ወንጌል በስነ-ፅሁፍ


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


አላማችን በስነፅሁፍ ወንጌልን ለአለም ሁሉ ማድረስ ነው ። የተፈጠርንለትም አላማ ነውና!
-ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ
-ግጥም
-አዳዲስ ዝማሬዎች
-ወግ ሌሎችንም ያገኙበታል
ማንኛውንም ሀሳብ አስተያየት ለመስጠት
እንዲሁም አብሮ ለማገልገል በዚህ ያናግሩን።
@AksanAdane
chanal created January/ 30/2020

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter


ሰላም ቅዱሳን በTELEGRAM አድሱ ቻናል ተወዳጅ የሆነ እናንተም JOIN በማለት በተሰብ ይሆኑ 🙏

ለማስታወቅያ ስራ👉@kal_tf


ሰላም የዚህ ቻናል ቤተሰቦች ዛሬ ድንቅ የሆነ መንፈሳዊ ቻናል ይዘንላችሁ መተናል፦ ከታች ያሉትን ይቀላቀሉን!

WAVE ለመቀላቀል 👉@KAL_TF
መሳሰብያ WAVE የምንሰራው ክርስቲያን ቻናሎች ብቻ ነው
👇🔻👇🔻👇


ሰላም የዚህ ቻናል ቤተሰቦች ዛሬ ድንቅ የሆነ መንፈሳዊ ቻናል ይዘንላችሁ መተናል፦ ከታች ያሉትን ይቀላቀሉን!

WAVE ለመቀላቀል 👉@KAL_TF
መሳሰብያ WAVE የምንሰራው ክርስቲያን ቻናሎች ብቻ ነው
👇🔻👇🔻👇


Forward from: Wave Folder
❤🌍በ ቴሌግራም በብዙዎች ዘንድ የተወደደ ቻናል ልጠቁመችሁ
እኔም ወድጄዋለሁ ❤❤
ከታች ክፈት ያምለውን በመጫን ይግቡ 
Free promotion የምትፈልጉ አነግሩኝ 👉@seer_lewi
👇👇👇👇👇👇👇


ኣዳር እንዴት ነበረ


በ ጥቅት ግዜ ውስጥ በ ሺዎች ማግኛ መንገድ ነው
➺ Above  ➣  1k+ subscribers
➺ Above  ➣  2k+ subscribers
➺ Above  ➣  5k+ subscribers
➺ Above  ➣  10k+ subscribers
➺ Above  ➣ 100k+ በላይ subscribers ያላችሁ አነግሩን 👍
      ➨  @EtCwaver  👈
ማሳሰብያ
ከ 1k በታች  ❌አንቀበልም❌


...

       እንኳን አንተ
የፃፍከውን የቃልህን ባርኮት
እኔ የፃፍኩትን ስላንተ መለኮት
      ኖሬው ብሆን ኖሮ
ባላወቀው ነበር ሐጢያት መልኬን
ባልመተረው ነበር አለም ልኬን።


    (እንግዳዬሁ ዘሪቱ)


(አንተን ከኔ ማራቅ)

እኔን ካንተ ማራቅ
አውለብልቦ ሙዳ ስጋ
አንበሳን ማስከተል ከዚህ እስከ እዚያ ጋ
አንተን ከኔ ማራቅ
ከአንበሳው ታግሎ በሳምሶን ትክሻ
ያንን ሙዳ ስጋ
ተፍጨርጭሮ መንጠቅ  ከጥርሱ ንክሻ።
እንደዚህ ነው እግዚሐር
እኔን ካንተ ማራቅ ውስን አያለፋም
አንተን ከኔ ማራቅ፣ ኑሮ ነው አይገፋም።

(እንግዳዬሁ ዘሪቱ)

(ልቀቀኝ!..አለቅም!)

መስመር አለ ከግሬ' ላይ፣ በደል ሰፈር ሀጢያት ስቀኝ
ካለሁበት ድረስ መጥተህ፣ በህይወት ቃል የጠፈርከኝ
ሰንበር አለ ከእጄም ላይ፣ ስፍጨረጨር የሰነኩት
አለቅህም ያልከኝ ለታ'፣ እንድትለቀኝ የታገልኩት።
                      ;
እኔን መከተል ነው፣ ያንተ የለት' ፍዳ
ካንተ ለማምለጥ ነው፣ የኔ ደሞ እዳ
            ግና በዚህ ሁሉ
አልልህም ለምን ፤ እንዴት አትለቀኝም
ጥያቄ ነው እንጂ መልስስ አያልቀኝም
          ያኔ...ድሮ....ድሮ
          ልቤ ካንተ አድሮ
           የደከምኩ ለታ
እንዳትለቀኝ ብዬ የፀለይኩት ፀሎት
መልስ ይሆናልና መጥቶ ከፀባኦት።



(እንግዳዬሁ ዘሪቱ)


(መናኝ አትድከም)

ሕይወት መንገዱ የለውም ድንበር
መኖር ነው የሚያልቅ ከሞት ደጃፍ በር
ብትጓዝ ጥረህ ጠቅጥቀህ አቅም
እድሜ ነው ሚቋጭ መንገድ አያልቅም
መናኝ አትድከም
የሌት' ፋናህን አሁን ለኩሰው
ውስን አይደለም
ከግቡ ቀድሞ ሚጨረቁሰው።

(እንግዳዬሁ ዘሪቱ)


(ስንወድቅ ለመነሳት)

ለመቆዘም የምትሆን ለመተከዝ ከሰው ጀርባ
ለማለቀስም የምትሆን በእንፍስፍ ትንሽ እንባ
ለትዝታም የምትሆን ሃሳብ ቀዝፎ ለመሰወር
ለናፍቆትም የምትሆን ካድማስ ማዶ ለመወርወር
ለመኖርም የምትበቃ ጥቂት ሰይፍም ጠላት መውጊያ
ለትርክትም የምትሆን እግዚሐርኮ ብሎ ማውጊያ
ለደግነት የምትበቃ ጥቂት ለሰው ለመሳሳት
ለመዳህም የምትሆን በእንፉቅቅ ለመነሳት
ለመስማትም የምትሆን ጥቂት ጆሮ ማዳመጫ
ለማየትም የምትበቃ የእግዚሐር ደጁን መመልከቻ
ለማገገም የምትሆን  ትንሽ አቅም ይዘህ ውደቅ
አቅም ከድቶህ ለእግዚሐር መኖር
ነፍስህ ድረስ አቅም ሲደቅ።


(እንግዳዬሁ ዘሪቱ)


(ቆይ አንድ ጊዜ)

በሽህ ቃላት ጥሪ
አምላክ እንደ እንግዳ ቆሞ እየጠበቀው
ቆየኝ ነው መልሱ
ይሄንን ልጨብጥ ያኛውን ልልቀቀው።
በቀጠሮ ቃላት
እየተፍገመገመ ፈጣሪውን መርሳት
ጠብቀኝ ቆይ እግዚሐር እቺን ልጨርሳት።
መጣሁ አንድ ጊዜ
መኖሬን ለነገ ትንሽ ላበጃጀው
እንዳለ ነበረ
ሲንከላወስ ባለም' ሳይጎብዝ ያረጀው።

አንድ ጊዜ እግዚሐር ቆየኝ
ከህይወት አፍ እቺን ልሙላ
ብሎ ቢጓዝ ወደ የትም፣ ከመኖር ዘንድ የለም ኬላ
ታገስማ መጣሁ አንዴ
መስመር ላስይዝ እቺን ልምራት
እያለ ነው ዓለም ሞኙ፣ የሚሆነው የሳት' ራት።

(እንግዳዬሁ ዘሪቱ)


"ለውለታኽ"
ምድር መጻፊያ ብትሆነኝ፤
ሰማይ ቀለሟን ብትለግሰኝ፤
ከዛፎች መሀል ረዥሙን፡ወስጄ ቢሆነኝ ብዕር፤
በውሀ አጥቅሼ ልፅፍ፡ብራና ሆና ምድር፤
ካደረክልኝ ከሆንክልኝ ከሰራክልኝ፡ከውለታኽ ጋር አይነፃፀር፤

ባለውለታዬ የይሁዳ አንበሳ፤
ውለታኽን ልፅፍ ስነሳ፤

የሰማይ ቀለሟ የፈዘዘ፤
ውበት የሌለው የደበዘዘ፤
ምድር አንድ መስመር፤
የማትበቃ ስንኝ ለመደርደር፤
የምታንስ ውለታኽን ለመዘርዘር፤
ባህር ትንሽ ጠብታ ውሀ፤
ፀሀይ የሚነግስበት ሰፊ በረሀ፤
እንኳን ለማጥቀስ የማትበቃ ለመጠጥ ውሀ፤
ውቅያኖስ ትንሽ አጭር፤
የምሻገራት ዘልዬ በእግር፤
ሀይቁ ባዶ ጉድጓድ፤
የተገኘ በመሀል መንገድ፤
ምንጩ ባዶ ደረቅ መሬት፤
የውሀ ጠብታ 'ኳን የማይታይበት፤
ይሆንብኛል ሁሉ ያንስብኛል፤
ቃላት ያጥረኛል ይሳሳብኛል፤
ውለታኽን መግለፅ ያቅተኛል፤

ግን እንዲሁ በደፈናው ተመስገን ልበል፤
ላደረክልኝ ነገር ሌላ ምን ልከፍል፤
ምን ልስጥ እጅ መንሻ፤
ለውለታኽ ይሆን ዘንድ መካሻ፤
ወርቅ አልማዝ ዕጣን ከርቤ
መሸከም አቃተኝ ጥቂቱን ሰብስቤ፤
በውለታኽ ፍቅርህን አኑረህ በልቤ፤
አንተ ግን!አንተ ግን!
ለእኔ ያደረክልኝን የሆንክልኝን የሰራክልኝን፤
ደግሞም ዕለት ዕለት ምታደርግልኝን፤
አትቆጥርብኝ አታይ ከቶ እንደ ውለታ፤
የፍቅርህ መግለጫ አድርገህ ስጦታ፤
ታደርግልኛለህ መልካሙን ጠዋት ቢሆን ማታ፤
መልካም ቸር ነህ ጥሩ አሳቢ ጌታ፤
ለውለታኽ
ለውለታኽ
ለውለታኽ፤
ተመስገን እንጂ ምን ልበልኽ፤

✍ሰውሁን በለው(አቤኒ)


💐የእግዜር ልጓም💐
       ክፍል 25

    ተከታታይ ልብ-ወለድ

✍Aksan Adane


.........ወዲያው እሳቱ ተወንጭፎ እባቢቱን አመድ አደረጋት ሴትየዋ ተዝለፍልፋ ወደቀች ሌሎቹ ይሄ ክስተት የታያቸው አልመሠለኝም ተሸካክመው ይዘዋት ወጡ :: ምንድነው ያየሁት? ቅዠት አይደለማ አቶ ዴቪድ አልቆዩም ወጥተው ሄዱ የዚያድን መንቃት በብርቱ እጠባበቅ ጀመር እርሱን እየጠበኩ እንቅልፍ አሸለበኝ::
ከእንቅልፌ ስነቃ ዚያድ አልነበረም::
የት ወሰዱት ብዬ ግራ ተጋባሁ :: ከቆይታ በኋላ ሜርሲ ምግብ ይዛ መጣች ዜማ እንዴት ነሽ? ደህና ነኝ ዚያድን የት ወሰዱት አልኳት እሽሽሽሽ ብላ ጠቋሚ ጣቷን አፏ ላይ አሳረፈችው እባክሽ ሜርሲ ገደሉት? ሞተ? ንገሪኝ ምን አደረጉት? ጮኹኩ በፍጥነት በሩን ከውስጥ ቆለፈችው ጥግ ጥጉን ካሜራ መኖር አለመኖሩን ካረጋገጠች በኋላ
ኸረ ዜማ አፍሽን ዝጊ እባክሽ:: ይከውልሽ ዛሬ መስዋዕት ሚቀርብበት ቀን ነው በየከተማው ያሉ የተመረጡ ሰዎችን በአደጋ :በሰዉ እጅ ህይወታቸው መስዋዕት ይደረጋል :: ሁሉም ወደ ሰይጣንነት የሚቀየሩበት ሰዓት ነው ድምፅሽንም ጮክ አታድርጊ እኔም ከዚህ አልወጣም :: በእርግጥ ዚያድን ምንም የሚያደርጉት አይመስለኝም እናቱ ግን ዛሬ ከሚሰዉት መካከል እንደሆነች ሰምቼአለሁ አለች እያቀረቀረች ::
ስቅስቅ ብዬ አለቀስኩ ኸረ ጌታ ሆይ እንደፍቃድህ ይህንን ነገር አስቁም እናቱን ክፉ አይንካበት በእኔው እናት ልክ ተሰማኝ ልታረጋጋኝ ተጠግታ ከአልጋው ጥግ ተቀመጠች::






💐💐 @wengelbeArt 💐💐





ይኸውልሽ ዜማ የጭንቁ ዘመን ሳይደርስ አልቀረም ከዚህ ላንወጣ ሁሉ እንችላለን መጨረሻችን እዚሁ ሊሆን ይችላል ግን ተስፋ አንቆርጥም በየትም በየትም አድርገን ከዚህ እንውጣ ትውልዱን ልናነቃው ይገባል አይመስልሽም?
ሜርሲ እኔ ከማስመስል በእነርሱ ፊት በተለይ ዋናቸው ሚባለውን ሉሲፈር ያረፈበትን ሰዉዬ ፊት ለፊት ቆሜ አንተ አይደለህም ኢየሱስ ነው ጌታ ኢየሱስ ነው ንጉስ ብዬ እዛችው ቢሰይፉኝ ይሻለኛል ከእነርሱ ጋር መመሳሰል ምን ማለት ነው እንዴትስ ጭንቅ ነው?
ዜማ ለእኛማ ቢሆን ያ እጅግ የተሻለ ነበር :: ውጪ ስላለው ትውልድ ነው መሆን ያለብንን ምንሆነው እኛ የምናሳልፈውን ህይወት ወጥተን ብናወራ ድራማ ወይ ቅዠት ነው ልንባል እንችላለን :: ጌታም እንደሚያስወጣን አምናለሁ ::
በሩ ለመከፈት ተሞከረ ሁለታችንም ተፋጠጥን ማነው? አለች ሜርሲ ክፈቺው ድምፁ ትንሽ ይርቅ ነበር ::ቁልፉን ከፈተችው አቶ ዴቪድ ነበሩ :: ሲጣደፉ ገቡና ወንበር ስበው ተቀመጡ ሜርሲ እና እኔ ተያየን ሁኔታቸው አንዳች ነገር እንደተፈጠረ ያሳብቃል አቶ ዴቪድ በሰላም ነው አለቻቸው ......



........ይቀጥላል.......


✍written by Aksan Adane


💐💐 @wengelbeArt 💐💐
💐💐 @wengelbeArt 💐💐


(የፅድቅ ልብሳችን)

አዳም
ለገባበት የእግዚሐር እዳ
ዘየደና ከራሱ ጋር ሲነጋጋ በማለዳ
ቅጠል ቆርጦ ልብስ ሰራ ፣ መሸፈኛ ለሃጥያቱ
ሃፍረት ገላን መጋረጃ አጠለቀ ከሰውነቱ

ቀትር ሲሆን ፍሟ ሲነድ ፀሐይ ግላ
ነፀብራቋ አልፎ ሲዘልቅ ከገነቱ የዛፍ ጥላ
አዳም ሆዬ አሸልቦ
ከከሰአት ኋላ ግድም
ጠወለገ በፀሐይዋ ያጠለቀው ቅጠል ግልድም።

ማለዳ አበጀ
ቀትር ላይ አረጀ።

ቢያበጃጅም ለሃፍረቱ ከበደሉ ለመነጠል
ለዘመናት አልሆነውም የለበሰው ከንቱ ቅጠል።

ግና
የኛ ጌታ ያለበሰው ቆዳ ገፎ
ዛሬም አለ
ይለብሰዋል ትውልድ ሁሉ ከሱም አልፎ
አይጠወልግ አያረጅም አይገባበት ውሽንፍሩ
ስለበደል ያጠልቀዋል አህዛብ ሁሉ በስፍሩ
እግዚሐር የኛ ዲዛይነሩ
አይገመት መቼም በሰው
አንድ ጊዜ የሰፋልን ለዘላለም ሚለበሰው።

አዳም ገላን ያለበስከው በገነቱ ገፈህ ቆዳ
በክርስቶስ ያለበስከን የፅድቅ ልብስ በጎልጎታ
ክብራችን ነው ጌታችን ሆይ
የምንለብሰው መዘነጫ
ለገላችን ማማር ውበት ከመከራም ለማምለጫ።


(እንግዳዬሁ ዘሪቱ)


ሠላም ይብዛላችሁ የዚህ ቤት ቤተኞች እህታችሁ አክሳን ነኝ ::
በአንድ አንድ ገጠመኞች ይህቺን ሶስት ቀን ተጠፋፍተን ነበር ::
ስለ ትዕግስታችሁ ተባረኩ::
...የእግዜር ልጓም ምዕራፍ 1 ሊፈፀም ሁለት ክፍሎች ይቀሩታል :: በመሃል በሌላ ሰዉ የተፃፈ አጭር ታሪክ አብረን እናነባለን ::አስከትሎም
ምዕራፍ 2 ይቀጥላል ተባረኩ::

💐💐
@wengelbeArt 💐💐


💐የእግዜር ልጓም💐
       ክፍል 24

    ተከታታይ ልብ-ወለድ

✍Aksan Adane

...........   አንደኛው አጠገቤ ደርሶ በጥፊ ደረገመኝ እሺ የኛ ተዋናይ አንቺ ነሽ ጌታችንን ልታታይ ምትሞክሪው? አንቺ ትንኝ :: ፀጉሬን ጨምድዶ ያዘኝ ይታይሻል ይሄ ካሜራ አለኝ ከአናቴ በላይ የተደቀነ ካሜራ እያሳየ ሁሌም ቢሆን እይታ ውስጥ ነሽ ሰማሽ ?ፀጉሬን የያዘበት ህመም ብቻ ነው የተሰማኝ ለእኔ ዚያድ ከተኛበት ብድግ አለ ፀጉሬን ለቀቀኝና አንገቱን አነ ቀው ከተቀመጥኩበት ብድግ ስል ገፍትሮ ወረወረኝ ኑ ያዙአቸው እነዚህን ቆራርጦ መጣል ነው አላቸው ሁሉም እኛን ለመያዝ ተጣደፉ :: ሁሉም እጁን ሰነዘረብን :: እንደዚያ እየደበደቡን ገና ሳያገግም ከአሁን አሁን ዚያድን ገደሉት ብዬ ተሳቀኩ :: ከአፍንጫዬ ደም ይንቆረቆር ጀመር :: እንደ ውሻ መሬት ለመሬት እየጎተቱን የሆነ ጨለማ ክፍል አስገቡን እንደፈራሁትም ዚያድ ራሱን ስቷል ትንፋሹ ይሰማኛል ነገር ግን የእኔም ሰዉነት በመድቀቁ ልጠጋው አልቻልኩም አንዳች የብርሀን ጭላንጭል እንኳን የለም ዚያድ ብሎ መጣራት አማረኝ እንዴት አድርጌ ድምፅ ላውጣ :: በዚህ ሁሉ ውስጥ ዚያድ ሲነግረኝ የነበረዉን በአእምሮዬ እየሳልኩ እደሰት ጀመር ::
አንድ ዝማሬ ልክ በትልቅ ስፒከር ከውጪ እንደተከፈተ ሆኖ ይሰማኝ ነበር ::
"በከንቱ እንዳልለፋ ስለራራልኝ ስላዘነልኝ
" የህይወትን መንገድ አቅጣጫ አሳየኝ
"ያየኹትን መንገድ ይዤ እዘልቃለሁ
" እንደ ሄድኩም አልቀር ወደ እረፍቴ እገባለሁ :: የቤቲ ተዘራ ዝማሬ ነበር በራሷ ድምፅ በጆሮዬ ይንቆረቆር ነበር በዚያው ልክ በጀርባዬ እንደወደኩ እምባዬ በጆሮዎቼ እየ ወረደ ይንቆረቆር ጀመር ለረጅም ሰዓት በእንደዚህ ሁኔታ ነበርኩ አይኖቼ እንቅልፍ አሸነፋቸው ::ስነቃ ያስታወስኩት ነጭ በግ ሲያወራኝ እንደ ነበረ ነው :: ሰዉነቴ ላብ በላብ ሆኖ ነበር አፍንጫዬ በወረደው ደም ደርቆ ነበር ::ወደ ቀኝም ወደ ግራም መገላበጥ ተሳነኝ እንደ ቀደሙ የዚያድ ትንፋሽም አልሰማ አለኝ ይሄ ልጅ ሞተ እንዴ ?እንዴት ተጠግቼ ልየው ጨለማው በቃል አይገለፅም ::







💐💐 @wengelbeArt 💐💐







ከረጅም ሰዓታት በኋላ በሩ ሲከፈት ቀይ ብርሃን ቤቱን ሞተ ጨለማው በስንት ጣዕሙ አይኔ መቋቋም እስኪያቅተው አስቀያሚ ብርሃን ነበር :: የብዙ ሰዉ ኮቴ ነበር የተሰማኝ :: ወንበር ስበው አስቀመጡት አንገቴን ማንቀሳቀስ ስላቃተኝ ሚሆነውን በመስማት ነው እየተረዳሁ የነበረው :: እንዲያውም ዛሬ ሌሊት ለሚቀርበው መስዋዕት ብናውላቸው ባይ ነኝ ቅድም በጥፊ ያለኝ ሰውዬ ድምፅ ነበር ::
ተው ተው ወዳጄ ዞያር እነዚህ ርካች ለአምላካችን መስዋዕትነት ይመጥናሉ እያልክ ነው? የአቶ ዴቪድ ድምፅ ነበር ማመን አልቻልኩም :: አይደለም ወዳጄ እነዚህ ትናንሽ ትንኞች የአምላካችን ትልቅነት እስኪገባቸው እየቀጣን እናቆያቸው ::ከዚያም ጥሩ ሌሎችን ማራኪዎች እናደርጋቸዋለን ::
:-አቶ ዴቪድ ለአምላካችን አይመጥኑም ባልከው ብስማማም ጥሩ ማራኪ የሚለው ቃል ጎርብቶኛል እነዚህ ከሀዲዎች በምን ሂሳብ የአባታችን ትልቅነት ይገባቸዋል? ለድፍረታቸው እዚሁ ቆራርጬ ልተዋቸው እንጂ ::
ወዳጄ ዞያር አትቸኩል እኛም በግዜ ሂደት መስሎኝ እውነቱ የገባን በእኔ ጣላቸው ::
ክርክሩ ጦፈ ግሩፑ ለሁለት ተከፈለ ግማሾቹ ከአ ዴቪድ ጋር ግማሾቹ ከሰውየው ጋር ሆኑ ሰዉየው እሱ በበላይ አካል የሚወሰን ይሆናል እያለ ሄደ ሌሎችም ተከተሉት ::
አቶ ዴቪድ ሀሳቦን ተስማምቼ የቀረሁ ብሆንም ግን እንዳሉት ማድረግ እንችላለን? አንደኛዋ ጠየቀች::
:-እንችላለን ክሩዳ አላማችን ሁሉን አባል ማድረግ አይደለም? እዚህ ድረስ ከመጡ አባል ማድረግ ካቃተን እኛም ብንሞት አይሻለንም?
አዎ አዎ ሁሉም አጉረመረሙ በጣም ጥሩ አሉ አቶ ዴቪድ ::
ይሄ ሰዉዬ የምሩን ነው? እኛ በአንዴ የተያዝን እርሱ እንዴት እስከዛሬ ሊነቁበት ከይችሉም? የአሁኑ ሁኔታ እንኳን በቂ ነበር ለነገሩ መንፈስ ቅዱስ አሳውሮአቸው ነው :: እኔም ነገሩን ስለማውቀው ይሆናል እያልኩ ደግሞም በካሜራ መያዛችን ወይ ሰይጣን ተብዬ ሰዎች እኮ ሁለም ባይሆኑም ሁሉን ማድረግ ምትችል ይመስላቸዋል :: በእኔ ህይወት ግን እድል ፈንታ የለህም አልኩኝ በውስጤ ::
ወዲያው ቃሬዛ አምጥተው ወደ አንድ ክፍል ተወሰድን ::
ጥግና ጥግ ሁለት አልጋዎች ነበሩበት ግሉኮስ ተደረገልን :: አቶ ዲቪድ በአይናቸው ምልክት ሰጡኝ አንደኛዋ ይህንን ክስተት በመመልከቷ በክፉ አይን አየቻቸው ፊቷ ላይ የሚታይ አውሬ ነበር አይኖቿ ደም ለበሱ አቶ ዴቪድ ፊት ለፊቷ ቆመው ተፈጠጡ ለእኔ ራዕይ እስኪመስለኝ ከእርሷ ግንባር ላይ የምትወራጭ ትንሽዬ እባብ ከእርሳቸው ግንባር እንደ ነበልባል የሚንተከተክ እሳት ተመልከትኩ ወዲያው እሳቱ ተወንጭፎ አባቢቱን ገመድ አደረጋት ሴትየዋ ተዝለፍልፋ ወደቀች ::
ሌሎቹ ይሄ ክስተት የታያቸው አልመሰለኝም ተሸካክመው ይዘዋት ወጡ ..........



........ይቀጥላል.......


✍written by Aksan Adane


💐💐 @wengelbeArt 💐💐
💐💐 @wengelbeArt 💐💐


..........የሆነችውን ለማወቅ ይጎተጉቷታል።የአብስራ ግን "አያገባችሁም:አትከተሉኝ፣ብቻዬን መሆን እፈልጋለሁ።"ስትለቸው መከተላቸውን አቆሙ።የአብስራ በታክሲ የመጣችውን መንገድ በእግሯ አቀጠነችው።

የ የአብስራ አባት ከቤታቸው ሳሎን በሶፋው ላይ ቁጭ ብሎ ማጉያ መነፅሩን አድርጎ መጸሀፍ ቅዱስ እያነበበ ነው። እናቷ ደግሞ ቲቪ እያየች ነው።

የአብስራ የግቢያቸውን በር በርግዳ ገብታ የሳሎኑንም በር በእግሯ ረግጣ ስትከፍት እናቷ እና አባቷ ተደናግጠው ከተቀመጡበት ተነስተው"ምንድ ነው? ምን ሆነሻል?የአብስራ?አንቺ የአብስራ?" እያሉ ደጋግመው እየጠሯት የሆነችው ቢጠይቋት ምንም እንዳልሰማች ወደ ክፍሏ ገብታ በሩን ዘጋች።

አባት እና እናቷ የክፍሉን በር ደጋግመው እያንኳኩ እንድትከፍት ቢለምኗት "ብቻዬን መሆን እፈልጋለሁ" ነበር መልሷ። ወላጆቿም እሷን ላለማስጨነቅ ሲሉ ብቻዋን እንድትሆን ፈቀዱላት።ባህሪዋን ስለሚያውቁ ወደ ቦታቸው ተመልሰው ተቀመጡ።

ከክፍሏ ሆና ብቻዋን ታሰላስል ጀመር። "እግዚአብሔር ለምን ጥቁር አድርጎ ፈጠረኝ?ለምን?እግዚአብሔር ሆይ ለምን ጥቁር አርገህ ፈጠርከኝ?" እያለች ስትጠይቅ ከቆየች በኋላ "ቆይ እግዚአብሔር አንዱን ነጭ አንዱን ጥቁር አድርጎ ፈጠረ?ለምን?ለምን ቀይ፣ጠይም ፣ጥቁር አድርጎ እኮ ለምን ፈጠረ" እያለች ራሷንና የሰው ሁሉ ጠበቃ አድርጋ መጠየቁን ተያያዘችው።

ብዙ ጥያቄ በአዕምሮዋ ከተመላለሱ በኋላ መሸትሸት ሲል ስለተረጋጋች የክፍሏን በር ከፍታ ወጣች።ስትወጣ እናቷ በሳሎኑ አትታይም።አባቷ ብቻ ቁጭ ብሎ ሲያነብ የነበረውን መጸሀፍ ቅዱስ የመሀል ጠረጴዛው ላይ አስቀምጦ ቲቪ
እያየ ነው።

አባቷም"ነይ ልጄ እስቲ እዚህ ቂጭ በይ" እያለ በእጁ እንድትቀመጥ ጠቆማት። እሷም ፊቷን ጥላ እግሮቿን እየጎተተች አጠገቡ ስትቀመጥ ትከሻው ላይ ጣል ያደረገውን ጋቢ ከእሷም ትከሻ አድርጎ በአንድ እጁ አቅፏት ተቀመጡ።

እናቷም ከማዕድ ክፍል እየወጣች "ውይ ልጄ ወጣሽ፣እኛ እኮ ምን ሆናብን ይሁን ብለን ስንጨነቅ"አለችና"ቆይ ወጥ እንዳያርብኝ መጣሁ"ብላ ወደ ማዕድ ቤት ገባች።

አባቷም እንዳቀፋት የሆነችውን ጠየቃት። እሷም አንድም ሳታስቀር ሁሉንም ዘርዝራ ነገረችው።አባቷም "ለዚችው ነው"ሲላት ቅድም ውስጧ ሲመላለስ የነበረውን ጥያቄ አባቷን ጠየቀችው።

አባቷም"አይ ልጄ እግዚአብሔር እኮ ታላቅ አምላክ ነው፡ስራውም አይመረመርም፡ እርሱ ሁሉን የሚያደርገው በፈቃድ ነው፡ እርሱ ለምን አይባልም:እግዚአብሔር እኮ ሉዓላዊ አምላክ ነው"አለና ትንሽ አሰብ አድርጎ ቀጠለ"ይሄውልሽ የኔ ልጅ፡አንቺ እግዚአብሔር ለምን ጥቁር አደረገኝ ብለሽ ማዘን፣መተከዝ፣መከፋት፣ማማረር የለብሽም።እኛ ሁላችንም የእግዚአብሔር ልጆች እኮ ነን።በእግዚአብሔር አምሳል የተፈጠርን፣እርሱን የምንመስል፣በምድር ላይ ስንኖር ደግሞ ሁሌም እርሱን እያሳየን ነው።መዝሙረኛው ዳዊት ምን አለ መሰለሽ""ግሩም እና ድንቅ አድርገህ ስለፈጠርከኝ አመሰግናለሁ""ይላል። ታዲያ ልጄ አንቺም ግሩምና ድንቅ የሆንሽ ፍጡር ነሽ።ሁሌም ቢሆን ስለ አፈጣጠርሽ እግዚአብሔርን ማመስገን አለብሽ!እሺ ልጄ"ሲላት እሷም "እሺ አባዬ" ብላ ተቀበለችው።

እናቷም ምግቡን ሰርታ ጨርሳ ስለነበር ራት አቅርባ በልተው ከተጫወቱ በኋላ የአብስራ ወደ ክፍሏ ገባች።አልጋዋ ላይ ሆና አባቷ ያላትን ማሰብ ጀመረች።

"ለካስ እኔ ግሩም እና ድንቅ ፍጡር ነኝ።ቆይ ግን ጓደኞቼ ብርቋም አካብዴም ግሩምና ድንቅ ፍጡር ናቸው"ብላ ፊታቸውን እያስታወሰች አሰበችና
"ሰው ሁሉ በእግዚአብሔር አምሳል ነው የተፈጠረው።ስለዚህ እነርሱም የሚገርሙ የሚደንቁ ፍጡር ናቸው።"

"እግዚአብሔር ሆይ ግሩምና ድንቅ አድርገህ ስለፈጠርከኝ አመሰግንሃለሁ። አንተ ሉዓላዊ አምላክ ነህ፡ሰውን ግሩምና ድንቅ አድርገህ ስለፈጠርካቸው አመሰግንሃለሁ።"አለችና አባታችን ሆይ ጸልያ"በሰላም ያዋልከኝ በሰላም አሳድረኝ" ብላ በንጋታው ወደ ቤተ-ክርስቲያን ስትሄድ በዓይነ ህሊናዋ እየታያት እያደከማት እያደከማት እያንገላጀጃት እንቅልፍ ወሰዳት።ይህ ቀን ለየአብስራ ህይወቷ የተለወጠበት ቀን ነው።

ውይ የእኔ ነገር!የየአብስራን አባት ሰም ሳልነግራችሁ።አባቷ አቶ ግሩም ድንቁ ይባላል።የየአብስራ ሙሉ ስም የአብስራ ግሩም ድንቁ ነው።እውነትም የእግዚአብሔር ስራ ግሩምና ድንቅ ነው።

ሰውሁን በለው(አቤኒ)
5/10/2014
ኢትዮጵያ🇪🇹❤️
ተባረኩ🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏


(እግዚሐር ማለት ለኔ..)

እግዚሐር ማለት ላንተ
ብሎ ቢጠይቀኝ
እስክመልስ ነበር እድሜዬ ያለቀኝ
እርሱ ማለት ለኔ
ብዬ እንደፃፍኩት
እስከዛ ድረስ ነው መኖርን የኖርኩት።
;
እሱ ማለት ለኔ...
እናት አባት እህት ወንድም
ጓደኛዬ በመውደድም
ተንከባክቦ ያሳደገኝ
ከነ ክምር እድፍ ጎኔ
ሞግዚቴም ነው አምላክ ለኔ።

ያምላክ' ወጉን ለኔ ጥሎ
ከመስቀል ላይ ተንጠልጥሎ
አጀገኖ በጣር ልቡን
አንጠባጥቦ የደም ላቡን
የገደለ ስጋ ነፍሱን በጭካኔ
አዳኜም ነው አምላክ ለኔ።

ከሰማያት ከአሪያም ዘንድ
ከራሱ ላይ የደፋ ዘውድ
ህዝብ ኩሉ የሚወደው
ግርማ ሞገስ የሚያውደው
የሚገዛ አለማትን
በሚቃጠል በፍም ወኔ
ንጉሴም ነው እግዚሐር ለኔ።

የሲኦልን ደጃፍ መዝጊያ
ከነውጥ አለም መሸሸጊያ
በሁካታው በማዕበሉ
ቢተራመስ አለም ሁሉ
የሚያኖረኝ በእርጋታ
አለኝታም ነው ለኔ ጌታ።

እርሱ ማለት ለኔ
ብዬ እንደፃፍኩት
እስከዚህ ድረስ ነው መኖርን የኖርኩት።

እግዚሐርኮ ለኔ...
:
:
:
:

(እንግዳዬሁ ዘሪቱ)
@wengelbeArt


💐የእግዜር ልጓም💐
       ክፍል 23

    ተከታታይ ልብ-ወለድ

✍Aksan Adane

........... ላገኘው ወደ ተኛበት ቦታ ሄድኩ :: ገና የክፍሉን በር ከመክፈቴ ሊበርር ምንም አልቀረው
:-ዜማ እንዴት መጣሽ አየሁት እኮ አየሁት ዜማ::
:-ማንን ?
:-አየሁት ዜማ የት አግኝቼ ልንገርሽ?.
ስለ አቶ ዴቪድ ነው? ምንድነው ሚያወራው ልጁ?ምንድነው
የሆነ ደስታም መገረምም በተቀላቀለው ስሜት ነበር የተቀበለኝ :: ተጠግቼ እጄን ዘረጋሁለት :: አለባበሴ ሁኔታዬ ግራ ሳያጋባው አልቀረም ከእግር ጥፍሬ እስከ ራሴ እያየኝ አአአንንቺቺ ዜማ ነሽ ? ራስሽ ነሽ? እንዴ መንፈስ መሠልኩህ እንዴ ከግድግዳ ጥግ የተቀመጠውን ወበርን ወደ አልጋው አስጠግቼ ተቀመጥኩ :: በሩን ዝጊው አለኝ ኦዉዉዉ እሺ ብዬ በሩን ዘጋሁት ::
:-ሀኪሞችህስ?
:-ወጥተዋል ::
:-አሁን በጣም ደህና ትመስላለህ ለምን እንደዛ አደረክ አልልህም ግን የሆነ ነገር ብትሆን ፀፀት ይገድለኝ ነበረ ዚያድ ::
:-ዜማ አመንሻቸው ማለት ነው? ምን አስነክተው ነው የቀየሩሽ በዚህች አጭር ጊዜ ሁሉ ነገርሽ እነርሱን እኮ ነው የሚመስለው ::
:- አረጋጋው ዚያድ ወደ ጆሮው ተጠግቼ እየተወንኩ ነው አልኩት ::
:- እየተወንኩ ማለት ?
:-ይከዉልህ ዚያድ የአቶ ዴቪድ ንግግር ትውስ አለኝ ስለ እርሱ ለማንም እንዳልናገር ያስጠነቀቀኝ ::እእእእእእ ምንነቱን አሁን አልነግርህም ግን ተመሳስዬ እያስመሠልኩ እንጂ በጌታዬ ቀልድ አላውቅም::
:-አንተ ምንድነው አየሁ አየሁ ያልከኝ?
መርዙን ጭልጥ እንዳደረኩት ከደቂቃዎች በኋላ የሆነ ነገር ምንጭቅ አድርጎ ወሰደኝ አንዲት የብርሃን ጭላንጭል በሌለበት ፀጥታ ቦታ ቀጥላም ነብሴ ከደመና በላይ ከፍ ከፍ ከፍ አለች ደመናውን እየሰነጠቀች በኃይል ትበር ነበር :: በከፍታ ላይ ሆኜ ክንፌ እየተርገበገበ ታላቅ ከተማ አየሁ ታላቅ ነበረች ውበቷ ግሩም ነበር በቃለ የማይገለፅ ውበት የነገስታት ከተማ ትመስላለች:: ሁሉ ሰዉ ደስተኛ ነው ::
ወዲህ እና ወዲያ ይቦርቃል :: ዋዉዉዉዉዉ እዚህ ነበር መኖር ወርጄ ልቀላቀላቸው አማረኝ ::ይህን እያሰብኩ ወዲያው እሳት ወረደባት ምንጩ የማይታወቅ እሳት ::አንዳንዱ እሳቱን ያላየ ባለበት ድርጊቱን ቀጠለ ::እንዴ ምን እየተደረገ ነው ኸረ አለቃችሁ ነደዳችሁ እያልኩ እጮህ ጀመር ::ርቀታችን ለየቅል ነበርና ማንም አልሰማኝም ስትቃጠል አየሁ ፈራርሳ ባድማ ሆነች ያደነቅሁት ውበቷ ዶቃአመድ ሆነ :: አዘንኩ ውይይይይይይ ምንድናት ይህቺ እንዲ በሚንቀለቀል እሳት የምትነድ ? ጥያቄ ፈጠረብኝ::
ይህቺ አንተ የምትኖርባት ዓለም ናት::
ከበስተኋላዬ የተዋበ ልብን የሚያልፈሰፍስ ድምፅ ተሰማኝ እንዴት ያለ ድምፅ ነው ብዬ ለመዞር ገና ሳስብ የብርሃኑን ጨረር መቋቋም አልቻልኩም ::



💐💐 @wengelbeArt 💐💐





እንኳን መልኩን ላየው ከፊቱ የሚወጣውን
ብርሃን መቋቋም አቃተኝ እና በጉልበቴ ተንበረከኩ በቃ እሷቱን ያዘነበው ሰዉ ነው ሚሆነው ሊፈጀኝ ነው::አለቀለኝ እያልኩ
አንተ ማነህ? አልኩት
ድምፁ በጆሮዬ ሲፈስስ ያለመልማል እኔ ኢየሱስ ነኝ አለኝ::
ታላቅ ፍርሃት ወደቀብኝ ኢየሱስ ? ኢየሱስ ኢሳ?
አዎን ኢሳ ብለህ የምታውቀኝ ያለሁ የነበርኩ ለዘለዓለምም የምኖር እኔ ነኝ አለኝ::
ዜማ በቃ ከአሁን ከአሁን ፈጀኝ ብዬ በሰቀቀን አለቅሁ ::
እባክህን አታጥፋኝ እባክህ የአሁኗን ከተማ በእሳት እንደመታህ በቁጣህ አታጥፋኝ አልኩት :: ቀና ብዬ እጅ ለመንሳት ስሞቅር በቅፅበት በብርሃን መካከል ያየሁት መልክ እንባው ይወርድ ጀመር ከቀድሙ በእጥፍ አበራ
ወደ እኔ እንዳተረቀርብ ግዜህ ገና አልደረሰም ::
ያየኸውን ትመሠክራለህ መፍጠርም ማጥፋትም ዘለዓለማዊነትም ህያውነትም የእኔ ነው በስሜ የሚመጡ ሁሉ የሚያምኑብኝ የዘለዓለም ህይወት አላቸው ያርፋሉ በመንግስቴ ይሰማራሉ ::
አሁን የምትኖርባት አለም አትቀጥልም ትጠፋለች አሁን ካየኸው በእጥፍ እሳት ትቃጠላለች በጎቼን ግን እሰበስባቸዋለሁ ::
ለዘለዓለምም ከእኔ ጋር ይኖራሉ ::
እሺ ንጉሥ ሆይ አታጠፋኝም?
:-የምህረት ደጆች አልተዘጉም አላጠፋህም ታርፋለህ ::
ደስታዬን መቆጣጠር አልቻልኩም አቤቤቤቤቤቤቤቤትትትትትትት እንዴት ያለህ መሀሪ ነህ ብዬ ጮኹኩ ከጩኸቴ ሳበቃ ያንኑ ሰዉ በደም የተጨማለቀ ነጭ ልብስ ለብሶ አየሁት እጆቹ ቀዳዳ ነበራቸው እግሮቹም እንደዚያው ከአናቱ ላይ እሾህ ተከምሯል ደነገጥኩ ይሄ በፊልም ሲያሳዩን ድራማ ነው የምንለው ነገር አይደል እንዴ?
በውስጤ ነበር ያልኩት ድራማ አይደለም አንተ ትድን ዘንድ ስለ ሀጢያትህ ዋጋ እከፍል ዘንድ ይህን ሆኜአለሁ እወድሃለው እያለኝ ጀርባውን ሰጥቶኝ ወደ ታላቅ ብርሃን ገባ ቆይ አውራኛ አትሂድ አንዴ ልንካህ እባክህ አንዴ ልንካህ ምንም መልስ የለም ወደ ታላቁ ብርሃን ዘለቀ አቤት ፍቅርርርርርርር ብዬ ስጮህ ከከፍታው ላይ ተወረወርኩ እየጮኹኩ ስመጣ ራሴን እዚህ አልጋ ላይ እየጮኹኩ አገኘሁት ዜማ አየሁት እኮ እምባው እኔንም አስለቀሰኝ ተጠግቼ ከቀፍኩት ወዲያው በታላቅ ሀይል በሩ ተከፈተ ወደ 10 የሚደርሱ ሰዎች ነበሩ :: አንደኛው አጠገቤ ደርሶ በጥፊ ደረገመኝ እሺ የኛ ተዋናይ አንቺ ነሽ ጌታችንን ልታታይ ምትሞክሪው? አንቺ ትንኝ.....



........ይቀጥላል.......


✍written by Aksan Adane


💐💐 @wengelbeArt 💐💐
💐💐 @wengelbeArt 💐💐


ርዕስ፦አብ-ስራ

✍ሰውሁን በለው(አቤኒ)

አንዲት ጥቁር፣ጥርሷ ድፍን ያለ፣ሀጫ በረዶ የመሰለ፣ጸጉሯ ሉጫ ወገቧን የሚነካ፣ቁመቷ ሜትር ከሰባ፣ወፍራምም ቀጭንም የማትባል መካከለኛ የሆነች ሴት በቤታቸው ውስጥ ካለው፣በሮዝ የግድግዳ ቀለም በደመቀው፣ከራሷ ክፍል ውስጥ ከመስታወት ፊት ለፊት ቁጭ ብላ ራሷን ታያለች።

አንዴ የጸጉሯን ውበትና ርዝመት፣አንዴ የአይኗ ብሌን ዙሪያ ወተት መምሰል፣ አንዴ የአፍንጫዋን አወራረድ፣አንዴ የከንፈሯን አቀማመጥ፣አንዲሁም ፈገግ እያለች ለሳቋ ውበት የሚሰጣትን የጉንጯን ስርጉድ፣ሲያሻት ከተቀመጠችበት በመነሳት መላ ራሷን ታያለች።የአብስራ ለመስታውት ያላት ፍቅር የተለየ ነው።

የአብስራ ከጓደኞቿ ጋር የምትሄድበት ቦታ ከሌላት ቤት እናቷን በስራ ካገዘቻት በኋላ ወደ ክፍሏ ገብታ እራሷን ስትንከባከብ ትውላለች።እናቷ የቤት እመቤት ስለሆኑ ጎረቤታቸው ጋ ቡና ለመጠጣት፣በሳምንት አንዴ ለመሸመት፣ወደ ቤተ ክርስቲያን ለመሄድ ካልሆነ በስተቀር ከቤት አትወጣም።ብዙውን ስራ እናቷ ስለምትሰራ የአብስራ ብዙ የስራ ጫና የለባትም።

የአብስራ አባት የመንግስት ሰራተኛ ናቸው። ስራው ቀን ሙሉ የሚያስውል ስለሆነ ጠዋት ከቤት የወጣ የሚገባው አመሻሽ ላይ ነው።በስራው ምክንያትም የአብስራና አባቷ የመገናኘት እድላቸው ጠባብ ነው።ቅዳሜና እሁድ ግን ስራ ስለሌላቸው ከቤት አይታጡም።

የአብስራ ለእናትና አባቷ አንድ የስለት ልጇቸው ነች።ስለዚህም የአብስራ የጠየቀችውን ነገር ለማድረግ አባትና እናቷ ይጥራሉ።የአብስራ ከምትጠይቀው ነገር ከማይደረግላት ይልቅ የሚደረግላት ይበልጣል።አባትና እናቷ ሰለሚሳስሏት በምንም መልኩ እንድትከፋባቸው አይፈልጉም።የአብስራና ቤተሰቦቿ ከሚጣሉበትና ከሚጨቃጨቁበት ነገር አንዱ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ቤተ ክርስቲያን አልሄድም የማለቷ ጉዳይ ነው። ከልጅነቷ ጀምሮ ያደገችው ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ነበር።
"የጌታ ፍቅር አስደናቂ ነው/2
በጣም ከፍ ያለ ልደርስበት የማልችል
በጣም ዝቅ ያለ ልወርድበት የማልችል
በጣም ሰፊ ነው ላመልክበት የማልችል
የጌታ ፍቅር!😍"
የሚለውን መዝሙር በሰንበት ቤት፣ከቤተ ክርስቲያን ጓደኞቿ ጋር እየዘመረች፣የእግዚአብሔርን ቃል እየተማረች ነበር ያደገችው።ዛሬ ላይ ግን እንደዛ ከመርዘሙ የተነሳ መውጣት፣በጣም ዝቅ በማለቱ መውረድ ያቃታት፣በስፋቱ ምክንያት ማምለክ የከበዳት የጌታ ፍቅርን ማየት ከበዳት፣ የጌታ ፍቅር ካላቸው ሰዎች ራቀች፣ ወደ ቤተ መቅደሱ መሄድ ተወች።ቀስ በቀስ ሁሉንም መንፈሳዊ ህይወቷን ወዲያ ብላ በአለም ሰዎችና መድረክ ለመታየት የምትጣጣር የ18 አመት አፍላ ወጣት ሆናለች።

ለአባትና ለእናቷ የስለት ልጅ ከመሆኗ የተነሳ ወላጆቿ የተንከባከቧት መስሏቸው አቅብጠዋታል።ቀበጥ ሆናለች። አብዛኛውን ጊዜዋን የምታሳልፈው እመስታወት ፊት ነው።የየአብስራ መስታወት አፍ ቢኖራት "ኧረ ሰለቸሽኝ!ኡኡኡኡኡ.........." ብላ የምታማርርባት ይመስለኛል።

የአብስራ ሁለት የልብ ጓደኞች አሏት። ሩትና በረከት የሚባሉ። ሩት በ የአብስራ እድሜ የምትገኝ ጠይም፣አጠር ብላ ወፈር ያለች የ18 አመት ወጣት ነች። የአብስራና በረከት ሩትን ሲጠሯት አካብዴ እያሉ ነው።ምክንያቱም ሩት ሁሉንም ነገር ማካበድ አመሏ ነው።ወሬ ስታወራ አካብዳ፣የምትሰራውን ስራ አካብዳ፣የሆነ ነገር ኮሽ ቢል እንኳን እሷ ጆሮ ውስጥ የሚገባው በሚያስጎመጉም ሀያል ድምፅ ነው።በቃ ሁሉ ነገርዋ ማካበድ ነው።ለዚህም ነው አካብዴ ብለው የሚጠሯት።

በረከት ደግሞ ቀጭን ስንጥር የምታህል፣ጸጉሯ ከአናቷ ውልፍት የማይል፣መካከለኛ ቁመት ያላት፣ አይኗ ሸብራራ፣ጥርሷ የገጠጠ የ19 አመት ልጃ ገረድ ነች።በረከት ከየአብስራና ከሩት ረጋ ያለች ነገር ግን ሁሉም ነገር ብርቅ የሚሆንባት ነች።የሚጠሯትም ብርቋ እያሉ ነው።

ሁሌም ብርቋ እና አካብዴ የእነ የአብስራ ቤት ሄደው ነው ወደ ሚሄዱበት የሚሄዱት።ዛሬ ቅዳሜ ነው። እንዲሁም የክፍል ጓደኛቸው ልደት አለ።ወደ ልደቱ ስፍራ ለመሄድም ሁሌም እንደ ሚያደርጉት ብርቋና አካብዴ የአብስራ ክፍል ውስጥ ተገኝተዋል።

ቁም ሳጥኑን ከሞላው የአብስራ ልብስ መምረጡን ተያያዙት።ይሄ አይሆንም፣ይሄ ብዙም አያምርብሽም፣ይሄ አዲህ ሆነ፣ይሄኛው ደግሞ እንዲያ ሆነ፣ቀይሪ ቀይሪ ሲሉ ቆይተው በመጨረሻም አካብዴ ያካበደችውን ብርቋ ብርቅ ያደረገችውን ጥቁር፣በብልጭልጭ የተሽቆጠቆጠ፣ከእግሯ እስከ ጉልበቷ ያለውን ሰውነቷን እንዲሚያሳይ የተሰነጠቀ ልብስ ለብሳ ለብዙ ደቂቃ ተቀባብታ፣ተኳኩላ፣ተሽሞንሙና ልብሷ የሳይነስ ሕመምተኛ እስኪሆን ድረስ ሽቶ አርከፍክፋበት ከቤት ወጡ።

አካብዴ ከቀኝ ብርቋ ከግራ ሆነው የአብስራ መሀል ሆና ወደ ፕሮግራሙ በታክሲ ሄዱ።እንደ ደረሱም ከታክሲው ወርደው ወደ ውስጥ ሲገቡ በልደቱ ላይ የነበሩት ወንዶችና ሴቶች በሙሉ አይናቸውን በየአብስራ ላይ ጣሉ። ማንሳትም አልፈለጉም።ከመግቢያው እስከ መቀመጫው ወንበር ደርሳ እስክትቀመጥ ድረስ የሁሉም ሰው አይን የአብስራን እየተከተለ ነበር። ገብታ ተቀምጣ ተኮሳትራ ስታያቸው ሁሉም አንድ በአንድ ዞሩ።

የአብስራና ጓደኞቿ ከተቀመጡበት ወንበር ኋላ የተቀመጡ ሁለት ሴቶች በለሆሳስ"አንቺ የለበሰችው ልብስ አያምርም?ጫማዋስ ብትይ፣የያዘችው የእጅ ቦርሳ አይተሽዋላ"አለች አንዷ
ሁለተኛዋም ቀበል አድርጋ"አው ውይይይይ ወይኔ የአብስራ ታድላ"አለች
የመጀመሪያዋም አስከትላ"ግን ምን ያደርጋል፣ጠቋራ ሆነች፣ደግሞ ሰሟን የአብስራ አሉ፣መልከ ጥፋን በስም ይደግፋ አለ የሀገሬ ሰው"አለችና ሁለቱም "አሀሀሀሀ............ኡ....ሀሀሀሀሀ" ብለው ተሳሳቁ።ያወሩት በሙሉ አንድም ሳይቀር የአብስራ ጆሮ ውስጥ እየገባ ነበር።መጀመሪያ ያወሩት ደስ ቢላትም ግን በመጨረሻ የተናገሩት ጎዳት።
ወዲያውም ስትገባ የነበራት በራስ መተማመንና ኩራት ጠፋ።ተነስታ እየተወራጨች እንቧዋን ለመቆጣጠር እየሞከረች ወጣች።ግን አልቻለችም። እንደወጣች እንቧዋን ለቀቀችው። እየተወራጨችም ስትወጣ ወደ ውስጥ ያስገቧት አይኖች ለመሸኘትም አልቦዘኑም ነበር።ጓደኞቿም ግራ በመጋባት እየተከተሏት "ምን ሆነሻል? ኧረ አታልቅሺ!ቆይ ምን ሆነሻል?"እያሉ የሆነችውን ለማወቅ ይጎተጉቷታል።

...............አንድ ቀጣይ ክፍል ይቀረዋል

20 last posts shown.