Ministry Of Education


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Education


📚ይህ ትክክለኛው የትምህርት ሚኒስትር የተማሪዎች መረጃ ማቀበያ ገፅ ነው
🔵ከ1-12 መፅሃፍት ለማግኘት: @STBookbot
🔴ለFreshman : @Freshman_Robot
«Buy Ads» @MoeAds_bot or https://telega.io/c/Tmhrt_minister

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Education
Statistics
Posts filter


SAT workbook. 2025.pdf
903.9Kb
📚474 SAT Questions

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister


#Ad

ከLightup ጋር የትምህርት አሰጣጥን መቆጣጠር ፣የተማሪዎችዎን ውጤት መከታተል እና ፈተናዎችን መስጠት በጣም ቀላል ነው።

ትምህርት ቤቶች የLightup ማስተማሪያ ተጠቃሚ ሲሆኑ፣ መምህራኖች ኦንላይን የተማሪን ሂደት መቆጣጠር፣ ፈተናዎችን መስጠት እንዲሁም መልመጃ እና አሳይመንቶችን እዛው ኦንላይን ማካሄድ ይችላሉ።
ትምህርት ቤትዎን ከዘመኑ ጋር ያራምዱት!

Website
🔗 https://Lightup.et

ይደውሉልን!
📞 0987110000

#LightupEthiopia #SmartLearning #Lightup #tutor #OnlineTutoring


#Reminder

የፋይዳ መታወቂያ አውጥተዋል?

በሰኔ 2017 ዓ.ም የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና ለመውሰድ ተፈታኞች የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) ሊያወጡ እንደሚገባ ትምህርት ሚኒስቴር መግለፁ ይታወቃል።

የመንግሥት እና የግል ዩኒቨርሲቲዎች የፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ በማድረግ ላይ ይገኛሉ።

የመውጫ ፈተናውን ለመውሰድ ምዝገባውን በጊዜ በማድረግ የፋይዳ መታወቂያዎን ይያዙ።

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister


ቀሰም_Academy_KINEMATICS_EUEE_2002_2015_&_ADDITIONAL_QUESTIONS.pdf
480.1Kb
📚Physics

📁kinematics EUEE question

Fom 2002-2015


ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister


#AmharaEducationBureau

በአማራ ክልል የ2017 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል የመጀመሪያ ዙር ክልል አቀፍ ፈተና ሰኔ 3 እና 4/2017 ዓ.ም እንዲሁም የ6ኛ ክፍል የመጀመሪያ ዙር ክልል አቀፍ ፈተና ሰኔ 5 እና 6/2017 ዓ.ም ይሰጣል፡፡

የክልሉ ትምህርት ቢሮ ለሁሉም የዞን፣ የከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያዎች በላከው ሰርኩላር፥ የ2017 ዓ.ም የመጀመሪያ ደረጃ (6ኛ ክፍል) እና የመካከለኛ ደረጃ (8ኛ ክፍል) ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና በሁለት ዙር ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጿል፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister


Gr12 New History hanout chapter 1-9(1).pdf
2.7Mb
📁History handout

📚chapter 1-9

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister


#MoE

በሰኔ 2017 የሚሰጠውን የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ዳግም ለመፈተን እየተጠባበቃችሁ ያላችሁ አመልካቾች ምዝገባ ከዛሬ ሚያዝያ 14 /2017 ዓ.ም እስከ ግንቦት 05/2017 ዓ.ም የሚከናወን መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡

የመመዝገቢያ ቅፅ https://exam.ethernet.edu.et ላይ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች በሟሟላት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል፡፡ ፈተናው የሚሰጥበት ቀን ወደፊት ይገለፃል ተብሏል፡፡

ፈተናውን ለመውሰድ የብሔራዊ (ፋይዳ) መታወቂያ መያዝ ግዴታ ሲሆን፤ የአገልግሎት ክፍያ (500 ብር) በቴሌብር በኩል ብቻ የሚፈፀም መሆኑ ተገልጿል፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister




ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለትንሳኤ በአል በሰላም አደረሳችሁ !
መልካም ፋሲካ

ትምህርት ሚኒስቴር


የ129 የፌዴራል መሥሪያ ቤት ሠራተኞች የትምህርት ማስረጃ ሃሰተኛ ሆኖ ተገኘ

የፌዴራል መሥሪያ ቤቶች ላይ በተደረገ ፍተሻ የ129 የፌዴራል መሥሪያ ቤት ሠራተኞች የትምህርት ማስረጃ ሃሰተኛ ሆኖ መገኘቱን ትምህርት ሚኒስቴር ገለጸ።

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የ2017 የበጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት አፈፃፀም ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረበቡት ወቅት እንደተናገሩት ትምህርት ሚኒስቴር የፌዴራል መስሪያ ቤት ሠራተኞችን የትምህርት መረጃ የማጣራት ሥራ እያከናወነ ይገኛል።

በመጀመሪያ ዙር ከ280 የፌዴራልና ተጠሪ ተቋማት መስሪያ ቤቶች ከሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በተላከው መረጃ መሰረት የ32 ሺህ 815 ሰራተኞች የትምህርት ማስረጃ ትክክለኛነት መጣራቱን አብራርተዋል።

በዚህም 129 ሀሰተኛ የትምህርት ማሰረጃ የተገኘ ሲሆን፤ የ469 ሰራተኞች መረጃ ያልተሟላ በመሆኑ ለሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ተመላሽ ተደርጓል ብለዋል።

ከዚህ በኋላ የዲፕሎማ ትምህርት ማረጋገጫ ወረቀት በፌዴራል ትምህርት ሚኒስቴር ታትሞ የሚሰጥ ሲሆን፤ ከዚህ በፊት በዩንቨርሲቲ ሲሰጥ የቆየው ሂደት እንደማይቀጥል ተናግረዋል።

በትምህርት ስርዓቱ ላይ እየዋሉ ያሉ የትምህርት መረጃዎች የተዓማኒነት፣ የወቅታዊነት እና የጥራት ችግር የነበረባቸው በመሆኑ፤ ይህንን ለመቅረፍ አዲስ ዲጂታል የመረጃ ሥርዓት በመላው ሀገሪቱ ተግባራዊ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ገልፀዋል።


ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister


" የ12ኛ ክፍል ፈተና ከአንድ ወር / ከአንድ ወር ተኩል በኃላ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው " - ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር)

የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከአንድ ወር / ከአንድ ወር ተኩል በኃላ እንደሚሰጥ ጠቁመዋል።

ሚኒስትሩ ፥ " ይሄ አራተኛው ነው በአዲሱ የፈተና አሰጣጥ ፈተና የሚሰጥበት " ብለዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር ባለፉት ዓመታት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከትምህርት ቤቶች ወጥቶ ተማሪዎችን ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ አስገብቶ ፈተና እንዲሰጥ እያደረገ መሆኑ ይታወቃል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ስለዘንድሮው የ2017 ዓ/ም ፈተና በተናገሩበት ወቅት 150 ሺህ ተማሪዎች ፈተናቸውን በኦንላይ እንዲወስዱ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

ብርሃኑ (ፕሮፌሰር) ፥ " እንደ ከዚህ ቀደሙ አድካሚ በሆነ ከቦታ ቦታ ልጆችን እያዘዋወሩ ከመሄድ ባለፈው ዓመት 29 ሺህ ተማሪ ነበር ኦንላይን ፈተና የሰጠነው ዘንድሮ ደግሞ 150 ሺህ ተማሪ ኦንላይን ፈተና ለመስጠት እየተዘጋጀን ነው " ብለዋል።

ሚኒስትሩ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበትን ቀን ቆርጠው ባይናገሩም ፈተናው ከአንድ ወር / ከአንድ ወር ተኩል በኃላ እንዲሰጥ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።


ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister


ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ
"እንኳን ለብርሃነ ስቅለቱ በሰላም አደረሳችሁ!!"

ትምህርት ሚኒስቴር



13 last posts shown.