ደብረ ዘይት ሚዲያ


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Religion


ቤተክርስቲያን ሆይ ብረሳሽ ቀኜ ትርሳኝ ።

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Religion
Statistics
Posts filter


ብጹዕ አባታችን አቡነ ገብርኤል የይቅርታ መግለጫቸውን በፍቅር ተመለከትኩ

ያረሙት ያላስተካከሉትና ያዙኑበት እውነታ

1ያረሙት

እመቤታችን ቤዛ አትባልም ባሉበት አንደበት እመቤታችን የልጇም ቤዛናት ።ቤዛ ኩሉ ዓለም እያልናት ኑረናል ።በሰዓታት ጸሎታችንም ቤዛ ኩሉ ዓለም እናላታለን። እመቤታችን ጥንተ አብሶ የለባትም። ማለታቸው በትክክል የታረመ የተመለሰ ንግግር ነው።

2 ያላስተካከሉት

ብሳሳትም እኔን መምከር ማናገር ሲቻል ዐውዱን በማጣምም ሚድያ ላይ ዘመቱብኝ ማለታቸው ነው።

ብጹዕ አባታችን ያስተማሩት በዐደባባይ ባይሆን በሊቃውንት ፊት በተደረገ ክርክር ብቻ ጠቅሰውት ቢሆን ለብጹዕነታቸው በሚቀርቡ አባቶች በግል መልስ ይሰጧቸው ነበር እንጅ
ያነሷቸው ነጥቦችን በሚድያ ማስተጋባት የሚፈልግ በፍጹም አልነበረም።

እኔ በግሌ እና የወላጅ እናታቸው የቀቢር ሥነሥርዓት ላይ ባስተማሩት ቃል ልቤ ተገዝቶ ሰሚት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ላይም ነገረ ድኅነትን ሲያስተምሩ ተመልክቸ ተስፋ የማደርግባቸው ልቤ ከሚያርፍባቸው አባቶቸ አንዱን አገኘሁ ብየ ነበር እንጅ በፍጹም ብጹዕነታቸውን ለማረም የሚፈልግ ልብ አልነበረኝም።

3 ቃሉን ከዐውዱ ውጭ በመተርጎም ዘመቱብኝ ላሉት

ቃሉን ከዐውዱ ውጭ የተረጎመ የቤተክርስቲያን መምህር አላየሁም ።ከዐውዱ ውጭ የተረጎመ ካለም ስሕተት ስለሆነ በቤተክርስቲያን ሥርዓት ያስጠይቃልና ከተርጓሚያኑ ዘንድ ይኼን አልተመለከትንም


ነገር ግን ብጹዕነታቸው አትግጡ እመቤታችን ቤዛ ኩሉ ዓለም አትባልም ብለው በድፍረት ከመጥቀስ እመቤታችን ቤዛ ኩሉ ብትባልም የርሱን ቤዛነት አትወክልም በማለት ቀደመው በትክክል ቢያስተምሩ (ድንግል ማርያምን ሳያነሱ ጨረሰውት ቢሆን

በክረስቶስ ፍጹም ቤዛነት የሚጠራጠር ኅሊና አልነበረንምና እንደለመደው በአንክሮ ተከታትለን ቃለሕይወት ያሰማልን በማለት ቃሉን እናደምጥ ነበር።

4 እርሳቸው ያዘኑበት እውነታ

በነገረማርያም ትምህርት ላይ ባስተማሩት የስሕተት ቃልብቻ መጠየቅ እየተቻለ የኮታ ጵጵስና የብልጽግና ካድሪ በሚሉ ጭፍን ተቃውሞ የኋላ ታሪክ ጎተታዎች ባንድ በኩል ሲሰለፉ በሌላ በኩል ደግሞ ቢሳሳቱም የኛ ናቸው አባታችን አትንኳቸው የሚሉ ጭፍን ደጋፊዎች መካከል የተፈጠረው ንትርክ ከአግባብ ውጭ ነበርና ለወደፊቱ ልንማርበት ይገባል።

ተራ ስድቦችና ብሽሽቆች ትልቁን የቤተክርስቲያን ጥያቄም የመሸፈን እድል ስላላቸው ጥንቃቄ ያስፈልገዋል።

የብጹዓን አባቶች አሿሿም ጉዳይ ከተነሳም ከብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ዘመን ጀምሮ ሲያጨቃጭቅ የኖረ መንፈስ ቅዱስ በተዘዋዋሪ ሥራውን እንሚሰራ ብናምንም። በመንግሥታት ጣልቃ ገብነት በተቃዋሚነትና በሔር እሳቤ እየተከናወነ የመጣ ሲሆን የብጹዕ አቡነ ገብርኤል ጵጵስና ከዚህ የተለየ አልነበረምና ብቻቸውን አያስከስስም።

በመጨረሻ

2በአግባቡ ያረሙ ያቃኑና ያስተካከሉ ምእመናንን ያስተማሩ ሊቃውንት ነገም ተመሳሳይ ችግር ሲፈጠር እርማት መስጠታቸው የአገልግሎት ግዴታቸው በመሆኑ ሊከሰሱና ሊወቀሱ አይገባም።
ምእመናንም ለሃይማኖታቸው መንፈሳዊ ቅናት ያሳዩበት መንገድ እጅግ ሊመሰገን ይገባዋል።

ስለብጹዕ አባታችን የይቅርታ ቃልቋሚ ሲኖዶስ የሚለውን በአክብሮት እንጠብቃለን።

መምህር ኤፍሬም ተስፋዬ








ሆሳዕና በደብራችን በደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ቡሌ ሆራ (ሀ/ማርያም










በነፍሳችሁ ጨው ይኑርባችሁ፥ እርስ በርሳችሁም ተስማሙ" ማር 9 : 50፡፡

☞ጨው የተባሉ፦
1. ክርስቶስ
2.ቅዱሳን (እመቤታችን ፤ መላእክት ፣ ጻድቃን ሰማዕታት....)
3. ሐዋርያት (ካህናት)

4. ምእመናን ናቸው፡፡

➊ ጨው ምግብ ያጣፍጣል፦ የጨው ዋና ጠባይ ራሱ የሚበላ ሳይሆን ሌሎች ምግቦች በእርሱ አጣፋጭነት እንዲበሉ እንዲፈለጉ እንዲወደዱ ማድረግ ነው (በጨው ደንደስ በርበሬ ተወደስ፦ እንዲሉ አበው፡፡)፤

• 👉ክርስቶስም ጻድቅሆኖ ሳለ ለእራሱ ጽድቅ ሳይሆን ለእኛ ጽድቅ በኃጢአታችን ሞቶ የእኛን ሕይወት አጣፍጦታል፡፡
(ፄው ዘአጥዐሞ ለልሱሕ)
• ጨው ሲያጣፍጥ ሟሙቶ ነው ጌታችንም ሊያጣፍጠን በመስቀል ድቅቅ ብሎ ነው (ኢሳ 53 ፥5 ስለ በደላችን ደቀቀ)፡፡
👉ቅዱሳንም ተጋድለው ተንከራተው ነው

• ካህናትም በምእመናን ሕይወት ውስጥ ሟሙተው ሕይወታችንን ያጣፍጣሉ

• ምእመናንንም በሌሎች ሰዎች ሕይወት የበጎ አርአያ ሆነው፤ በምጽዋትና በጾም በበጎ ምግባር ሟሙተው የሌሎችን ሕይወት ያጣፍጣሉ

➋ጨው ከሁለት ኢለመንቶች (Elements, Sodium Na እና Chlorine Cl) የተሠራ ውሕድ ነው 👉(Table salt)
• ♥ክርስቶስም ከሁለት አካል እንድ አካል፤ ከሁለት ባህርይ አንድ ባህርይ መሆኑን ያመለክታል፤ ይህም ማለት የቃልና የሥጋ ተዋሕዶ ማለት ነው (ዮሐ 1፡14)፡፡
👉ቅዱሳንም ከሥጋ ከመንፈስ ናቸው

• ካህናትም የሁለት ነገሮች ተዋሕዶ ናቸው ፦ የሥጋና የነፍስ ፤ የውኃና የመንፈስ፤የክርስትናና የክህነት ውጤቶች ናቸው
• ምእመናንም ክህነት ባይኖራቸውም ከእናት ከአባት ፤ "ከውሃና ከመንፈስ" የተወለዱ ናቸው፡፡

➌ጨው ርካሽ ነው፦ በቀላል ዋጋ ይገኛል፦
• ♥ክርስቶስም ያለ ዋጋ ተገኝቶልናል፤ ለፍቅሩ ለቸርነቱ የምንከፍለው ምንም የለንም፤ ለመክፈልም ዓቅሙ የለንም፡፡

👉የቅዱሳን ቃል ኪዳንም እንዲሁ ነው ....አይከፈልም
..... ለቅዱሳንም ሳንከፍላቸው ይማልዱልናል

• ካህናት ያለ ዋጋ ይገኛሉ፤ ለቡራኬያቸው አንከፍልም፤ ለጸሎታቸው አንከፍልም፤ ለቅዳሴው ለማኅሌቱ አንከፍልም...በነጻ!

• ምእመናን ሲመጸውቱ ፤ ሲረዱ፣ የታመመና የታሰረ ሲጠይቁ አይከፈላቸውም...ደግ ሆነው ግን በነጻ ያለ ዋጋ ደግ ሆነው ይኖራሉ፡፡

➍ጨው ምግብ እንዳይበላሽ መጠበቂያ (Preservative) ነው፡፡
• ♥ክርስቶስም በኃጢአትና በበደል ከርፍተን ሸተን የነበርነውን የሁላችንን ክፉ ሽታ በመስቀል ጠርቆ አስወግዶ እንዳንበላሽ እንደገና ሠርቶናል፤ ወደፊትም እንዳንበድል በመስቀሉ/በመከራው በውስጣችን ይኖራል፤ መከራ መስቀሉ ይመዘምዘናል፡፡

👉ቅዱሳንም ሕይወታችን እንዳይበላሽ በአርአያነታቸው ይጠብቁናል

• ካህናትም በኃጢአት ውስጥ ሆነን እንዳንበላሽ በንስሐ ይጠብቁናል፡፡
• ምእመናን ሌሎችን መክረው ፤ በንስሐ ለሌሎች ምሳሌ ሆነው ሌሎችን እንዳይበላሹ ወደ በጎ ምግባር ይመልሳሉ፡፡

➎ጨው ፈውስ/መድኃኒት ነው፤ ቁስል ያደርቃል፡
• ♥ክርስቶስም መድኃኒታችን ነው፤ በመስቀል ስለ እኛ ቆስሎ የእኛን ቁስል አድርቆ ፈውሶናል (ኢሳ 53) ፡፡
👉ቅዱሳንም በምልጃቸው በቃል ኪዳናቸው ከእግዚአብሔር ጋር ያስታርቁናል
• ካህናትም በምክር በአገልግሎት በማስታረቅ በንስሐ መድኃኒት ሆነው ወደ እግዚአብሔር ያቀርቡናል፡፡
• ምእመናን በሕይወታቸው፤ በደግነታቸው፤ በምጽዋታቸውና በጾማቸው ሌሎችን ኢአማንያንን ጭምር ይፈውሳሉ ፡፡

☞"ጨው መልካም ነው፤ ጨው ግን አልጫ ቢሆን በምን ታጣፍጡታላችሁ? በነፍሳችሁ ጨው ይኑርባችሁ፥ እርስ በርሳችሁም ተስማሙ" ማር 9 : 50፡፡

ጨው ሆነን አልጫ የሆነውን ዓለም ለማጣፈጥ ያብቃን🙏

መጋቤ ሐዲስ ነቅዐጥበብ ከፍያለው

ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, Subscribe እና Share ያድርጉ :-
ዩቱብ
https://www.youtube.com/@12Samual

ቴሌግራም
https://t.me/tsidq

tiktok
https://vm.tiktok.com/ZMBYPbBMJ/




ቸር አገልጋይ ማነው✞

ቸር አገልጋይ ማነው ለንጉሥ የታመነ
መክሊቱን ያልቀበረ አትርፎ የከበረ (፪)

ባለ አምስቱ መክሊት መልካም ያደረገው
በመውጣት በመውረድ አትርፎ መጥቶ ነው
በጥቂቱ ታምኖ በብዙ የተሾመው
ባለ አምስቱ መክሊት ሊቀ ጳጳሱ ነው
አዝ= = = = =
ሳይሰለች የተጋ ባለሁለት መክሊት
የታመነ እረኛ በፍቅርና በእምነት
ግባ የተባለው ወደ ጌታው ደስታ
አጥምቆ ያቆርባል ካህኑ የጌታ
አዝ= = = = =
ለሚበልጠው ጸጋ ተጠርቶ የነበረ
መክሊቱን ደብቆ ቆፍሮ የቀበረ
ሰነፍ ባርያ ተብሎ ወደ ፍርድ ተጣለ
ማኔ ቴቄል ፋሬስ በአምላክ ፊት ቀለለ
አዝ= = = = =
ፈቃድህን ማድረግ ነፍሱ ለምትወደው
ወንጌልህን መግለፅ የየዕለት ግብሩ ነው
ህግህ ለዘለላም ተጽፎ ይኖራል
በታላቅ ጉባኤ ጽድቅህ ይነገራል

መዝሙር
ዲያቆን ቀዳሜጸጋ ዮሐንስ

ማቴ፳፭፥፲፬-፴፩






ሐዋ 4-12 መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና።


ዮሐ 8-12 ደግሞም ኢየሱስ፡— እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ፤ የሚከተለኝ የሕይወት ብርሃን ይሆንለታል እንጂ በጨለማ አይመላለስም ብሎ ተናገራቸው።




* ከንብ ጋራ ኑሮ****
       ** በዳንኤል ክብረት*
      ትዳር ከንብ ጋር መኖር ነው።ንብ ሁለት ጠባይ አላት።አንዱ ያስደስታል ሌላኛው ያስከፋል አንዱ ጤና ይሆናል ሌላኛው ግን ያማል አንዱ ይጣፍጣል ሌላው ግን ይመራል።አንዱን ይቆርጡታል ሌላውን ግን ይከላከሉታል።ትዳርም እንዲሁ ነው።ሁለት ጠባይ አለው አንደኛው ያስቃል አንዱ ያሳቅቃል አንዱ ያስደስታል ሌላው ያሳዝናል።አንዱ ግቡ ግቡ ሌላው ውጡ ውጡ ያሰኛል።አንዱ ይናደፋል አንዱ ይጣፍጣል አንዱ ጤና ሌላው ህመም ይሰጣል።አንደኛው ግን ያለ ሌላው አይገኝም።ይኼን ለመድሀኒት ለብርዝ ለጠጅ የምናደርገውን ማር የምትሰጠው ንብ ናት የምትናደፈው።ያቺ ስትናደፍ ፊት የምታሳብጠው ውስጥን የምትመርዘው የምትጠዘጥዘው ንብ ናት ማሩን የምትሰጠው።በትዳርም ውስጥ ሁለቱም አሉ።ጭቅጭቁ ንዝንዙ ጠቡ ኩርፊያው አንዱ ለሌላው የግድ መታዘዙ አንዱ የሌላው አገልጋይ መሆኑ አንዱ ያለ ሌላው ለመወሰን አለመቻሉ የሌላውን ጠባይ የሌላውን ዐመል የግድ መታገሱ ከሚታገሱት ሰው ጋር አብሮ መኖሩ ይኼ ነው የንቧ ንድፊያ።
     ትዳር ከንብ ጋር መኖር ነው።ለማሩ ስንል ንድፊያውን መታገስ ቆይተህ ደግሞ ንድፊያውን መልመድ።ገበሬ ቀፎ ሰቅሎ ንብ ሲያንብ ንብ እንደምትናደፍ ሳያውቅ ቀርቶ አይደለም።የማትናደፍ ንብ ከፈለገ በየደጁ ቆሻሻ ፍለጋ የምትጓዝው ዝንብ ነበረችለት።ዝንብ ምን ጠባይዋ ሸጋ ቢሆን ጠብ የሚላት ግን ሌላ ነገር ነው።ይህን ያውቃል ገበሬው።እያወቀም ንብ ያንባል።ማነብ ብቻ ሳይሆን ከንብ ጋር እንዴት መኖር እንደሚችልም ያውቃል።ንብ ትናደፍለች ግን እንዳትናደፍ ማድረግ ይቻላል።የምትወደውና የማትወደው ሽታ አለ ስትቀርብህ ምን ማድረግ እና  ምን አለማድረግ እንዳለብህ ገበሬው ያውቃል።
   ትዳርም እንዲህ ነው።አኗኗሩን ነው ማወቅ የንቧን ንድፈያ የመቀነሻውን መንገድ ነው ማወቅ የማሩን አቆራረጥ መንገድ ነው ማወቅ።ደግሞምኮ አስገራሚው ገበሬው የሚንከባከበው ይህቺኑ የምትናደፈውን ንብ መሆኑ ነው።የምትቀስመው አበባ ትፈልጋለች ንፁህ አካባቢ ትፈልጋለች ከጉንዳንና ከአውሬ ነፃ የሆነ ቀፎ ትፈልጋለች።ግን ትናደፋለች ደግሞም ማር ትሰጣለች።
    ትዳር አስደሳች ነገር ብቻ ሳይሆን አስመራሪ አንገብጋቢ አስጠሊታ ጨጓራ አንዳጁ አንጀት ቆራጭ ልብ አቃጣይ ክፍል ሊኖረው ይችላል ይናደፋል ግን ደግሞ ክብካቤም ይፈልጋል።ንፁህ ልብ ታማኝ ህሊና ቻይ አንጀት ታጋሽ ሆድ ጠቢብ አእምሮ ቀና መንፈስ አሳላፊ ልቡና ይፈልጋል።ለምን ቢሉ? ማር ይሰጣልና።
    አንዳንዶች ቤት ካለችው ወይም ካለው ንብ ይልቅ ውጭ ያለችውን ወይም ያለውን ዝንብ ሲፈልጉ ሲያደንቁ ይሰማል።መቼም ከቀፎ ውጭ ምን እንደሚኖር የታወቀ ነው።ንብ ትናደፋለች ብሎ ንብ የማያነባ ገበሬ ስንፍናውን እንጂ የንቢቱን ክፋት ማንም አይረዳለትም።ጥበብ አልባ መሆኑን ትዕግስት አልባ መሆኑን ተሸናፊነቱን እየተናገረ እንጂ የንቧን ጠባይ እየተናገረ አለመሆኑን ሁሉም ያውቅለታል።የትዳር ችግር ብቻ የሚያወራ በትዳር ተመርሮ ከቀፎው ውጭ የሚሄድም ስንፍናውንና ዐቅመ ቢስነቱን እንጂ የቀፎውን ችግር እየተናገረ አይምሰለው።ቀፎ ውስጥ ማረ የምትሰራው ንብ እንዳለች ሁሉም ያውቃልና።ሌላው ቀርቶ ውጭ ያለችው ዝንብም ይኼንን ታውቃለች።
     አንዳንዶች ከንብ ጋር የመኖር ጥበብ ሲያንሳቸው የማትናደፍ ንብ ፍለጋ ይኳትናሉ።የማትናደፍ ንብ መፈለግ" ከመረቁ አውጡልኝ ከስጋው ጦመኛ ነኝ" እንደማለት ነው።ወይም የማትዞር መሬት እንደመፈለግ።
     የማትናደፍ ንብ ከፈለግክ ከዝንብ ጋር ተጋባ።





20 last posts shown.