Ministry Of Education


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Education


📚ይህ ትክክለኛው የትምህርት ሚኒስትር የተማሪዎች መረጃ ማቀበያ ገፅ ነው
🔵ከ1-12 መፅሃፍት ለማግኘት: @STBookbot
🔴ለFreshman : @Freshman_Robot
«Buy Ads» @MoeAds_bot or https://telega.io/c/Tmhrt_minister

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Education
Statistics
Posts filter


Forward from: betting
🔴 ሰበር ዜና ዛሬ ትምህርት ሚኒሰትር ያወጣው አዲስ ያልተጠበቀ መግለጫ   ‼️

ሙሉ መግለጫውን ለማንበብ ከስር open ሚለውን ይጫኑ 👇👇


Forward from: Learn English
➡️ እንግሊዝኛን በአንድ ወር ውስጥ አቀላጥፎ ማውራት ይፈልገሉ❔

🗣 አዎን እፈልጋለሁ ካሉ
⭐️ እንግዲያውስ አሪፍ ቻናል ልጋብዛችሁ
❤️ ያለ ምንም ጥርጥር
ትወዱታለችሁ💯

📝 JOIN አድርጉና እንግሊዝኛን በአማርኛ ይማሩ።

✈️ የቻናሉ Link👇
t.me/English_Ethiopian/14946
t.me/English_Ethiopian/14946
t.me/English_Ethiopian/3778


...........ምንም እንቅፋት የለም፣ መማር ብቻ! 🌍

📢 ከፍተኛ ጥራት ያለው የፈተና ዝግጅት ውድ መሆን ወይም ለማግኘት አስቸጋሪ መሆን የለበትም!

eTemari በኢትዮቴሌኮም በኩል በልዩ የመዳረሻ ፓኬጆች መምጣቱ ተመጣጣኝ እና ምቹ ያደርገዋል።

💡 ይህ ለእናንተ ምን ማለት ነው፡-
✔️ ውድ የገንዘብ ወጪ ቀረ - በተመጣጣኝ ዋጋ የጥናት ተደራሽነት!
✔️ ስለ internet ወጪዎች ሳይጨነቁ በማንኛውም ጊዜ እና ቦታ ይማራሉ ።
✔️ ያለምንም ጭንቀት በራስዎ ፍጥነት ይማሩ።

🚀 የወደፊት ህይወትህ በከፍተኛ ወጪ መገደብ የለበትም! ለተማሪ ተስማሚ በሆነ ዋጋ ሙሉ መዳረሻ ያግኙ።

⚡️ልዩ ቅናሾች ለማግኘት ቴሌግራማችንን ይቀላቀሉ!
👉 @etemari_net

⚡በተመጣጣኝ ዋጋ መማር ለመጀመር
👉 ድህረ ገጻችንን ይጎብኙ! ✅😊


#ExitExam

👉የመውጫ ፈተና ያላለፉ ተማሪዎች መረጃ አሰጣጥ


፨ለሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት

ጉዳዩ- የከፍተኛ ትምህርት መውጫ ፈተና ያላለፉ ተማሪዎችን መረጃ አሰጣጥን ይመለከታል!


የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሀገራዊ የቅድመ-ምረቃ መውጫ ፈተና ከሰኔ 2015 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ ተወስኖ የአፈጻጸም መመሪያ ቁጥር 919/2014 ወጥቶ ተግባር ላይ ውሏል፡፡ በዚህ መመሪያ አንቀጽ 12 (12.3) ላይ የመውጫ ፈተና ውጤት በተማሪዎች ሰርተፍኬት (Temporary Degree) ወይም ትራንስክሪፕት ላይ አልፏል (PASS) ወይም ወድቋል (FAIL) በሚል እንዲቀመጥ እና ከዚህ ደብዳቤ ጋር አባሪ በተደረገው ሰርተፍኬት ፎርማት መሠረት እንዲፈጸም እናሳውቃለን፡፡ (ትምህርት ሚኒስቴር)

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister


@Tmhrt_Minister G-12 BIOLOGY THE NERVOUS SYSTEM.pdf
1.5Mb
@Tmhrt_Minister G-12 BIOLOGY, UNIT 6 CLIMATE CHANGE.pdf
1.1Mb
📚Biology Grade 12 😊 ምርጥ PPT ( Shorte Note ) ለፈተና ዝግጅት

📁Unit 5 Nervous System
📁Unit 6 Climate Change

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister


" 10ኛ ክፍል ላይ ሀገር አቀፍ ፈተና ሳይወስዱ ወደ 11 የተዘዋወሩ ተማሪዎች ልዩ የማካካሻ ትምህርት ሊሰጣቸው ይገባል፣ ካልሆነ ግን መውደቅ ይቀጥላል  " - ትምህርት ሚኒስቴር

ትምህርት ሚኒስቴር ወደ ዩኒቨርስቲ የሚገቡ ተማሪዎች ቁጥር በየጊዜው በከፍተኛ ሁኔታ እየቀነሰ መሆኑን ተከትሎ አካሄድኩት ባለው እና ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረበው ጥናት ዘርፈ ብዙ ችግሮች መገኘታቸውን ገልጿል።

የትምህርት ዘርፍ ሪፎርም ከተካሄደ በኋላ ትምህርት ቤቶች ማስተማር ከሚችሉት በላይ ተማሪዎችን ያስተምራሉ ያለ ሲሆን ከዚህ በፊት 10ኛ ክፍል ይሰጥ የነበረውን ፈተና በመቅረቱ ሳይፈተኑ 11ኛ ክፍል መግባታቸው ለችግሩ ዋና ተጠቃሽ ምክንያት መሆኑን አመላክቷል።

በትምህርት ቤቶች በሚሰጠው የሞዴል ፈተና እና ትምህርት ሚኒስቴር በሚሰጠው የሀገር አቀፍ ፈተና ሰፊ ልዩነት እንዳለውም ገልጿል።

" በማህበራዊ እና በተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች መካከል የማለፍ ንፅፅር ሲታይ ልዩነት አለ " ያለው ሚኒስቴሩ " የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የተሻለ ውጤት በማምጣት ወደ ከፍተኛ ተቋም ይገባሉ፣ ይሁን እንጂ በቂ አይደለም፣ ብዙ ነገሮች መሻሻል እንዳለባቸው ጥናቱ አሳይቶናል " ብሏል።

ጥናቱ ምን አይነት የትምህርት ዘርፍ ችግር ነው ይሄን ያክል ውድቀት ያመጣብን ፣ ከተማሪዎች መውደቅ እና ማለፍ ጋር ተያይዞ የትምህርቱ ባህሪ ምንድን ነው የሚለውን እና በአጠቃላይ በትምህርት ዘርፉ ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን የያዘ ነው።

በሁሉም የትምህርት ዘርፍ ላይ ያሉ ችግሮችን ያሳየው ይሄ ጥናት በመጨረሻም የመፍትሄ ሃሳቦችንም አቅርቧል።


ትምህርት ሚኒስቴር ምን የመፍትሄ ሃሳብ አቀረበ ?

" ከዚህ በፊት 10ኛ ክፍል ላይ ይሰጥ የነበረውን ሀገራዊ ፈተና ሳይወስዱ 11ኛ ክፍል የሚማሩ ተማሪዎች ልዩ የማካካሻ ፕሮግራም ያስፈልጋቸዋል። ይሄ ካልሆነ ግን መውደቅ ይቀጥላል ፣ ምክንያቱ የሚፈለገውን ያህል እውቀት እና ክህሎት ይዘው አይወጡም።

በገጠር በተለይም በአርብቶ አደሮች አካባቢዎች ላይ ያለው የትምህርት ዘርፍ ልማት አነስተኛ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ እጅግ ወደ ኋላ እየቀረ ስለሆነ ማካካሻ መሰራት አለበት።

ሌላው ደግሞ ከትምህርት አመራር፣ መምህራን እና ከአቅም ግንባታ ጋር ተያይዞ ያሉ ጉዳዮች ውጤት በሚያመጡ ጉዳዮች  ላይ ብቻ ትኩረት ተደረጎ የትምህርት አመራሩ አቅም እስካልሰጠ ችግሮቹ ይቀጥላሉ።

ለመምህራን የደመወዝ ጭማሪ ብቻ ሳይሆን መምህሮችን የሚያቅፍ የ insensitive package እስካልመጣ ድረስ ችግሮቹ ይባባሳሉ።

በተጨማሪም በሀብት ክፍፍል ላይ ክፍተት በመኖሩ በትምህርት ዘርፉ ልማት ላይ ተግዳሮት መኖሩን ያሳያል፣ ይሄም መፈታት አለበት
" ሲል መፍትሄ ያለውን ሃሳብ አቅርቧል።

ትምህርት ሚኒስቴር ጥናቱን ባቀረበበት ወቅት የህዝብ ተወካዮች የተለያዩ አስተያየቶች፣ ጥያቄዎች እና ሃሳቦችን አቅርበዋል።

በጥናቱ ላይ የመፍትሄ ሃሳቦች መቅረባቸው ጥሩ ሁነው ሳለ እንደዚሁ ተወርተው መሬት ላይ ሳይወርዱ ከቀሩ ትርጉም አልባ ናቸው፣ በመሆኑም ሁሉም በአፅንኦት ሊመለከተው እንደሚገባ በተወካዮች ተጠቁሟል።

ከ1 እስከ 8ኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች የሚደረገው ድጋፍ አነስተኛ ነው፣ ይሄም አሁን ላለንበት ውጤት ማጣት ትልቁን ድርሻ ይወስዳል ፤ በጥናቱስ ላይ ለምን ይሄ ሳይካተት ቀረ፣ ምክንያቱም የትምህርት መሰረቱ ከታች ጀምሮ ስለሆነ የሚሉ ጥያቄዎች ተነስቷል።

የተለያዩ ተማሪዎች በህገወጥ መንገድ ወደተለያዩ ሀገሮች እየተሰደዱ ነው፣ ተማሪዎች ይሄ ሲፈጠር ተረጋግተው መማር እየቻሉ አይደለም፣ ትምህርት ሚኒስቴር ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ተብሏል።

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister




#MoE

የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከመመረቃቸው በፊት ለአንድ ዓመት  እንዲያስተምሩ ሊገደዱ ነው።

ትምህርት ሚኒስቴር የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከመመረቃቸው በፊት ማኅበረሰቡን ለአንድ ዓመት በቅድሚያ እንዲያስተምሩ ወይም እንዲያገለግሉ የሚያደርግ አሰራር ተግባራዊ ለማድረግ ዕቅድ መያዙን አስታወቀ።

ትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) ዛሬ መጋቢት 24 ቀን 2017 ዓ.ም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፣ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና የተማሪዎች ውጤት ዝቅተኛ የሆነበትን መንስዔ በተመለከተ ጥናት አቅርበዋል።

ውይይት ሲደረግ ነበር።

በዚህም ወቅት በዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ላይ ስለተያዘው እቅድ አብራርተዋል።

ላለፉት ዓመታት (እሳቸው  በኃላፊነት ከተሾሙ ጀምሮ) ፣ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና የተማሪዎች ውጤት በከፍተኛ ደረጃ ዝቅተኛ  እንዲሆን ካደረጉ መንስዔዎች መካከል፣ የመምህራን ብቃትና የተነሳሽነት ማነስ ተጠቃሽ መሆናቸው ጠቁመዋል።

ችግሩን በአጭር ጊዜ ለመፍታት እንዲቻል የተለያዩ ተግበራት እየተሰሩ መሆኑን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።

'' የኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲ ሰርቪስ '' የሚል መጠሪያ የተሰጠው አሠራር ከ2019 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ ዕቅድ የተያዘ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፣ " በአራት ዓመት የሚመረቅ ተማሪ፣ የሦስተኛ ዓመት ትምህርቱን እንዳጠናቀቀ ወደ አስተማረው ማኅበረሰበብ ተመልሶ ለአንድ ዓመት የማስተማር አገልግሎት ይሰጥና (ማኅበረሰቡን እንዲያገለግል ይደረግና) እንዲመረቅ ይደረጋል " ሲሉ ተናግረዋል።

ይህም ሲሆን የተማሪዎቹ መሠረታዊ ወጪ የሚሸፈን እንደሚሆንም አክለዋል።

ይህ አሰራር ለተማሪዎች ለራሳቸው የተግባር ትምህርት እንደሚሆንና የበለጠ እንዲበስሉ እንደሚያደርጋቸውም ተናግረዋል።

ተማሪዎች የመምህርነትን ሙያ ተላብሰው በዚያው ወደ ሙያው እንዲያመሩ ዕድል በመፍጠር ለጊዜውም ቢሆን በዘርፉ እየቀነሰ የመጣውን ወደ ሙያው የሚገባ የአስተማሪን ቁጥር ለማሳግ እንደሚረዳም ሚንስትሩ አብራርተዋል።

በቅርቡ በመምህራን ላይ በተደረገ ግምገማ ፣ 100,000 የሚደርስ የመምህራን ዕጥረት መኖሩ መታወቁን የተናገሩት ብርሃኑ (ፕሮፌሰር)፣ አሰራሩ በከፍተኛ ደረጃ ያለውን የመምህራን ዕጥረት እንዲቀንስ የበኩልን እንደሚወጣ አስረድተዋል።

ወደ መምህርነት ሙያ የሚገቡ ሰዎችን ክፍተት ለማስተካከል ከተያዙ ዘርፈ ብዙ የማትጊያ ሥርዓቶች አንዱ፣ መምህራን በአገሪቱ የፋይናንስ ሥርዓት ውስጥ የራሳቸው ድርሻ እንዲኖራቸውና የኑሮ ውድነቱን እንዲቋቋሙ ለማድረግ፣ " የመምህራን ባንክ " ማቋቋም አንዱ እቅድ መሆኑን አንስተዋል።

ባንኩ " በአንድ ዓመት ውስጥ ወደ ሥራ ይገባዋል ብለን እንጠብቃለን " ያሉት ሚኒስትሩ፣ በ2019 ዓ.ም ደግም በእርግጠኝነት ወደ የኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲ ሰርቪስ አሰራር እንደሚገባ ጠቁመዋል።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሪፖርተር ጋዜጣ ነው።

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
🎙የፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ንግግር

ከተቻለ በሚቀጥለው ዓመት ካልሆነም በ2019 ዓ.ም. የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከመመረቃቸው በፊት ለአንድ ዓመት የተማሩበትን ማህበረሰብ እንዲያስተምሩ ለማድረግ እየተሰራ ነው።

፨ይህ አዲስ አሰራር ተግባራዊ መደረግ ሲጀምር ለምሳሌ አምስት ዓመት የሚማር የምህንድስና ተማሪ የአራተኛ ዓመት ትምህርቱን ሲጨርስ ለአንድ ዓመት የተማረበትን ማህበረሰብ እንዲያስተምሩ ይደረግና በቀጣዩ ዓመት አምስተኛ ዓመት ትምህርቱን ይቀጥላል። ከዚያም ይመረቃል።

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister


#TVTI

በፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ውስጥ የፋሽን ስልጠና ማዕከል ሊከፈት ነው።

የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር (ዶ/ር) ከማፊ ፋሽን አካዳሚ ባለቤት ዲዛይነር ማህሌት አፈወርቅ (ማፊ) ጋር በኢንስቲትዩቱ ውስጥ የፋሽን ስልጠና ማዕከል ለመክፈት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።

የፋሽን ማሰልጠኛ ማዕከሉ የአጭር እና የረጅም ጊዜ ስልጠናዎችን እንደሚሰጥ ተገልጿል፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister


የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የኮሎምቢያ አምባሳደር ጋር ተወያዩ።
------------------//--------------------------
(መጋቢት 23/2017 ዓ.ም) የትምህርት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የኮሎምቢያ አምባሳደር ዬሶን አርካዲዮ ሜኔስ ኮፕቴን በጽ/ ቤታቸው በመቀበል ውይይት አድርገዋል።

በውይይታቸውም ሁለቱ አገራት በትምህርቱ ዘርፍ በትብብር መስራት የሚችሉባቸውን ጉዳዮች አንስተው ተወያይተዋል።

በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የኮሎምቢያ አምባሳደር በጽ/ቤታቸው ተቀብለው በማነጋገራቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸው በትምህርቱ ዘርፍ በትብብር ለመስራት የሚያስችሉ ጉዳዮችን ለአምባሳደሩ አንስተውላቸዋል።

በተለይም በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ በተማሪዎች ነጻ የትምህርት እድል፣ በሙዚቃና ባህል ልውውጥ እንዲሁም በሌሎች ጉዳዮች በትብብር መስራት እንደሚቻልም አብራርተዋል።

በኢትዮጵያ የኮሎምቢያ አምባሳደር ዬሶን አርካዲዮ ሜኔስ ኮፕቴ በበኩላቸው ኮሎምቢያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር ኤምባሲዋን በአዲስ አበባ መክፈቷን ገልጸው በትምህርቱ ዘርፍም ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር መስራት እንደምትፈልግ ተናግረዋል።

አክለውም በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ነጻ የትምህርት እድልና የባለሙያ ልውውጥ፣ በከፍተኛ ትምህርት የሰላም ግንባታ እንዲሁም በሙዚቃና ባህል ልምድ ልውውጥ በማድረግ ረገድ በትብብር መስራት እንደሚፈልጉም አንስተዋል።

ሁለቱ አካላት በቀጣይ በሚኖራቸው ግንኙነቶች በትምህርቱ ዘርፍ የሚደረጉ የጋራ ትብብሮችን አጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር

https://t.me/Tmhrt_Minister


ተማሪዎች ሁሉ የግድ ሊኖራቸዉ የሚገቡ ምርጥ ቻናሎች እነሆ 😊 ፦

1. Ministry Of Education 📚

2. MOE Library 📚

3. Matric Fetena 📚

4. Freshman Journey 📚

Bonus +

5. 𝚙𝚒𝚗𝚝𝚎𝚛𝚎𝚜𝚝 ᴇᴛ 🌁


@Tmhrt_Minister BIOLOGY QUESTION BANK.pdf
2.2Mb
📚 Biology Question Bank

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister


Maths Grade 9 and 10 Worksheet 2016.pdf
2.2Mb
📚Maths Grade 9 and 10 Worksheet 2016

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister


💫እንኳን ለ1446ኛው የዒድ አልፈጥር በአል በሰላም አደረሳችሁ።
                
የመላው የእስልምና እምነት ተከታይ ወገኖቻችን እንኳን ለ1446ኛው የዒድ በአል በሰላም አደረሳችሁ።

          ዒድ ሙባረክ!!!


የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና ለመውሰድ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ቅደመ ሁኔታ ሆነ
****

ከሰኔ 2017 ዓ.ም ጀምሮ የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና ለመውሰድ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ቅደመ ሁኔታ መቀመጡ ተገልጿል።

የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ በሁሉም የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እንደሚመቻችም ነው ተቋሙ ያስታወቀው።

የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የተማሪዎችን እና የሰራተኞችን መረጃ በተደራጀ መልኩ ለመያዝና ከከፍተኛ ትምህርት መረጃ አገልግሎት ጋር በማስተሳሰር ጥራት ያለው መረጃ ለማግኘት እና የሚሰጡ ሀገር ሀቀፍ ፈተናዎችን ደህንነት ለመጠበቅ ይረዳል።

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister


@Tmhrt_Minister_Reproduction_Notes_and_MCQ_2017_for_grade_9.pdf
1.1Mb
📚Reproduction Notes and MCQ

📁For grade 9 (2017 E.C)

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister

15k 0 39 2 15



#RemedialExam

የ2017 ትምህርት ዘመን የሪሚዲያል ተማሪዎች ከማዕከል የሚሰጥ ፈተና ከግንቦት 26-30/2017 ዓ.ም እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡

በሚኒስቴሩ የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ሥራ አስፈጻሚ ኤባ ሜጄና (ዶ/ር) በቀን መጋቢት 15/2017 ተፈርሞ ለሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች እና ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በጻፉት ሰርኩላር፤ የ2017 ዓ.ም የሪሚዲያል ተማሪዎች የማጠቃለያ ግምገማ ከ100% ከማዕከል እንደሚሆን አስታውሰዋል፡፡

የሪሚዲያል ተማሪዎች ከዚህ በፊት 70% በማዕከል እና 30% በተቋማት የሚዘጋጁ ምዘናዎችን ይወስዱ የነበረ ሲሆን፤ ከ2017 የትምህርት ዘመን ጀምሮ የሪሚዲያል ተማሪዎች የማጠቃለያ ምዘና ከ100% ከማዕከል እንዲሰጥ በጥቅምት 2017 ዓ.ም መወሰኑ ይታወሳል፡፡

በዚህም የ2017 ዓ.ም የሪሚዲያል ተማሪዎች በሚማሩበት ተቋም የሚሰጥ የተከታታይና የማጠቃለያ ፈተና ውጤት ለትምህርት ሚኒስቴር የሚላክ ይሆናል፡፡ ከዛም በማዕከል በሚሰጥ ፈተና የተማሪዎቹ መቀጠል እና አለመቀጠል የሚወሰን ይሆናል፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister

24.1k 0 135 20 93

#NGAT_Result

ሀገር አቀፍ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ውጤት ተለቋል።

በ2017 ዓ.ም የድኅረ-ምረቃ ትምህርት ለመከታተል የተመዘገቡ አመልካቾች ፈተና መጋቢት 12/2017 ዓ.ም መሠጠቱ ይታወቃል።

https//:result.ethernet.edu.et ላይ በመግባት NGAT የሚለውን በመምረጥና የራስዎን User Name በማስገባት ውጤትዎን መመልከት ይችላሉ።

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister

20 last posts shown.