَٰن ማለት "እምነት" ማለት ሲሆን የኢማን ትልቁ ቅርንጫፍ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" ማለት ነው፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 1, ሐዲስ 60
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ “የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ "ኢማን ከሰባ ወይም ከስልሳ በላይ ቅርንጫፎች አሉት፥ ትልቁ ቅርንጫፍ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" ማለት ነው"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم “ الإِيمَانُ بِضْعٌ وَسَبْعُونَ أَوْ بِضْعٌ وَسِتُّونَ شُعْبَةً فَأَفْضَلُهَا قَوْلُ لاَ إِلَهَ إِلاَّ اللَّهُ
"ነፍይ" نَفْي ማለት “ማፍረስ” ማለት ሲሆን ነፍይ “ላ ኢላሀ” لَا إِلَـٰهَ ነው፥ “ኢስባት” إِثْبَات ማለት “ማጽደቅ” ማለት ሲሆን ኢስባት “ኢለል ሏህ” إِلَّا اللّٰه ነው፦
2፥256 “በጣዖት የሚክድ እና በአሏህ የሚያምን ሰው ለእርሷ መበጠስ የሌላትን ጠንካራ ገመድ በእርግጥ ያዘ”፡፡ فَمَن يَكْفُرْ بِالطَّاغُوتِ وَيُؤْمِن بِاللَّهِ فَقَدِ اسْتَمْسَكَ بِالْعُرْوَةِ الْوُثْقَىٰ لَا انفِصَامَ لَهَا
“ላ ኢላሀ” لَا إِلَـٰهَ በጣዖት መካድ ሲሆን “ኢለል ሏህ” إِلَّا اللّٰه በአሏህ ማመን ነው፥ ከአርካኑል ኢማን አንዱ የሆነው የመጀመሪያው እና ዋናው "አመንቱ ቢላህ" آمَنْتُ بِاللَّه ነው። "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه የሚለውን ጠንካራ የአሏህን ገመድ መያዝ "ዐቂዳህ" عَقِيدَة ይባላል፦
3፥103 የአሏህን ገመድ ሁላችሁም ያዙ። وَاعْتَصِمُوا بِحَبْلِ اللَّهِ جَمِيعًا
"ያዙ" የሚለው ይሰመርበት! ይህ ገመድ ሰዎች ከጀሀነም እሳት ጉድጋድ አፋፍ ላይ እያሉ ተንጠንጥለው የሚድኑበት ገመድ ነው፦
3፥103 በእሳት ጉድጓድ አፋፍም ላይ ነበራችሁ፥ ከእርስዋም አዳናችሁ፡፡ وَكُنتُمْ عَلَىٰ شَفَا حُفْرَةٍ مِّنَ النَّارِ فَأَنقَذَكُم مِّنْهَا
አርካኑል ኢሥላም "ዐቂዲያህ" عَقِيدِيَّة ወይም "ዐቃዒዲያህ" عَقَائِدِيَّة ናቸው፥ "ዐቂዲያህ" عَقِيدِيَّة ወይም "ዐቃዒዲያህ" عَقَائِدِيَّة ማለት "ዶግማውያን"dogmatism" ማለት ነው። ከአርካኑል ኢሥላም አንዱ የሆነው የመጀመሪያው እና ዋናው "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه ነው፥ ሙሉ ሁለንተናውን ለአሏህ የሰጠ ሙሥሊም ጠንካራ ገመድን በእርግጥ ያዘ፦
31፥22 እርሱ መልካም ሠሪ ሆኖ ፊቱን ወደ አሏህ የሚሰጥም ሰው ጠንካራ ገመድን በእርግጥ ያዘ፡፡ وَمَن يُسْلِمْ وَجْهَهُ إِلَى اللَّهِ وَهُوَ مُحْسِنٌ فَقَدِ اسْتَمْسَكَ بِالْعُرْوَةِ الْوُثْقَىٰ