«ሱና የኑሕ መርከብ ናት »


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


✍🏽‏ قال العلامة ربيع المدخلي -حفظه الله- :

*《 ما ضاع شباب الأمة وما ضاع الناس ،*
*إلا بالسكوت على الباطل 》.‏*
📓 |[ المَـصـدَرُ : المجموع (436/15) ]|

Related channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter


~ ቤተሰቦቻችንንና ጎሮቤታችንን  እንፈልጋቸው

ከቤተሰቦቻችን እና ከጎረቤት ከልጅ እናት ከነብሰጡር ከየቲም ቤቶች ስንት አሉ ሰው አንጠይቅም ብለው እጃቸውን የሰበሰቡ በተለይ በዚህ ረመዷን ወር ማፍጠሪያ አጥተው በረሀብ የሚሰቃዩ ቤታቸውን /ጎጃቸውን ዘግተው የሚያለቅሱ!  ምግብ ልብስ ባዩ ቁጥር ልባቸው የሚደሙ በርግጥ ሁኔታቸውን በቅርብ የሚያውቅላቸው ከአሏህ በቀር ማንም ያሌላቸው ብዙ ናቸው ።

ስለዚህ እኛ ስንበላ ስንጠጣ ስንለብስ ስንደሰት እነሱን የት ናቸው በምን አሉ እንበል አሏህ ባሪያውን በማገዝ ላይ ነው ባሪያው ወንድሙን በማገዝ ላይ እስከሆነ ድረስ ብለዋል መልዕክተኛው ﷺ የየቲሞችን የዘመዶቻችንን እንባ እናብስ ።

join #telegram ቻናል
https://t.me/abuabdurahmen


Video is unavailable for watching
Show in Telegram


📌 አዲስ ትምህርት

مجالــــــــس شهر رمضـــــان

لفضيلة الشيخ محمد بن صالح العثيمين رحمه الله تعلى

መጃሊስ ሸህሩ ረመዳን

🔹 درس جديد

🔷 በኡስታዝ አቡ አብድራህማን አብድቃድር ቢን ሐሰን

الأستاذ ابو عبد الرحمن عبد القادر بن حسن

ክፍል 07

درس ٧

በአዳማ ከተማ ሰለፍ አል ሷሊህ መድረሳ እየተሰጠ ያለ ትምህርት

• هدفنـا الدعـوة إلـى الله عزَّوجـل بالرجـوع إلـى الكتـاب و السنـة بفهـم سلـف الأمـة
https://telegram.me/Adamamedresa
https://telegram.me/Adamamedresa
https://telegram.me/Adamamedresa


🚫 የኢብኑ ሙነወር የነሲሓዎች ትችት ወቀሳ ወይስ ውለታ ?

ኢብኑ ሙነወር ሶሞኑን ስለመርከዙ ሰዎች ትችት መሳይ ነገር ፅፎ የተለመደውን ከጭብጥ የማስወጣቱን አካሄድ ሄዶ አብዛኞችን ለመሸወድ ችሏል ። በሱ ሚዛን በጭፍን ሳይሆን በመረጃ የሚከተሉ የሚላቸውን ተከታዮቹን ብቻ ሳይሆን የሱን አካሄድ የማያውቁ ሰለፍዮችንም የመርከዙን ሰዎች የተቸ እንዲመስላቸው አድርጓል ።
ኢብኑ ሙነወር የመርከዙ ሰዎች ወሰን ታልፎባቸዋል ብሎ እኛን ለውይይት ሲጠራ አንዱ አጀንዳ ወሰን ታልፎባቸዋል የሚለውን አድርጎ ነበር ። እኛም ይሄኛው ነጥብ እኛና እነርሱን የሚለይ መሆኑን አሳውቀን ውይይቱን የሰረዝን መሆኑን ገልፀን ሜዳውን በአሸናፊነት እንዲጨፍሩበት ትተን ወጣን ።
በዚህ መልኩ ኢብኑ ሙነወር የሚሞግትላቸው ነሲሓዎች ግን ከድጡ ወደ ማጡ እንዲሉ በአደባባይ ኢኽዋንይነታቸውን በሚታክት መልኩ ያውጁ ጀመር ። እወጃው ዐቅል ያላቸውን ጥቂቶችን እያሸማቀቀ ቀጠለ ። መጨረሻ አካባቢ ብዙዎች እነዚህ ሰዎች በዚህ መልኩ አልመሰሉንም ነበር ብለው ወደ ሰለፍዮች መቀላቀል ጀመሩ ። የተወሰኑት ከማንም አይደለሁም የሚል ሌላ መዝሀብ እንዲዙ አደረጋቸው ። በጣም ብዙዎች አሁንም ለመስላሓ ነው እያሉ በሽንት ላይ እንደሚጎተት የረዘመ ጀለብያ መጎተት ጀመሩ ።
የዚህን ጊዜ የኢብኑ ሙነወር ተከታዮችን ስለ ነሲሓዎች አሁን ምን እንደሚል ጠዩቁት ሰለፍዮች ናቸው ወይስ ኢኽዋኖች በሉት ብለን ጥያቄ ላክን ።
ብልጣብልጡ ኢብኑ ሙነወር ለመስላሓ ሲባል በማያምኑበት ነገርም ቢሆን መነካካት ብስለትና ድፍረት የሚፈልግ ተግባር መሆኑን መቼና በምን አይነት ጉዳይ እንደሆነ ሳይገልፅ ለራሱ በደንብ ቆርሶ የመርከዙን ሰዎች በዚህ ጉዳይ ላይ በመኮነን አመለጠ ።
ኢብኑ ሙነወር መልስ ይስጥ የተባለው የመርከዙ ሰዎች ሰለፍዮች ናቸው ወይስ ኢኽዋንዮች ለሚለው ጥያቄ ነበር ። እሱ ግን የዚህን ጥያቄ መልስ በቀጥታ ሳይሆን በተዘዋዋሪ መልሶ ብዙዎችን ሸወደ ።
መልሱ ሰለፍዮች ናቸው ችግራቸው መስላሓና መፍሰዳ ማየት አለመቻል ነው የሚል ነው ። ‼
ይህ ለነሲሓዎች እነርሱ ባይፈልጉትም ወቀሳ ሳይሆን ውለታ ነው ። ምክንያቱም አሁን ለእነርሱ ኢኽዋንዮች ናቸው መባሉ እንጂ ሰለፍዮች ናቸው የሚለው አትራፊ ስለማያደርጋቸው ። የነሲሓዎች እንባ ጠባቂው ኢብኑ ሙነወር ግን ልክ ኢልያስ አሕመድ ዶ/ር ጀይላን ባይፈልግም ሰለፍይ ነው እንዳለው እሱም ነሲሓዎች ባይፈልጉም ሰለፍዮች ናቸው እያለ ነው ልብ በሉ ።

https://t.me/bahruteka




.السلام عليكم ورحمة الله وبركاته
.
በአይነቱ ለየት ያለና ደማቅ ፕሮግራም

➡️ዛሬ ማለትም የካቲት 15/2017 E.C
🕰ማታ ከ 3:20 ጀምሮ በአዳማ ከተማ የአልፈትህ ወነስር የሰለፊዮች የመስጅድ ቦታ ግዢ ገቢ ማሰባሰቢያ ግሩፕ ላይ የሙሓደራና የኒያ ፕሮግራም
ተዘጋጅቶ ይጠብቀናል።

🪑 ተጋባዥ እንግዳችን

🎙የተከበሩ  ሸይኽ አቡዘር አላሕ ይጠብቃቸው

🔹 ሙሐደራው የሚደረግበት አድራሻ የሚከተለው ሲሆን 𝕛𝕠𝕚𝕟 ብለው ይጠብቁን !!!

https://t.me/adama_ahlusuna_weljemea


.السلام عليكم ورحمة الله وبركاته
.
በአይነቱ ለየት ያለና ደማቅ ፕሮግራም

➡️ ነገ ማለትም የካቲት 10/2017 E.C
🕰ማታ ከ 3:20 ጀምሮ በአዳማ የሰለፊዮች መስጅድ ግዢ ገቢ ማሰባሰቢያ ግሩፕ ላይ የሙሓደራና የኒያ ፕሮግራም
ተዘጋጅቶ ይጠብቀናል።

🪑 ተጋባዥ እንግዳችን

🎙የተከበሩት ሸይኽ ሙሐመድ ሐያት ሐራ አላሕ ይጠብቃቸው

🔹 ሙሐደራው የሚደረግበት አድራሻ የሚከተለው ሲሆን 𝕛𝕠𝕚𝕟 ብለው ይጠብቁን !!!

https://t.me/adama_ahlusuna_weljemea


Forward from: መንሀጃችን ግልፅነው
አቡ ሁዘይፈተ #join_Share_ያርጉ
➘➘➘➘➘➘➘
https://t.me/Abuhuzeyfah20


ታላቅ የምስራች በአይነቱ ልዩ እና አጓጊ ታላቅ የሙሓደራ ድግስ በአዳማ ከተማ



    እነሆ የፊታችን እሁድ የካቲት 2/2017 በአዳማ ከተማ 03 ቀበሌ በመደረሰቱል ፈትህ ወነስር ልዩ የሙሐደራ እና ደማቅ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ተዘጋጅቶ ይጠብቃችኋል ።

     የእለቱ ተጋባዥ እንግዶች : –

①ታላቁ እና ተወዳጁ ዶ/ር ሸይኽ ሑሰይን ብን ሙሐመድ አስልጢይ (ሀፊዘሁሏህ)

②ተወዳጁ ዳዒ ኡስታዝ ሻኪር ሱልጣን (ሀፊዘሁሏህ)
  
በአሏህ ፍቃድ ሌሎችም ይኖራሉ

     ፕሮግራሙ በአላህ ፈቃድ ከጠዋቱ 2 : 30 የጀመራል ። 

https://t.me/adama_ahlusuna_weljemea














ሁላችንንም የሚመለከት መልዕክት
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته
➞➞➞➞➞➞
የተከበራችሁ  #ወንድሞቼ እና #እህቶቼ ቀን አልፎ ቀንን እየተካ  ይሄው  ትልቁ እንግዳችን  #ረመዷን  እየደረሰ ነው።
በመሆኑም  ይህን  ውድ እንግዳችንን  ተዘጋጅተን  መጠበቅ  አለብን።


#በተለይ_ደግሞ
ቀዷ ያለባችሁ ማለትም፦
                            ➲ #በህመም
                            ➩   በሀይድ
                            ➲ #በወሊድ
                            ➩   በጉዞ
                                ወይም
በሌላ ምክንያት  የባለፈውን #ረመዷን  በሙሉ ወይም በከፊል  ያልፆምን  እንድሁም  ቀዷውንም  እስካሁን  ያላወጣን  ካለን ይሄኛው #ረመዷን  ከመግባቱ በፊት  ማውጣት  አለብን።
ዝም ብለን ቆይተን ወሩ ከደረሰ በኋላ  ለፈታዋ #ከመሯሯጥ አሁኑ ቀዷ ያለብን  ቀዷችንን መፆም ተገቢ ነው።

በሌላ ከኩል በቀሩት ቀናት ውስጥ ደግሞ #ስለረመዷን ትምህርቶችን መማር አለብን።
#ይህ_ማለት
      ✅ ስለረመዷን ሁክም
      ✅ #ረመዷንን_መፆም ያለውን ደረጃ
      ✅ ረመዷንን ስለሚያበላሹት ነገሮች
      ✅ #ለፆመ_ሰው_ስለሚከለከሉ ነገሮች
      ✅  ለፆመ ሰውስለሚፈቀዱ ነገሮች
      ✅ #በረመዷን_ዙሪያ_ስለተሰጡ ፈታዋዎች
➷➴➘   
ወዘተ…ከተለያዩ #የመረጃ_ምንጮች  መማርና ማወቅ  ይጠቅመናል። 

ከመረጃ ምንጮች መካከል፦
                    ➜ የኡለሞች #ኪታቦች
                    ➜ የታማኝ
#ኡስታዞች
የቴሌግራምና የዋትሳፕ #ቻናሎች
#ስለረመዷን   የተለቀቁ   የታማኝ         
                           
#ኡስታዞች_ኦዲዮ
እንዴ ኡምደቱል እህካም መንሃጁ ሳሊኪን እና መሰል የፊቅህ ኪታቦች ላይ ኪታቡ ሲያም የሚለውን በአካባቢው በሚገኙ ኡስታዞች መሻይኾች ላይ ብትቀሩ (በትማሩ) መልካም ነው።

እና ሌሎችም።  እነዚህን #ተጠቅመን  ስለዚህ  ውድ  እንግዳችን  #ረመዷን  ተገቢውን  መረጃ  እና  #እውቀት  መሰብሰብ  አለብን።

ላልደረሳቸው Share በማድረግ  የአጅሩ  ተካፋይ  ይሁኑ!!!

▵▮▱▰▱▰▱▰▱▰▱▰▯▴
⚙ 📝 أَبُـــو عِـمْــرَان ❨𝕒𝕓𝕦 𝕚𝕞𝕣𝕒𝕟❩

🏝 ••⇣⇣.  🏖   ••⇣⇣ 
╰𝐒𝐡𝐚𝐫𝐞.   ╰𝐒𝐡𝐚𝐫𝐞

---------------⫷⫸-----------------
🖥️ በ 𝐓𝐞𝐥𝐞𝐠𝐫𝐚𝐦~𝐂𝐡𝐚𝐧𝐧𝐞𝐥
🏝 ⇣⇣⇣🍭⇣⇣⇣📲 ⇣⇣⇣↙️
https://t.me/AbuImranAselefy
https://t.me/AbuImranAselefy
https://t.me/AbuImranAselefy
⫷⫸⫷~⫸⫷⫸⫷~⫸⫷⫸⫷~⫸


«عظم شأن كلمة التوحيد: "لا إله إلا الله"، وبيان فضلها»

فَضِيلَة الشَّيْخِ عَبْد اللّه القُصَيِّـر
-حَفِظَهُ اللهُ-
join #telegram ቻናል
https://t.me/abuabdurahmen




🚫 ማቆሚያ የሌለው የነሲሓ ሙሪዶች መከራ

    የነሲሓ ከዐቅላቸው የተለያዩ ሙሪዶች ለሸይኻቸው ኢልያስ የሚደረድሩዋቸው ዑዝሮች መና የሚያስቀረው የኢልያስ ተግባር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ቅስማቸው ተሰብሮ አንገታቸውን እንዲሰብሩ ማድረጉን ቀጥሏል ። ነገር ግን ኢልያስ የገባበት እንገባለን የሚያቆመን የለም የሚሉት በውዴታው የታወሩና የሰከሩ ጭፍኖቹ ተከታዮች ስህተቱን የሚያዩበት አይናቸው እንዲታወር ዱዓእ አድርገው ተቀባይነት ያገኘ ይመስላል ።
      የኢልያስ አሕመድ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣው የማንነቱ ማሳያ ዛሬ ላይ ከሙሐመድ ዘይን ዘህረዲንና ከሀይደር  ከድር ጋር የኢኽዋን ሱፍይና አሕባሽ ጥምር መጅሊስ በ27/4/2017 ቦሌ ወሎ ሰፈር አቡ ሁረይራ መስጂድ ባዘጋጀው የዳዕዋ ፕሮግራም ላይ ፖስተሩ ተለጥፎ እኔ ማለት ይሄ ነኝ እዩኝ እያለ ነው ።
    ተቀጥፎት ነው እንዳትሉ ከተማው ላይ ዞር ዞር በሉ ለሱ ኩራት የመሰለው አሳፋሪው ከኢኽዋን አቀንቃኞች ጋር የተነሳው ፎቶ ፖስተር በሚቀጥለው ሊንክ ገብታችሁ እዩት : –
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://drive.google.com/file/d/1qEAPEj2G4zg_4Qcomh8lShRul4N6XhK2/view?usp=drivesdk
       ሙሐመድ ዘይን ዘህረዲን ማለት ማን ምን አይነት ሰው እንደሆነ በሚከተለው ሊንክ ገብታችሁ ተመልከቱ : –
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://drive.google.com/file/d/1rRiinpobQ_AUp_CcJXCkzwZYiPvc-YB7/view?usp=drivesdk

     መከረኛ ሙሪዶች ሆይ ይህ ነው ሸይኻችሁ ። ሱብሓነላህ !!! አሁንም ሲያነሱኝ ከአሮጊት ጋር አሁንም ሲያነሱኝ ከአሮጊት ጋር አለ ፎቶ ሲነሳ እድሉ ከአሮጊት ጋር የሆነው ሽማግሌ ። ምነው ሸይኻችሁ ከእነዚህ በኢኽዋንያ ፊክራ የጨረጨሱ አካላት ጋር አደረገው ጓደኝነቱ ? የናንተን ሙሪዶቹን መከራ ለማብዛትና ለኢኽዋኖች ታማኝነቱን ለማሳየት ነው ? ወይስ የናንተን መኖር ከነአካቴው ረስቶት ነው ? እናንተ ዐቅለቢስ መከረኛ ሙሪዶች አሁንስ ሸይኻችሁ ሰለፍይ ነው ? ወይስ ሰለፍይ ማለት ቢዳዓ ነው የደረሳችሁበት የመሟሟት ዝቅጠት ? ነው ወይስ  ሁወ ሰማኩሙል ሙስሊሚን የሚለውን አንቀፅ ያለ አግባብ ተረድተው የሚያቅራሩት  ቀረርቶ አደንቁሮዋችሁ ነው ? አው ካላችሁ የናንተና ቀብር ላይ ተደፍቶ እያለቀሰ እዱኝ ፣ አሽሩኝ ፣ አክብሩኝ ፣ ለምን ተውኝ እያለ የሙታን መንፈስን ከሚያመልከው ጋር አንድ ነው ? ካልሆነ ቀብር አምላኪዮችን ታከፍራላችሁ ማለት ነው ። ጣፋጩ መራራ ነው ከሁለት አንዱን ምረጡ ። እናንተና አቡ በከርን ፣ ዑመርን ፣ ዑስማንን ፣ ዓኢሻንና ሐፍሳን የሚያከፍሩ ሺዓዎች እስልምና አንድ ነው ? አሁንም አንዱን ምረጡ ።
     ዲሞክራሱ ከተከበረ ዲኔ ተከበረልኝ ማለት ነው ። ዒሳም ፍቅርን ያስተማረ ጌታ ነው, ሁሉም ሰማያዊ እምነቶች ፍቅርን ነው ያስተማሩት, ኢትዮዽያ የሸሪዓ ሀገር መሆን አለባት ብሎ ማሰብ በራሱ ወንጀል ነው ብለን ነው የምናምነው,  የፈለገ መውሊድ ያክብር የፈለገ ጫት ይቃም አንተ ምን አገባህ, የሚሉ ኢኽዋኖችና የናንተ እስልምና አንድ ነው ? ሸይኻችሁ አንድ ነን ብሎ አደባባይ ላይ አንድነቱን እያሳየ ነው ። እንደነዚህ አይነት ጥያቄዎች ሰምታችሁ መልሱን እንዳታስቡ ቃል ኪዳን ገብታችሁ ለሸይኻችሁ ቆርባችኋል? 
     አይ የነሲሓ ሙሪዶች ስታሳዝኑ ምነው መከራችሁ በዛ እስኪ የእንቅልፍ ክኒኑ ሀይል አልቆ ከሆነ ወደ አንደኛው ጎናችሁ ለመገልበጥ ሞክራችሁ እዩት !!! ነው ወይስ በድብቅ ካሜራ እይታ ውስጥ ናችሁ የሚል ፁሑፍ አለ ? ለማንኛውም አላህ ይድረስላችሁ ወደ ቅኑ መንገድ ይምራችሁ እንላለን ።
  
https://t.me/bahruteka


Forward from: Bahiru Teka
✅ ሰለፍዮች በትግላችሁ ቀጥሉ

የአላህ መሺኣ ነውና የሐቅና ባጢል ግብግብ እስከ ቂያማ ይቀጥላል ። በዚህም እውነተኛች በጫፍ ላይ ካሉት ይለያሉ ። ነገሮች ሲመቻቹ ሁሉም አማኝ ነው ሁሉም ሱና ወዳጅ ነው ነገር ግን በፈተና ጊዜ ነው እንክርዳዱ ከፍሬው የሚለየው ። የተወሰኑ የአላህ ባሮች እሳት ውስጥ ገብቶ እንደ ወጣ ወርቅ የዲኑ ጌጥ ሲሆኑ አብዛኞች ጎርፍ ያመጣው አረፋ ሆነው ዳር ይቀራሉ ።
የአላህ መልእክተኛ ፈተናን አስመልክተው ሲናገሩ ከኋላ የሚመጣው የፊተኛውን ቀላል ያደርገዋል ብለውናል ። አሁን እያየን ያለነው ይሄው ነው ። ድሮ የኢኽዋን አንጃ በነ ሓሚድ ሙሳ አማካይነት ወደ ሀገራችን ሳይገባ በፊት ሁሉም ወደ ተውሒድና ሱና ሲጣራ ሱፍዮች ካጠቃላይ የተውሒድ ሰዎች ጋር ነበር ትግላቸው ።
የሱናው ወጣት በኢኽዋን አስተሳሰብ መጠለፍ ሲጀምር ሰለፍይና ኢኽዋንይ ተብሎ ተከፈለ ። ሰለፍዮች ከሱፍይና ኢኽዋን ጋር ትግል ጀመሩ ። ብዙም ሳይቆይ ኢኽዋኖች ከሱፍዮች ጋር ተደመሩ በጋራ ሰለፍያን ለመጣል መስራት ጀመሩ ። ሰለፍዮች በጋራ የተከፈተባቸውን ትግል ተቋቁመው ወጣቱን ለማዳን የሞት ሽረት ትግል አደረጉ ። ተሳክቶላቸው የጥምር ሀይሉን መቋቋም ቻሉ ።
በዚህ ሁኔታ እያሉ የአሕባሽ አስተሳሰብ መጥቶ መጅሊሱን ተቆጣጥሮ የአወሊያ ተማሪዮችን ሲያባርር ኢኽዋኖች አጋጣሚውን ተጠቅመው መድረኩን ይዘው ከጫፍ እስከ ጫፍ ፀረ አሕባሽ ንቅናቄ አካሄዱ ።
ከአሽባሽ ጋር የነበረው ፀብ የስልጣን እንጂ የዐቂዳ አልነበረም ። ለዚህ ማስረጃው ኢኽዋን ያደርገው በነበረው ሀገራዊ ሰልፍ መፈክሩ " አሽ ሻዕብ ዩሪድ ኢስቃጠል መጅሊስ " ( ህዝቡ መጅሊስን መጣል ይፈልጋል ) የሚል የነበረ መሆኑ ነው ። በዚህ ንቅናቄ ኢኽዋን ካገኘው ያልጠበቀው ትርፍ አብዛኛው ሱና ሲደግፍ የነበረው ወጣትና ባለሀብት ወደ ትግሉ መቀላቀሉና የሰለፍያን ዳዕዋ ሲመራ የነበረውን ናጂያን መኮነኑ ነበር ። ጊዜው አብዛኛዎች የናጂያ ዱዓቶች አገር ጥለው የተሰደዱበት ወቅት ነበርና ይህ ሁኔታ ዋና ዋና የናጂያ መሪዮች አቋማቸውን እነዲቀይሩ አደረጋቸው ።
የሰለፍያው ዳዕዋ በተለያዩ መሻኢኾችና ዱዓቶች አማካይነት ትግል እያደረገ የነበር ሲሆን በሚዲያው ላይ በነኢብሙነወርና ሳዳት አማካይነት ዳዕዋው መነቃቃት ጀመሮ ከፍተኛ ትግል ይደረግ ነበር ።
በዚህ ጊዜ ትግሉ በዋነኝነት ወደ ኢብኑ መስዑድ ከተዘዋወረው ናጂያ አመራሮች ጋር ነበር ። በዚህም የሰለፍያው ዳዕዋ ትግል ከኢኽዋኖችና ኢብኑ መስዑዶች ጋር ሆነ ። ትግሉ ቀጥሎ የሰለፍያው ዳዕዋ ወጣቱን መልሶ መቆጣጠርና ከተቃራኒዮቹ መዳፍ አብዛኛውን ማውጣት ቻለ ።
ይህ በንዲህ እያለ ስርአቱ ከኢሀዲግ ወደ ብልፅግና ሲሸጋገር የመደመር ስሌት አሕባሽን ፣ ሱፍይን ፣ ኢኽዋንና ወደ ነሲሓ የተዛወረው ኢብኑ መስዑድ ተቋም አመራሮች አንድ ሆነው ወደ መጅሊስ መጡ ። ይህን የድምር ውጤት ያዩት እነኢብኑ ሙነወር መደመሩ ነው የሚያዋጣው ብለው የጥምሩ የእንጀራ ልጆች ሆኑ ። ባለውለታ ለመሆንም ሰለፍዮችን ባለ በሌለ ሀይላቸው መዋጋት ጀመሩ ። እነ ኢብኑ ሙነወር በእስክሪብቶ የጥምሩ መጅሊስ አመራሮች በመሳሪያ አፈሙዝ የሰለፍያ ዳዕዋ መዋጋት ጀመሩ ።
የጥምሩ መጅሊስ አመራሮች ሰለፍዮችን ከዳዕዋው ሜዳ ለማስወጣት መስጂዶችን መረከብ የመጀመሪያው ተግባር አድርገው ያዙት ። ይህ አካሄድ የሰለፍዮችንም መስጂዶች ጭምር መረከብን ያካተተ ነው ። ለዚህ ደግሞ በሰለፍዮች መስጂዶች ላይ ሁከትና ረብሻ በመፍጠር ሰለፍዮች የፈጠሩት በማስመሰል ለጅምላ እስር መንገድ ይከፍታል ብለው ነው ። በአሁኑ ሰአት በስራ ላይ ያዋሉት በስልጤ ዞን ላይ ሲሆን እንደሞመከሪያ ነው እየሰሩት ያሉት ። ሰለፍዮች መርሳት የሌለባቸው ኢብኑ ሙነወር ላይደርሱላችሁ መስጂዳችሁን ያሰነጥቁዋችኋል ማለቱን ነው ። ‼ ይህ ማለት እስትራቴጂውን ያውቀው ነበርና ለመጅሊስ እጅ ስጡ ነበር መልእክቱ ።
ማስገንዘቢያ ለሰለፍዮች :–
ሰለፍዮች ይህን እስትራቴጂ ማስቆም የምትችሉት በዳዕዋ ላይ በመፅናት ነው ። የተዘጋጀላችሁን ወጥመድ ተጠንቀቁ በፍፁም ስሜታዊ እንዳትሆኑ ። ከመስጂድ ቢያስወጡዋችሁ ጊቢ ውስጥ ዳዕዋ አድርጉ, ልጆቻችሁን እቤትችሁ አስተምሩ, አንዱ ዳዒ ሲታሰር ሌላው ይቀጥል ፍፁም ዳዕዋ እንዳታቆሙ, እነርሱ ይሰሩ እናንተ ዳዕዋችሁን ቀጥሉ, ሀይለቃልም ከመጠቀም ተቆጠቡ አብዛኛው ማህበረሰብ እናንተ ዲን ለማጥፋት የመጣችሁ ተደርጎ ስለተሳለለት እዘኑለት ። ትግላችሁ አፈር የለበሰውን ሐቅ አፈሩን ጠርጋችሁ ለማሳየት መሆን አለበት ።
ከአላህ ጋር እውነተኛ ሁኑ አላህ እውነተኞች ይረዳልና አብሽሩ ። ፅናት የትግል ድልድይ ናት ። ትግሉን ለመሻገር ፅኑ ። ለዚህ በሶብር ፣ በኢኽላስና ዱዓእ ታገዙ ። የነብዩ ሱና መርከብ ነውና ከሱ እንዳትወርዱ በቢዳዓ ባሕር እንዳትሰጥሙ ተጠንቀቁ ። ሌላው በፍፁም ዳዕዋ ላናደርግ ብላችሁ እንዳትፈርሙ ያለ ፈቃድ ለሚሉዋችሁ የህገመንግስቱ ፈቃድ በቂያችን ነው በመጅሊስ ደብዳቤ ከተሻረና ዳዕዋ ማድረግ ወንጀል ከሆነ ቅጣቱን ለመቀበል ዝግጁ ነን በሉ ። በሱና መርከብ ላይ ለመሳፈር ቆራጥ መሆን ያስፈልጋል ቆራጥ ያልሆናችሁ አላህ ፊት እንዳታፍሩ ፀንታችሁ ታገሉ ።
አላህ ተውሒድና ሱናን የበላይ ለማድረግ ሰበብ ያድርገን ።

https://t.me/bahruteka

20 last posts shown.