ወንጌል በስነ-ፅሁፍ


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


አላማችን በስነፅሁፍ ወንጌልን ለአለም ሁሉ ማድረስ ነው ። የተፈጠርንለትም አላማ ነውና!
-ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ
-ግጥም
-አዳዲስ ዝማሬዎች
-ወግ ሌሎችንም ያገኙበታል
ማንኛውንም ሀሳብ አስተያየት ለመስጠት
እንዲሁም አብሮ ለማገልገል በዚህ ያናግሩን።
@AksanAdane
chanal created January/ 30/2020

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter






🧿በተለያዩ የሀገራችን ቋንቋዎች የተዘመሩ መዝሙሮችን በቻናላችን ላይ ማድረስ ልንጀምር ነው

🇪🇹በየትኛው የሀገራችን ቋንቋ የተዘመሩ መዝሙሮችን ማግኘት ይፈልጋሉ⁉️

       ✴️ምረጡ✴️
የሚመጣላቹን መንፈሳዊ ቻናል በመቀላቀል በመዝሙሮቹ ይባረኩ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇


የሆነ ቦታ የሆነች የተረጋጋች ሴት ያለች ይመስለኛል። የሰውን ትኩረት የማትፈልግ ናት፤ ሰዎች እንዲወዷት የተለየ ነገር የማታደርግ የራሷን ኑሮ የምትኖር ናት።

ህይወቷ በእውነት እንጂ በፈጠራ ድራማ ያልተሞላ ፤ በሰዎች የህይወት ጉዞ ላይ ባለ አዎንታዊ አስተዋፅኦ አድራጊ የምትሆን ናት። የተሰማትን የፈለገቺውን ደስ ያሰኛትን የምታደርግ ፤ ምታደርገው የማይፀፅታት ናት።

ምድር ላይ ያለውን የህይወት ብሶቷን አልያም ችግሯን ለመግለጥ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ወ'ታ ከመንዘባዘብ ይልቅ ከአምላኳ ጋር የምትነጋገር። ስለራሷ እሷ እና አምላኳ ብቻ የሚያውቁ። ይህቺ ሴት ብርቱ ናት።

ለጓደኝነት ትመቻለች። ነፃነት ትሰጣለች። ለጊዜያዊ የፍቅር ግንኙነት ታስፈራለች። ወንዶች ይጠነቀቁላታል። የትኛውም ወንድ ደፍሮ ሌላዋን ሴት በሚያወራበት መልኩ ይቺን ሴት ሊያወራት አይችልም። ልባም ናት። ለዘላቂ ትዳር የምታስተማምን ሴት!! የቤቱ ራስ መሆን የሚችል ፣ ሚስቱ እንድትገዛለት ሆኖ መኖር የሚችል ባል የሆነ ወንድ የሚመኛት እና የሚያገኛት ሴት ናት።

ይህቺ ሴት ብርቅ ናት ! ፀሎቷ ልኬት ያለው ይመስለኛል። ከሚያስፈልጋት በላይ እንዲሰጣት አትለምንም። ተመስገንን ታውቃለች በተሰጣት አታማርርም ።

✍️ Zerfu Bolade


💐
💐 @wengelbeArt 💐💐


"ከአንተ ሚጠበቀውን የእግር ውሃ ረስተህ
የአልባስጥሮስ ዋጋ መወደዱ ደንቆህ
ይህች ሀጢያተኛ ብሎ ከማናናቅ
ቤትህ የተገኘውን ኢየሱስን ማላቅ....

✍Aksan Adane
💐💐
@wengelbeArt 💐💐


ቅድመ-ፍልስፍና

ፈላስፋ ተነስቶ እግዜር የለም ካለ
አምላክ የለም ካለ
ፈላስፋው ልክ ነው
እግዜር ነው ፈላስፋው
ምክንያቱም................
እግዜር.. አንዱን አስነስቶ
አፋን በቃል ከፍቶ
እግዜር አለ ብሎ.. ሊያናግር ሲሻ ነው
ያን- የለም አስብሎ.. ቀድሞ ሚያናግረው

ድንቅ ግጥም👏👏👏👏👏👏👏

#ኑ_ግርግዳ_እናፍርስ_ከሚለው_ከኤፍሬም_ስዩም_የግጥም_መድብል_ከገጽ_24_የተወሰደ

እናንብብ






"ቀንበሬን!!"
ብቻችሁን አይደላችሁም

የሀገሬ ልጆች አንድ ነገር ላውጋችሁ በዋነኝነት የሠማዩ አባቴ ልጆች :: በመቀጠልም ኢትዮጵያውያዊ የሆነ አብዛኛው ሰዉ የሚያውቀው ድርጊት አለ::
መሬት ሲታረስ በሁለት በሬ መሆኑን ሁላችንም እናውቃለን:: በሁለቱ ትከሻ ላይ
ቀንበር ይደረጋል ::አንደኛው ብቻውን አይሆንም ::
አንድ ብርቱ የእኔና የእናንተ ድካም ፣በኃጢያት መጉበጣችን ፣ባርነታችን አላስችል ብሎት አምጡት ልሸከመው ብሎ ተቀበለን ::
ጠራ ደካሞችን ሊያሳርፍ::
ብሎም የእራሱን ቀሊል ልዝብ ቀንበር አሸከመን::
አሸክሞ ዞር ላይል ቀንበሬን ተሸከሙ ብቻችሁን አይደለም::
እኔም አለሁ ።በክርስትናው ጎዳና ስትዝሉ፣ ዳገቱ ሲያደክማችሁ ፣እሾሁ ሲወጋችሁ አለሁ አብሬ። መከራ እንደሚቀበል መሲህ ስናየው ካለንበት ተስፋ መቁረጥ እንወጣለን::
እየመራ ፂዮን ሊያደርሰን አለ ከእኛ ጋር ::

ብቻችሁን አይደላችሁም!!

ከእኔ ተማሩ እኔ የዋህ በልቤም ትሁት ነኝ!! ከእርሱ እንማር ::
ማቴዎስ 11
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁸ እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ።
²⁹ ቀንበሬን በላያችሁ ተሸከሙ ከእኔም ተማሩ፥ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤
³⁰ ቀንበሬ ልዝብ ሸክሜም ቀሊል ነውና።

✍Aksan Adane

💐💐
@wengelbeArt 💐💐


ደጋሹን የማያውቅ አስተናጋጅ
ደጋሹን ከበር ያቆመዋል!!
💐💐
@wengelbeArt 💐💐


       ትርፍ አልጭንም!!
ለመዳን ለማረፍ ወደ አብ ለመግባት ፣
ከፍርድ ለማምለጥ ለመትረፍ ከመ ሞት፣
ይሄም ይጨመራል ይሄም ያስፈልጋል፣
የቅዱሳን ምልጃም ሚና ይጫወታል፣
    እንጂማ ኢየሱስ ብቻውን አይበቃም፣
    በስራሽ ነው እንጂ ያለዚያ አይዳንም፣
    አሉኝ ሊያሞኙኝ በከንቱ ሊያስመኩኝ፣
    ያንንም ያንንም መሸከም ቀርቶብኝ፣
   በእርሱ በማመኔ ለመንግስቱ አጨኝ።
የደካሞች ጌታ ሸክሜን ወሰደው፣
ጠራኝ ሙሽራዬ ታሪኬን ቀየረው።
የፍቅሩን ቀንበር ልዝብ አሸከመኝ፣
ብቻዬን እንዳልሆን ከእኔ ጋር አለልኝ ።
     በቅቶኛል ኢየሱስ ሌላ አልፈልግም፣
     የሞላ የሞላ ብዬ ትርፍ አልጭንም! ።
#እኔ ምስክርነኝ ✍Aksan Adane
💐💐 @wengelbeArt 💐💐


''...ነፍሰ-ጡሯ የፊንሐስ ሚስት...''

ሰሞኑን አንዳች ሥራ ጀምሬ ወትሮ እንደማደርገው የግል የመጽሐፍ ቅዱስ የጥናት ጊዜዬን ለመከወን እጅግ ተቸግሬ ነበር። ያው ሙሉ በሙሉ ጥናቴን ባላቆምም እንደበፊቱ ሰፊ ሰዓት የማንበቡ እና የማሰላሰሉ ዝንባሌዬ ርቆኛል። ሆኖም ጌታ እረድቶኝ በማገኛት ጥቂት ጊዜ ከአባቴ የተካፈልኩትን ወዳጆቼን ላጋራችሁ ሻትሁ።

ዛሬስ ምን ሊለኝ ይሁን በሚል አይነት የገጉት መንፈስ የናፈቀኝን አምላክ ቁም-ነገር ልካፈል የማጥኛ ጠረጴዛዬ ዘንድ ሰፈርሁ። በአንዲት ቅፅበትም የመከራ ዶፍ የዘነበባትን አንዲት ሴት ተጨባበጥኩኝ። ይህች ሴት ነፍሰ-ጡሯ የፊንሐስ ሚስት ነች። የነፍሰ-ጡር'ነቷ ወር ይነጉዳል። የምትወልድበትም ዘጠነኛው ወር እደጇን እያንኳኳ ነው።

ይህ አይነት ጊዜ ለሴት ልጅ ምን ያክል የጭንቅ ጊዜ እንደሆነ ግልጽ ነው። ታዲያ በዚህ ጊዜ ለሴቲቱ የቤተሰቦቿ አጠገብ መሆን ትልቅ አስተዋጽኦ አለው። ሆኖም በዚህ ጊዜ ከሚያበረታ ድምጽ ይልቅ አጥንት የሚሰብር መርዶ ይደርሳታል።(1ሳሙ:-4v19) የእግዚአብሔር ታቦት መማረኩ፣ የዐማቷ እና የባሏ የመሞት ዜና ጆሮዋ ዘንድ ደርሷል። ይህንም ስትሰማ እጅግ ተብረከረከች። ምጡ ጠናባት! ለመሞት ማጣጠር ጀመረች። ካለችበት ብርቱ የወሊድ ምጥ ላይ ሌላ ነፍስን አፍኖ የሚገድል ምጥ ተደመረባት። አይደለም ወልዶ መሳም ለመኖር እንኳን ተስፋን አጣች።

ታዲያ ለሞት በምታጣጥርበት ጊዜ ማንም ሌላ ተስፋ አይታየውም። አዋላጆቿም በታላቅ ስጋት ውስጥ ሊኖሩ እንደሚችሉ መገመቱ አይከብድም። ሆኖም በዚህ ጠንከር ባለ የሀዘን ጊዜ አንዳች ተስፋን የሰነቀ ድምፅ ይደርሳታል። ''አይዞሽ ወንድ ልጅ ወልደሻል።''(1ሳሙ:-4v20) የሚል ድምፅ!! ይህንን ቁጥር ሳነበው በአንዲት ቅፅበት የመርዶ መዓት የጎረፈባትን ሴት በርህራሄ ልብ አሰብኳት። አጠገቤ እንዳለች ያክል እያሰብኩኝ ''እንኳን ጌታ ካሰሽ አልኳት።'' ምንም እንኳን የህይወት አጋሯን፣ አማቷን ብታጣም፤ በአዲሱ በእግዚአብሔር ስጦታ ልትፅናና እንደምትችል በማሰብ እጅግ ደስ አለኝ። በማስታወሻ ደብተሬ ላይ'ም 'እግዚአብሔር ይክሳል' በሚል ርዕስ ትምህርት መስራት እንዳለብኝ በማሰብ ቀጣዩን ቁጥር ማጥናቴን ቀጠልኩኝ።

ቀጣዩ ቁጥር ግን ይልቁን አወዛገበኝ። ነፍሱ-ጡሯ ይልቁን ስትከፋ አገኘኋት። ለሰማቺው የምሥራች የሚመጥን የደስታ ምላሽ ሲጠበቅ ቅንጣት ታክል እንኳን ፈገግ ስትል አትታይም። ( ''እርሷ ግን መልስ አልሰጠችም፤ ልብ ብላም አላደመጠችም።''(1ሳሙ:-4v20) እርግጥ ነው በአንዲት ቅፅበት የደረሳት መርዶ አደናብሯታል። ቢሆንም በዚህ ሁሉ መሃል አምላክ ልጅ እያስታቀፋት፣ እየካሳትም ነው። እርሷ ግን ወይ ፍንክሽ ስትስቅ አትታይም። ታዲያ እኔም ዝብርቅርቅ ባለ ስሜት ወደ ቀጣዩ ቁጥር አቀናሁ።

ቀጣዩንም ቁጥር ደጋግሜ አየሁት። አንዳችም ቁም-ነገር ነፍሴን ይኮረኩራት ጀመር። ለካ ነፍሰ-ጡሯ እንዲያ የሆነቺው በዚህ ምክንያት ነው የሚል መገለጥ ነፍሴን ጠፍንጎ ያዛት።

1ሳሙ:-4v21 :- "የእግዚአብሔር ታቦት ስለተማረከ፣ ዐማቷና ባሏም ስለሞቱ፣ "ክብር ከእስራኤል ተለይቷል " ስትል የሕፃኑን ስም ኢካቦድ አለችው።

የዚህን ቁጥር ሀሳብ ሳገኝ ስክን አልኩኝ፤ እጅግ ተረጋጋሁ። የቅድሙን ደስታ ሁሉ ጣልኩኝ። የሠራሁትን ትምህርት አፈረስኩኝ።

ጉዳዩ ወዲህ ነው፦ ለካ ነፍሰ-ጡሯ በልጅ የማይካስ ሀዘን ነፍሷን በጦር ወግቷታል። ይህ ሀዘን የእግዚአብሔር ታቦት በመማረኩ የመጣ ነው። የቁ'21'ን የሀሳቡን ቅደም ተከተል እና 'flow' ስናይ የሚነግረን ይህንኑ ነው። የእግዚአብሔር ታቦት ማለት የእግዚአብሔር አብርሆት ማለት ነው።

ነፍሰ-ጡሯ አንድ እውነት ገብቷታል:- ልጅ በልጅ ይተካ ይሆናል። እግዚአብሔር ግን በምን ይተካል? በምንም አይተካም!!!

ነፍሰ-ጡሯ ሴት:- ሕፃኑን ልጇን ካለችበት ትልቅ ሀዘን እንደመፋቺያ መፍትሔ ስትቀበለው አናያትም፤ እንዲያውም ይልቁን ሀዘኗን የምታስታውስበት ማስታወሻ አድርጋ ስሙን ኢ-ካቦድ አለቺው። ኢካቦድ ማለት ክብር ከእስራኤል ተለይቷል ማለት ነው።

የእግዚአብሔር ክብር ተለይቶ የምን surprise አለ? የለም!!!

ተወዳጆች ሆይ:- ገንዘብ ቢጠፋ በገንዘብ ይካሳል፤ ሰው ቢሄድ ሰው በሰው ይካሳል፤ በዚህ ምድር ላይ ያለ የትኛውም ነገር መተኪያ ሊኖረው ይችል ይሆናል።

የእግዚአብሔር አብርሆት ግን በምን ይተካል?

ነፍሰ-ጡሯ የፊንሐስ ሚስት የገባት እውነት ይግባን!!!

✍️ Tesfatsion Feleke

💐💐
@wengelbeArt 💐💐


አይደለም በሙዚቃ በጦር መሳሪያ......!🔫
(ሰውሁን በለው"አቤኒ")

ትንሽ ዘግየት ብሏል ከአንዲት ልጅ ጋ ተያየን። አየኋት አየችን።ከዛም ገላምጣኝ ዞረች።እኔም ምን አስገላመጣት የሚለው ጥያቄ ውስጤን አብከነከነው።ለካስ ኋላ ላይ ስረዳው የመማረኪያ አመሏ ነው።ከቆይታ በኋላ በጓደኛዬ ምክንያት Hi Hi መባባል ጀመርን።አንድ ቀን ጓደኞቼን ስለ መጸሀፍ እያወሯዋቸው አንድ ያላነበብኩትን መጸሀፍ ስም ጠርተው እንዳነበቡት ሲነግሩኝ መጸሀፋን የት ላገኝ እንደምችል ጠየኳቸው።እናም መጸሀፋ የገላመጠችኝ ልጅት መሆኑን ነገሩኝ።ማናገሩም ቢደብረኝ የመጸሀፍ ነገር ሆኖ አላስችል አለኝና አወራዋት፡ችግር የለውም ውሰድና አንብበው አለችኝ፡በሁለት ቀን አንብቤ መለስኩኝ።እንደገና ሌላ መጸሀፍ ሰጠችኝ በ1ቀን አንብቤ መለስኩላት፡አደነቀችኝ፡ከዛም ሌላ መጸሀፍ ፡ በቃ መጸሀፍ አግባባን..............
እየተቀራረብን ስናወራ ልጅት ወሬዋ ሁሉ ስለ ሀይማኖት ሆነ።ስንገናኝም፣በቴሌግራምም፣ በስልክም.........ብቻ በተገኘው አጋጣሚ ወሬዋ ስለ ሀይማኖት ነው።እኔም እኔ ጋ ያለውን እርሷም እሷ ጋ ያለውን የሀይማኖት ነገሮች Share እንደራረግ ጀመር።በመሀል ከዕለታት አንድ ምሽት የፕሮቴስታንት መዝሙር ላኩላት። እሷም የእኛን የአዘማመር ሁኔታ አቃቂር ለማውጣት ተሰለፈች።እኔስ ማን ብሎኝ ዘራፍ የፓ/ር ...... ልጅ ዘራፍ ለአምልኮ ዘራፍ............
መዝሙሩን ሰምታ(የጨረሰችው እንኳን አይመስለኝም)"እንዲ አይነት በሙዚቃ መሳሪያ የተቀነባበረ መዝሙር አትስማ ከዚያ ይለቅ በበገና፣በከበሮ ፣በመሰንቆ፣በክራር እና እነዚህን በመሳሰሉት በቤተ ክርስቲያን ስርዓት ምናምን ባላቸው የተሰሩ መዝሙሮችን አዳምጥ እንጂ በሙዚቃ መሳሪያ ምናምን ኧረረ.........."
ይችን ይወዳል የ..............ልጅ ምን
የተናገረችው ነገር በጣም አናደደኝ ያዙኝ ልቀቁኝ (ውይ ብቻዬን ነኝ ለካስ)ዘራፍ.........እምቢ ለሚልኮን እምቢ..........ይህች የሚልኮን ልጅ የሚልኮን አልጋ ወራሽ(ሚልኮን ስል በቀጣይ በእሷ ዙሪያ ጽሁፍ ይጠበቅ)።
እናም ጨጓራዬ እየተቃጠለ፣አንጀቴ እያረረ ምን እንደምላት ማብሰልሰልን ተያያዝኩት🤔🤔🤔
አእምሮዬ ውስጥ የሚመጣው የዳዊት አምልኮ ሀገሬው ያከበረው ንጉስ ሆኖ ሳለ(በድሮ ግዜ ንጉስ እንደ አምላክ ነበር የሚታየው)ዳዊት ግን ክብሩን:ዝናውን፣ማንነቱን፣ንግስናውን ረስቶ፡ በጌታ መንፈስ ሰክሮ፡ሰው አየኝ አላየኝ ሳይል፡ እርቃኑን ጌታን እንዳመለከ ነው፦አእምሮዬ ውስጥ የሚመላለሰው።
ከዚያም የሚቀጥለውን መልዕክት ላኩላት

"ስሚ ዳዊት ንጉሡ እንኳን እርቃኑን አምልኮት አይደል እንዴ..እንኳን እኔ።አልሆንልህ ብሎኝ፣ ሰው ይደነግጣል፣ይሸበራል፣ሰላሙን መንካት ይሆንብኛል ብዬ እንጂ አይደለም በሙዚቃ መሳሪያ በጦር መሳሪያ እንኳን እያንደቆደኩ ባመልከውስ...................

ሰው ዝም ብሎ ይከራከራል፤
ጌታን ለማምለክ ቅርፅ ያወጣጣል፤
አንዱ እንዲ ሲል አንዱ እንዲያ ይላል።
አምልኮ ለጌታ ነው ሰው ምን ነክቶታል፤
በመንፈስ ይሁን እንጂ አምላኬ ተቀብሎታል።....


💐እግዚአብሔር በልጁ ልደት ሳመን፨፨፨🎄


#ከዘላለም ዘመን በፊት በቅድመ ዓለም #ባለመለወጥና ባለ መለየት በባሕርይ መስሎ በአካል አህሎ #ያለ _ እናት የተወለደው የእግዚአብሔር አብ ልጅ #ከዘላለም ዘመን በኃላ በድኅረ ዓለም በሰው አምሳል ሰውን አህሎ #ያለ_አባት ከድንግል ማሪያም ተወለደ (ገላ.4፥4)።

#ተቀዳሚም ተከታይም የሌለው #የእግዚአብሔር አንድያ ልጅ #በቃል ወደ ፈጠረው ዓለም #በእግሩ መጣ #በሰራው ኃጢአት ምክንያት ከገነት ወደ ምድር ያስወጣውን ሰው #ፍቅር ግድ ቢለው ተከትሎት ወጣ #በዓፀደ ገነት በድምፁ ፍለጋ የጀመረውን ዓዳም #በገፀ ምድር ወርዶ በስጋው አገኘው።

#የኢየሱስ ክርስቶስ መወለድ የአንድ ሰው ወደዚህ ዓለም መቀላቀል አይደለም፤ #የማይታየው አምላክ በሥጋ የተገለጠበት #ዲያብሎስ ዱካ አጥፍቶ ገነት ዘልቆ #ዓዳምን አታልሎ ወደ ዓለም ባስገባው ኃጢአትና ሞት #የፈቃዱ ባሪያ ያደረገውን #የሰው ዘር በሞላ በገዛ ደሙ ሊቤዥ #እግዚአብሔር የሄደበት የፍቅር ጥግ #ረቂቅ ምስጢር ነው።

#በዚህ ዓለም አሰከ-አሁን 1.8 ትሪሊዮን ገደማ ህጻናት ተወልደዋል #ነገር ግን ሁሉም የተወለዱት ለእራሳቸው ነው፡፡#ኢየሱስ ክርስቶስ ግን የተወለደው ለእኛ ነው #በጨለማ ለሚኖሩት ብርሃን #በሞት አገርና ጥላ ላሉት ሕይወት ሊሆን ነው፡፡(ኢሳ.9፥6)።

#የዘላለም አባት ሳለህ #ህጻን የተባልህ #ዓለማትን በመዳፍህ ይዘህ #በድንግል አቅፋ ያደርህ #ሰማየ ሰማያት የማይችሉህ #በመጠቅለያ የታጠፍህ #እኛን በእጅ ባልተሰራ ቤት ልታሳድር #አንተ በግርግም ያደርህ #ፅድቅ የሞላበትን ሰማይ መኖሪያህን ለእኛ ሰጥተህ #ኃጢአት የበዛበትን ምድር የከተብህ #የቆሙ መላዕክት ክብርና ውዳሴ ሳይማርክህ #የወደቁ ሰዎች ኃጢአትና ሞት ያስጨነቀህ #ለዘላለም የፀናው ዓለምህን ትተህ #በቅፅበት የወደቀውን ዓለም #ልታነሳ መጣህ።...
#እወድሃለሁ።

#ከዘላለም ሞት ሊያድነን በተወለደው #የቤዛነት ሥራ አምኖ ዳግም በመወለድ እንጂ #ልደቱን በማክበር የሚመጣ ብፅዕና የለም፡፡#በቤተልሔም የተወለደው #በልባችን ሲወለድ የዘላለም ሕይወት ይሰጠናል።


💐💐 @wengelbeArt 💐💐
💐💐
@wengelbeArt 💐💐


ልደት
ሰለሞን ቡላ
🎁 መልካም ገና 🎁
💐💐 @wengelbeArt 💐💐
💐💐 @wengelbeArt 💐💐


ልዑል ተወለደ
A.A MKC Choir
🎁 መልካም ገና 🎁
💐💐 @wengelbeArt 💐💐
💐💐 @wengelbeArt 💐💐




መጽሐፍ ቅዱሴን ባለማንበብ ሰይጣን እንዲጫወትብኝ አላግዘውም።

💐💐
@wengelbeArt 💐💐


ሳልወለድ አይቶኝ በፍቅሬ ወደቀ
እንዲሁ ራርቶልኝ እርቃኑን ደቀቀ
ፍቅር ፍቅሬ ይዞት ከላይ አስገድዶት
ዝም ብሎ ወደደኝ ያለ ምንም ምክንያት
ሰው ሁሉ ማይወደኝ ክፉ በደለኛ
ሀጥአት የበዛብኝ ምድር ምፃተኛ
የነበርኩኝ እኔን እራሱ ወደደኝ
ለክብሩ ቀይሮኝ አንቺ የኔ ነሽ አለኝ።

ያለተስፋ ምኖር የነበርኩኝ እኔ
ለህይወቴ ትርጉም መውጫ ያጣሁ እኔ
ዛሬ ደረሰልኝ መድህን መጣልኝ
በምድር እያለሁ ሰማይ አደረሰኝ

…………………✍ሜriታ የኢየሱስ ልጅ

💐💐 @wengelbeArt 💐💐



20 last posts shown.