እንደህዝብ አሸናፊ የሚያደርገንን ብቸኛ የአንድነት መንገድ በቶሎ መማተሩ ይበጃል!
በአማራ ህዝብ የህልውና ትግል ውስጥ ፤ በፍፁማዊ ጥላቻና በበቀለኝነት ስሜት የታወረ ፣ የሆኑ አካባቢዎችን ''ጠላት ፣ ፀረ-እነሱ ፣ መጥፋትና መደምሰስ ያለባቸው ፥ ወዘተረፈ '' ብሎ የፈረጀና ፣ ይህን የተፈረጀ የማህበረሰብ ክፍል ሁለንተናዊ እሱነቱን ለማኮላሸት ፣ በእሱ ላይ ፈላጭ ቆራጭ ሆኖ ለመታየት ፣...ወዘተ ሲል ፣ ከሰይጣን ጋርም ቢሆን አብሮ ለመቆም የማያመነታ ፣ እኩይ ፍላጎቱን ይዞ በመንደር (ጎጥ) ውስጥ የተወሸቀ ፣ ጥቂት የግለሰቦች ስብስብ እንዳለ የማይካድ ሀቅ ነው!
ይህ ቡድን መሻቱን እውን ለማድረግ የአማራ ህዝብ አሳቢ በመምሰል ለመታየት ቢሞክርም ፣ የአማራ ትግል በአፍጢሙ ቢደፋ ደንታ የሌለው ፣ አሁን ህዝባችን እንደፖለቲካ ማህበረሰብ ይኖርበታል ተብሎ ተሰፍቶ የተሰጠው ክልላዊ መዋቅር እንኳ ''መፍረስና መሸንሸን አለበት' ብሎ የሚያምን ፥ ይህን ለማሳካትም ፣ ይህን አማራውን በጎጣዊ ማንነት የተሸነሸነ የፖለቲካ ማህበረሰብ እንዲሆን ማድረግን የፖለቲካ ግባቸው አድርገው ከሚንቀሳቀሱ አካላት ጋር (መንግስትን ጨምሮ) አብሮ የሚሠራ ፣ ከትህነግ ጋር በተለያዩ የመንግስታዊ መዋቅሮች ውስጥ አብሮ እየሰራና እየተደራደረ እንኳ የአማራን ህዝብ ትግል ''የወያኔ'' እያለ ለመፈረጃነት የሚጠቀም አደገኛ አመለካከት የታጠቀ ቡድን ነው!
ታዲያ! ይህ ቡድንን ከማህበረሰብ ፣ ከተቋምና ከአደረጃጀቶች ውስጥ በጥንቃቄ ነጥሎ ማስቀረት ትልቁ የፖለቲካ ብስለት የሚጠይቅ ስራ ነው! ይህን ቡድን የብዙሀኑ ማህበረሰብ መፈረጃ ካደረክ ፣ ይህን ቡድን ለማጋለጥም ሆነ ለመታገል ስትል አነጣጥረህ የምትወረውረው የሀሳብ ቀስት ፥ ሌላውን ከነካብህና ይህ ቡድን ትግልህን ለመከፋፈል ብሎም ሀይል ለማሰባሰብ እንዲጠቀምበት ካደረግክ ፣ የዋናውን ህዝባዊ ትግልህን የአሸናፊነት መሠረት በቀላሉ እንዲናድ እያደረክ መሆኑን መገንዘብ ያሻሃል! ምክንያቱም የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ በአሸናፊነት ለመጠናቀቅ የቀረው ነገር ህዝባዊ አንድነትን አጠናክሮ አንድ ተቋማዊ ቅርፅ ባለው የሀይል አሰላለፍ በመሰተር ፣ ''የፖለቲካ ኃይል'' ሆኖ ድሉን ወደፍሬ መቀየር ብቻ ስለሆነ ነው!
ከዚያ ውጪ የአማራ ህዝብ ትግል በአውራጃዊና ቡድናዊ መከፋፈል ውስጥ ሆኖ የፈለገ ግዙፍ ሰራዊት ቢኖረው ፣ አውደውጊያዎችን ቢያሸንፍ ፣ የቱንም ያህል የፐርሶኔልና የሎጅስቲክ አቅም ቢያካብት ፣ ''ኃይል'' ሆኖ ለአማራ ህዝብ ጥቅምና ፍላጎት የሚደራደር ፣ ህዝቡ የተቃጣበትን የህልውና አደጋ ቀልብሶ ከጦርነት ማግስት ህዝባዊ አስተዳደር እንዲኖረው የሚያደርግ ሀይል መሆን አይቻለውም! 'እታገላለሁ' የሚለው ሀይል ሳይቀር ፥ ራሱን ወደማይታደግበት ደረጃ እንዲወርድ በራሱ ጊዜ በር ከፋች ይሆናል!
ይህ ደግሞ ከላይ የጠቀስኳቸው ጥቂት ቡድኖች ግብና ፍላጎት ነው! በየትኛውም መመዘኛ የአማራ ህዝብ ትግል አሸናፊ የሚያደርገውን አንድነትን የተላበሰ ተቋማዊ ትግል እውን እንዲሆን የማይሰራ ፣ በየፊናው የሚወራጭና እርስበርሱ የሚፈላለግ አደረጃጀት ሁሉ ፣ በአንደበቱ ''ለአማራ ህዝብ እታገላለሁ!'' ቢልም ፣ ከዚያም አልፎ የህይወት መስዋዕትነት ሁሉ የሚከፍል ቢሆንም ፣ አማራውን ' ተሸናፊ ' በሚያደርገው አሰላለፍ ውስጥ እስከተገኘና ፥ የራሱን ፍላጎትና ስሜት እስካልገራ ድረስ ፣ ከላይ ከጠቀስኳቸው በየመንደሩ ተቧድነው ጥላቻና በቀለኝነትን ታጥቀው ፣ ለአማራ ህዝብ ትግል ተውሳክ ከሆኑ ቡድኖች የተለየ ሊሆን አይችልም!
ስለዚህም መሠል ተውሳክ ቡድኖችን ከትግሉ ነጥሎ ለማስቀረትና ለማጋለጥ የሚደረገው እንቅስቃሴ ፍፁም ፖለቲካዊ ብስለት የታከለበት ሊሆን ይገባል! ብቻቸውን ነጥሎ ራቅታቸውን የሚያስቀር ብሎም መደበቂያ የሚሆን ማህበረሰባዊ ዋሻና ከለላ የሚያሳጣ ፣ በአርቆ አሳቢነት የሚከወን መሆን ካልቻለ ፣ በገዛ ቀስትህ አዙረው እንዲወጉህ ፣ ኃይል ማሰባሰቢያ እንዲያደርጉት ፣ የትግል አደረጃጀትህን ወደብዙ ትናንሽ ህዋስ እንዲከፋፍሉብህ ብሎም ''እንድትታረቅ ሆነህ ተጣላ '' እንዲሉት ብሂል ፣ በእነሱ ሳቢያ ከተከፋፈለው የገዛ ወገንህና የትግል ሀይልህ ጋር እንኳ ፣ ዳግም ተመልሰህ ለመነጋገርና መወያየት እንዳትችል አድርገው እንዲያራርቁህ እድሉን ትሰጣቸዋለህ ማለት ነው! ይህ ሁኔታ አሁንም በጉልህ እየተስተዋለ ነውና ልብ ያለው በቶሎ ልብ ሊለው ይገባል!
ውግንናችንና የምንከተለው ፦ አንዱ በአንዱ ሲስቅና ሲሳለቅ የምንደሰትና የምንከፋበት ፣ ተቋማዊነት ተዘሎ ቡድናዊ (መንደራዊ) አደረጃጀቶችና ግለሰቦች የሚገኑበት ብሎም የትርምስ ማእከል የሚሆኑበት ፣ ማንም ገብቶ እንዲፈተፍትበት ክፍት የተተወውና አሸናፊ የማያደርገን አዋራጅ መንገድ ሳይሆን ፣ እንደህዝብ ከተቃጣብን የህልውና አደጋ ታድጎ ፣ የህዝባችንን ጥቅምና ፍላጎት ተደራድሮ ለማስከበር የሚያስችለውን ፣ እንደህዝብ አሸናፊ የሚያደርገንን የህብረትና የተደራጀ ህዝባዊ ተቋማዊ የትግል መንገድ ሊሆን ይገባል!
አሁንስ ፈጣሪም ፦ ልቦናችንን ክፍት አድርጎ ፣ በሰማይ በምድር ያለእረፍት እሳት እየዘነበበት ላለው ህዝባችን ፣ ዋስትና የሚሆንና አሸናፊ የሚያደርገውን የትግል መስመር እንድንመለከት ይርዳን!
በቅንነት የምታነቡኝ በግርድፉ ያቀረብኳቸውን ነጥቦች ፣ ከነባራዊው አውድ ጋር በማሰናሰን ሰፋ አድርጋችሁ ግንዛቤ ትወስዱበታላችሁ ብዬ አስባለሁ!
ሠላማችሁ ይብዛ!
በአማራ ህዝብ የህልውና ትግል ውስጥ ፤ በፍፁማዊ ጥላቻና በበቀለኝነት ስሜት የታወረ ፣ የሆኑ አካባቢዎችን ''ጠላት ፣ ፀረ-እነሱ ፣ መጥፋትና መደምሰስ ያለባቸው ፥ ወዘተረፈ '' ብሎ የፈረጀና ፣ ይህን የተፈረጀ የማህበረሰብ ክፍል ሁለንተናዊ እሱነቱን ለማኮላሸት ፣ በእሱ ላይ ፈላጭ ቆራጭ ሆኖ ለመታየት ፣...ወዘተ ሲል ፣ ከሰይጣን ጋርም ቢሆን አብሮ ለመቆም የማያመነታ ፣ እኩይ ፍላጎቱን ይዞ በመንደር (ጎጥ) ውስጥ የተወሸቀ ፣ ጥቂት የግለሰቦች ስብስብ እንዳለ የማይካድ ሀቅ ነው!
ይህ ቡድን መሻቱን እውን ለማድረግ የአማራ ህዝብ አሳቢ በመምሰል ለመታየት ቢሞክርም ፣ የአማራ ትግል በአፍጢሙ ቢደፋ ደንታ የሌለው ፣ አሁን ህዝባችን እንደፖለቲካ ማህበረሰብ ይኖርበታል ተብሎ ተሰፍቶ የተሰጠው ክልላዊ መዋቅር እንኳ ''መፍረስና መሸንሸን አለበት' ብሎ የሚያምን ፥ ይህን ለማሳካትም ፣ ይህን አማራውን በጎጣዊ ማንነት የተሸነሸነ የፖለቲካ ማህበረሰብ እንዲሆን ማድረግን የፖለቲካ ግባቸው አድርገው ከሚንቀሳቀሱ አካላት ጋር (መንግስትን ጨምሮ) አብሮ የሚሠራ ፣ ከትህነግ ጋር በተለያዩ የመንግስታዊ መዋቅሮች ውስጥ አብሮ እየሰራና እየተደራደረ እንኳ የአማራን ህዝብ ትግል ''የወያኔ'' እያለ ለመፈረጃነት የሚጠቀም አደገኛ አመለካከት የታጠቀ ቡድን ነው!
ታዲያ! ይህ ቡድንን ከማህበረሰብ ፣ ከተቋምና ከአደረጃጀቶች ውስጥ በጥንቃቄ ነጥሎ ማስቀረት ትልቁ የፖለቲካ ብስለት የሚጠይቅ ስራ ነው! ይህን ቡድን የብዙሀኑ ማህበረሰብ መፈረጃ ካደረክ ፣ ይህን ቡድን ለማጋለጥም ሆነ ለመታገል ስትል አነጣጥረህ የምትወረውረው የሀሳብ ቀስት ፥ ሌላውን ከነካብህና ይህ ቡድን ትግልህን ለመከፋፈል ብሎም ሀይል ለማሰባሰብ እንዲጠቀምበት ካደረግክ ፣ የዋናውን ህዝባዊ ትግልህን የአሸናፊነት መሠረት በቀላሉ እንዲናድ እያደረክ መሆኑን መገንዘብ ያሻሃል! ምክንያቱም የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ በአሸናፊነት ለመጠናቀቅ የቀረው ነገር ህዝባዊ አንድነትን አጠናክሮ አንድ ተቋማዊ ቅርፅ ባለው የሀይል አሰላለፍ በመሰተር ፣ ''የፖለቲካ ኃይል'' ሆኖ ድሉን ወደፍሬ መቀየር ብቻ ስለሆነ ነው!
ከዚያ ውጪ የአማራ ህዝብ ትግል በአውራጃዊና ቡድናዊ መከፋፈል ውስጥ ሆኖ የፈለገ ግዙፍ ሰራዊት ቢኖረው ፣ አውደውጊያዎችን ቢያሸንፍ ፣ የቱንም ያህል የፐርሶኔልና የሎጅስቲክ አቅም ቢያካብት ፣ ''ኃይል'' ሆኖ ለአማራ ህዝብ ጥቅምና ፍላጎት የሚደራደር ፣ ህዝቡ የተቃጣበትን የህልውና አደጋ ቀልብሶ ከጦርነት ማግስት ህዝባዊ አስተዳደር እንዲኖረው የሚያደርግ ሀይል መሆን አይቻለውም! 'እታገላለሁ' የሚለው ሀይል ሳይቀር ፥ ራሱን ወደማይታደግበት ደረጃ እንዲወርድ በራሱ ጊዜ በር ከፋች ይሆናል!
ይህ ደግሞ ከላይ የጠቀስኳቸው ጥቂት ቡድኖች ግብና ፍላጎት ነው! በየትኛውም መመዘኛ የአማራ ህዝብ ትግል አሸናፊ የሚያደርገውን አንድነትን የተላበሰ ተቋማዊ ትግል እውን እንዲሆን የማይሰራ ፣ በየፊናው የሚወራጭና እርስበርሱ የሚፈላለግ አደረጃጀት ሁሉ ፣ በአንደበቱ ''ለአማራ ህዝብ እታገላለሁ!'' ቢልም ፣ ከዚያም አልፎ የህይወት መስዋዕትነት ሁሉ የሚከፍል ቢሆንም ፣ አማራውን ' ተሸናፊ ' በሚያደርገው አሰላለፍ ውስጥ እስከተገኘና ፥ የራሱን ፍላጎትና ስሜት እስካልገራ ድረስ ፣ ከላይ ከጠቀስኳቸው በየመንደሩ ተቧድነው ጥላቻና በቀለኝነትን ታጥቀው ፣ ለአማራ ህዝብ ትግል ተውሳክ ከሆኑ ቡድኖች የተለየ ሊሆን አይችልም!
ስለዚህም መሠል ተውሳክ ቡድኖችን ከትግሉ ነጥሎ ለማስቀረትና ለማጋለጥ የሚደረገው እንቅስቃሴ ፍፁም ፖለቲካዊ ብስለት የታከለበት ሊሆን ይገባል! ብቻቸውን ነጥሎ ራቅታቸውን የሚያስቀር ብሎም መደበቂያ የሚሆን ማህበረሰባዊ ዋሻና ከለላ የሚያሳጣ ፣ በአርቆ አሳቢነት የሚከወን መሆን ካልቻለ ፣ በገዛ ቀስትህ አዙረው እንዲወጉህ ፣ ኃይል ማሰባሰቢያ እንዲያደርጉት ፣ የትግል አደረጃጀትህን ወደብዙ ትናንሽ ህዋስ እንዲከፋፍሉብህ ብሎም ''እንድትታረቅ ሆነህ ተጣላ '' እንዲሉት ብሂል ፣ በእነሱ ሳቢያ ከተከፋፈለው የገዛ ወገንህና የትግል ሀይልህ ጋር እንኳ ፣ ዳግም ተመልሰህ ለመነጋገርና መወያየት እንዳትችል አድርገው እንዲያራርቁህ እድሉን ትሰጣቸዋለህ ማለት ነው! ይህ ሁኔታ አሁንም በጉልህ እየተስተዋለ ነውና ልብ ያለው በቶሎ ልብ ሊለው ይገባል!
ውግንናችንና የምንከተለው ፦ አንዱ በአንዱ ሲስቅና ሲሳለቅ የምንደሰትና የምንከፋበት ፣ ተቋማዊነት ተዘሎ ቡድናዊ (መንደራዊ) አደረጃጀቶችና ግለሰቦች የሚገኑበት ብሎም የትርምስ ማእከል የሚሆኑበት ፣ ማንም ገብቶ እንዲፈተፍትበት ክፍት የተተወውና አሸናፊ የማያደርገን አዋራጅ መንገድ ሳይሆን ፣ እንደህዝብ ከተቃጣብን የህልውና አደጋ ታድጎ ፣ የህዝባችንን ጥቅምና ፍላጎት ተደራድሮ ለማስከበር የሚያስችለውን ፣ እንደህዝብ አሸናፊ የሚያደርገንን የህብረትና የተደራጀ ህዝባዊ ተቋማዊ የትግል መንገድ ሊሆን ይገባል!
አሁንስ ፈጣሪም ፦ ልቦናችንን ክፍት አድርጎ ፣ በሰማይ በምድር ያለእረፍት እሳት እየዘነበበት ላለው ህዝባችን ፣ ዋስትና የሚሆንና አሸናፊ የሚያደርገውን የትግል መስመር እንድንመለከት ይርዳን!
በቅንነት የምታነቡኝ በግርድፉ ያቀረብኳቸውን ነጥቦች ፣ ከነባራዊው አውድ ጋር በማሰናሰን ሰፋ አድርጋችሁ ግንዛቤ ትወስዱበታላችሁ ብዬ አስባለሁ!
ሠላማችሁ ይብዛ!