የኢትዮጵያ አየር መንገድ ይህን እንዲፈቅድ የሚያስገድደው አለማቀፋዊ ህግ ይኖር ይሆንን ?
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ማረፊያዎቹን ለወታደራዊ አገልግሎት እንዲውሉ መፍቀዱን ፣ ይህ ዛሬ ከባህርዳር አየር ማረፊያ የተወሰደና ለበረራ ዝግጁ የሆነች Bayraktar TB2 ድሮንን የሚያሳይ ምስል አንድ ማሳያ ነው!
ይህን የሚፈቅድ አለምአቀፋዊ ህግ ካለ ምናልባት ላላውቅ እችላለሁ ፣ ነገርግን ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ የመንገደኛ አውሮፕላኖች ፣ ወታደሮች ሲጓጓዙ የሚያሳዩ መረጃዎችን በተለያዩ ሚዲያዎች ተመልክተናል ፣ የአየር መንገዱ አየር ማረፊያዎች ለወታደራዊ አገልግሎት እየዋሉ መሆኑንም ሰምተናል ፣ ሌላው ቀርቶ የበረራ ህጉ በማይፈቅደው መልኩ እኔን ጨምሮ በርካቶች ከእጃችን ላይ ካቴና እንኳ ሳይፈታ በበርካታ ወታደሮች ታግተን ወደእስር ቤቶች ስንጓጓዝ የነበረውም በዚሁ አየር መንገድ አውሮፕላን ነው!
አገዛዙ ባለፈው አንድ ሳምንት ብቻ በጎንደርና በጎጃም መጠነ ሰፊ የሆነ የድሮን ጥቃት እየፈፀመ ሲሆን ፣ በጎጃም በአንድ ሳምንት ብቻ ከ50 በላይ የድሮን ጥቃት ተሰንዝሯል። በዚህም ህፃናትና ሴቶችን ጨምሮ ከ100 በላይ አርሷደሮች ሲጨፈጨፉ ፣ ከ10 በላይ ትምህርት ቤቶችም መውደማቸውን ከአካባቢው የሚወጡ መረጃዎች ያስረዳሉ! በሸዋና በወሎም ተመሳሳይ የድሮን ጥቃት እየተፈፀመና በርካታ ንፁሀንን እየቀጠፈ እንደሚገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ!
በንፁሀን ወገኖቻችን ላይ ያለእረፍት ከከባድ መሳሪያዎች በተጨማሪ በድሮን ፣ በጀትና በሄሊኮፕተር የሚፈፀመውን ፍጅት በመረጃና በማስረጃ እያጠናቀሩ መያዝ ተብሎም ለአለማቀፍ ማህበረሰብ ማጋለጥ ያስፈልጋል!
//ምስሉን የወሰድኩት ከጋዜጠኛ በላይ ማናዬ - Belay Manaye የፌስቡክ ገፅ ነው።//
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ማረፊያዎቹን ለወታደራዊ አገልግሎት እንዲውሉ መፍቀዱን ፣ ይህ ዛሬ ከባህርዳር አየር ማረፊያ የተወሰደና ለበረራ ዝግጁ የሆነች Bayraktar TB2 ድሮንን የሚያሳይ ምስል አንድ ማሳያ ነው!
ይህን የሚፈቅድ አለምአቀፋዊ ህግ ካለ ምናልባት ላላውቅ እችላለሁ ፣ ነገርግን ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ የመንገደኛ አውሮፕላኖች ፣ ወታደሮች ሲጓጓዙ የሚያሳዩ መረጃዎችን በተለያዩ ሚዲያዎች ተመልክተናል ፣ የአየር መንገዱ አየር ማረፊያዎች ለወታደራዊ አገልግሎት እየዋሉ መሆኑንም ሰምተናል ፣ ሌላው ቀርቶ የበረራ ህጉ በማይፈቅደው መልኩ እኔን ጨምሮ በርካቶች ከእጃችን ላይ ካቴና እንኳ ሳይፈታ በበርካታ ወታደሮች ታግተን ወደእስር ቤቶች ስንጓጓዝ የነበረውም በዚሁ አየር መንገድ አውሮፕላን ነው!
አገዛዙ ባለፈው አንድ ሳምንት ብቻ በጎንደርና በጎጃም መጠነ ሰፊ የሆነ የድሮን ጥቃት እየፈፀመ ሲሆን ፣ በጎጃም በአንድ ሳምንት ብቻ ከ50 በላይ የድሮን ጥቃት ተሰንዝሯል። በዚህም ህፃናትና ሴቶችን ጨምሮ ከ100 በላይ አርሷደሮች ሲጨፈጨፉ ፣ ከ10 በላይ ትምህርት ቤቶችም መውደማቸውን ከአካባቢው የሚወጡ መረጃዎች ያስረዳሉ! በሸዋና በወሎም ተመሳሳይ የድሮን ጥቃት እየተፈፀመና በርካታ ንፁሀንን እየቀጠፈ እንደሚገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ!
በንፁሀን ወገኖቻችን ላይ ያለእረፍት ከከባድ መሳሪያዎች በተጨማሪ በድሮን ፣ በጀትና በሄሊኮፕተር የሚፈፀመውን ፍጅት በመረጃና በማስረጃ እያጠናቀሩ መያዝ ተብሎም ለአለማቀፍ ማህበረሰብ ማጋለጥ ያስፈልጋል!
//ምስሉን የወሰድኩት ከጋዜጠኛ በላይ ማናዬ - Belay Manaye የፌስቡክ ገፅ ነው።//