Forward from: ሂዳያ መልቲሚዲያ | ʜɪᴅᴀʏᴀ ᴍᴜʟᴛɪᴍᴇᴅɪᴀ
"ትንሹ ዒድ(የሸዋል ዒድ)" የሚባለው በሸሪዓ እንዴት ይታያል?
ለርእሳችን መንደርደሪያ ይሆነን ዘንድ ዑለሞች የሸዋልን ስድስት ቀን ፆም በተመለከተ የሚያነሷቸውን የተለያዩ ሀሳቦች አጠር ባለ መልክ ለማየት እንሞክራለን።
👉ከሸዋል ወር ስድስት ቀናትን መፆምን በተመለከተ አብዛኞቹ ዑለማዎች የሚወደድ በመሆኑ ላይ የተስማሙ ቢሆንም ከአራቱ መዝሀብ ኢማሞች የሁለቱ የአቡ ሀኒፋ እና የማሊክ አቋም ግን ከዚህ በጣም ይለያል። ኢማሙ ማሊክ ሙወጣእ በተባለው ኪታባቸው ላይ በግልፅ እንደሚጠላ ሲገልፁ ከአቡ ሃኒፋም ተመሳሳይ አቋም ተንፀባርቋል።
አቡ ሃኒፋ ምክንያታቸው አላህ በደነገገው ፆም ላይ መጨመር ከአህለል ኪታቦች ጋር ያመሳስላል፤ ከነሱ ጋር መመሳሰል ደግሞ የተከለከለ ነው። የሚል ሲሆን በኢማሙ ማሊክ በኩል ደግሞ የቀረበው ምክንያት የእውቀት ባለቤቶች ሲፆሙት አላየሁም፤ ይልቁን መሀይማን እነሱ ሲፆሙት ቢያዩ ከረመዳን ያልሆነውን ፆም ከረመዳን አንደሆነ በማሰብ ቢደዓ ላይ ይወድቃሉ ብለው እንደሚፈሩ ገልፀዋል፤ በተጨማሪም ከሰለፎች ከአንዱም ይፆም እንደነበረ መረጃ አልደረሰኝም የሚል ነው። እዚህ ጋር አብሮ ተያይዞ መጠቀስ የሚገባው እነዚህ ዑለማዎች በሰሂህ ሙስሊም ውስጥ ተጠቅሶ የሚገኘውን እና ሌሎችንም የሸዋልን ስድስት ቀን መፆምን በተመለከተ የተዘገቡ ሀዲሶች እንዳልደረሷቸው ነው። ለዚህም ነው ከነሱ በኃላ ዘግይተው የመጡ የሀኒፍያ እና የማሊክያ መዝሀብ ዑለሞች በፊቅህ ኪታቦቻቸው ከተወደዱ የፆም አይነቶች መደዳ ያሰፈሩት በሌላ በኩል እነሱ ይሰጉት የነበረው ነገርም በመወገዱ መሆኑን የጠቀሱም አልጠፉም።
👉 በሌላ በኩል መፆሙ ይወዳዳል ያሉትን አል ኢማም አሻፊዒይ እና አህመድን ጨምሮ አብዛኞቹ (ጁምሁሮቹ) ዑለማዎችን አቋም ስንመለከት መቼ ይፆም በሚለው ላይ ከዒዱ ቀን ማግስት ጀምሮ ከሚለው ጀምሮ ከሸዋል ወር በኃላም ቢሆን እሰከሚለው የሀሳብ ልዩነትን አንፀባርቀዋል። ከፊሎቹ አከታትሎ ከወሩ መጀመሪያ ላይ መፆሙ ይወደዳል ሲሉ፤ ከፊሎቹ ደግሞ አይ ከዒድ በኃላ ወዲያው መፆም የለበትም ይልቁን ከአስራ ሶስተኛው ቀን በፊት ሶስት ቀን ይፆማል ይላሉ፤ ሌሎቹ ደግሞ በወሩ ውሰጥ በማነኛውም ጊዜ ከፆመው ፆሙን ባያከታትልም ቢያከታተልም ለውጥ የለውም ብለዋል።
👉 እንደጥቅል ከሸዋል ስድስት ቀናትን መፆም የሚወደድ መሆኑን የአላህ መልእክተኛ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም “ ረመዳንን ጾሞ ከዛም በኃላ ከሸዋል ወር ስድስት ቀናትን በመጾም ያስከተለው አንድ አመት የጾመ ያህል ነው። ” ማለታቸው የሚያመላክተው እንዲሁም የአብዛኞቹ ዑለማዎች አቋምም ቢሆንም። ነገር ግን አሁንም በዚህ ሀዲስ እና ሌሎች ተመሳሳይ ሀዲሶች አረዳድ ላይ የሸዋልን ስድስት ቀናት መፆም ይወደዳል የሚል አቋም የያዙት ዑለማዎች እራሳቸው ሌሎች ጥያቄዎችን አንስተዋል። ለምሳሌ ረመዳንን አሟልተው ያልፆሙ ሰዎች ቅድሚያ ቀዷእ ነው የሚፆሙት ወይስ ሸዋልን መፆም ይችላሉ? አይችሉም ካልንስ የሸዋል ወር ከወጣ በኃላ ቀዷቸውን ከጨረሱ የሸዋልን ሰድስት ቀን መፆም እንዴት ይታያል? እና ሌሎችንም ጥያቄዎች ማንሳት ይቻላል።
👉 ይህንን ሀሳብ በመንደርደሪያዬ ላይ የጠቀስኩበትን ምክንያት ምን እንደሆነ ሳትረዱኝ የቀራችሁ አይመስለኝም። ምንም እንኳ እንደጥቅል በመልካም ስራ ላይ መቻኮል የተወደደ ስለሆነ በቶሎ መፆሙ አስፈላጊ እንደሆነ መምከሩ ተገቢ ቢሆንም ከርእሱ ጋር በተያያዘ ዑለማዎች ጋር ያለውንም ልዩነት ማወቁ አሁን ለምንነጋገርበት ርእስ ወሳኝ ነው። ያም እንኳን ለሸዋል ዒድ የሚባል ሊኖረው አይደለም ከጅምሩ ፆሙ የተወደደ ነው ወይስ አይደለም? የሚፆመው ከመቼ ጀምሮ እና እንዴት ነው? በሚለው ጉዳይ ላይ አራቱ ኢማሞች እና ተከታዮቻቸው ያላቸውን ልዩነት ማወቁ በእርግጠኝነት "የሸዋል ዒድ" የሚባል ርእስ በነሱ ዘመን ያልነበረ መሆኑን በማያሻማ መልኩ ያስረዳል።
እንደውም ኢማሙ አቡ‐ሀኒፋ እና ማሊክ ዛሬ ሰዎች የወደቁበት ችግር ላይ ወይም እርሱን ተከትሎ ከሚመጣ ቢደዓ ላይ እንዳይወድቁ በመፍራት ነበር መፆሙኑም ይጠሉት የነበረው። ይህንንም በንግግራቸው ውስጥ እንረዳዋለን።
✍️ ጣሀ አህመድ - (1441 የተፃፈ)
🌐 https://t.me/hidaya_multi
ለርእሳችን መንደርደሪያ ይሆነን ዘንድ ዑለሞች የሸዋልን ስድስት ቀን ፆም በተመለከተ የሚያነሷቸውን የተለያዩ ሀሳቦች አጠር ባለ መልክ ለማየት እንሞክራለን።
👉ከሸዋል ወር ስድስት ቀናትን መፆምን በተመለከተ አብዛኞቹ ዑለማዎች የሚወደድ በመሆኑ ላይ የተስማሙ ቢሆንም ከአራቱ መዝሀብ ኢማሞች የሁለቱ የአቡ ሀኒፋ እና የማሊክ አቋም ግን ከዚህ በጣም ይለያል። ኢማሙ ማሊክ ሙወጣእ በተባለው ኪታባቸው ላይ በግልፅ እንደሚጠላ ሲገልፁ ከአቡ ሃኒፋም ተመሳሳይ አቋም ተንፀባርቋል።
አቡ ሃኒፋ ምክንያታቸው አላህ በደነገገው ፆም ላይ መጨመር ከአህለል ኪታቦች ጋር ያመሳስላል፤ ከነሱ ጋር መመሳሰል ደግሞ የተከለከለ ነው። የሚል ሲሆን በኢማሙ ማሊክ በኩል ደግሞ የቀረበው ምክንያት የእውቀት ባለቤቶች ሲፆሙት አላየሁም፤ ይልቁን መሀይማን እነሱ ሲፆሙት ቢያዩ ከረመዳን ያልሆነውን ፆም ከረመዳን አንደሆነ በማሰብ ቢደዓ ላይ ይወድቃሉ ብለው እንደሚፈሩ ገልፀዋል፤ በተጨማሪም ከሰለፎች ከአንዱም ይፆም እንደነበረ መረጃ አልደረሰኝም የሚል ነው። እዚህ ጋር አብሮ ተያይዞ መጠቀስ የሚገባው እነዚህ ዑለማዎች በሰሂህ ሙስሊም ውስጥ ተጠቅሶ የሚገኘውን እና ሌሎችንም የሸዋልን ስድስት ቀን መፆምን በተመለከተ የተዘገቡ ሀዲሶች እንዳልደረሷቸው ነው። ለዚህም ነው ከነሱ በኃላ ዘግይተው የመጡ የሀኒፍያ እና የማሊክያ መዝሀብ ዑለሞች በፊቅህ ኪታቦቻቸው ከተወደዱ የፆም አይነቶች መደዳ ያሰፈሩት በሌላ በኩል እነሱ ይሰጉት የነበረው ነገርም በመወገዱ መሆኑን የጠቀሱም አልጠፉም።
👉 በሌላ በኩል መፆሙ ይወዳዳል ያሉትን አል ኢማም አሻፊዒይ እና አህመድን ጨምሮ አብዛኞቹ (ጁምሁሮቹ) ዑለማዎችን አቋም ስንመለከት መቼ ይፆም በሚለው ላይ ከዒዱ ቀን ማግስት ጀምሮ ከሚለው ጀምሮ ከሸዋል ወር በኃላም ቢሆን እሰከሚለው የሀሳብ ልዩነትን አንፀባርቀዋል። ከፊሎቹ አከታትሎ ከወሩ መጀመሪያ ላይ መፆሙ ይወደዳል ሲሉ፤ ከፊሎቹ ደግሞ አይ ከዒድ በኃላ ወዲያው መፆም የለበትም ይልቁን ከአስራ ሶስተኛው ቀን በፊት ሶስት ቀን ይፆማል ይላሉ፤ ሌሎቹ ደግሞ በወሩ ውሰጥ በማነኛውም ጊዜ ከፆመው ፆሙን ባያከታትልም ቢያከታተልም ለውጥ የለውም ብለዋል።
👉 እንደጥቅል ከሸዋል ስድስት ቀናትን መፆም የሚወደድ መሆኑን የአላህ መልእክተኛ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም “ ረመዳንን ጾሞ ከዛም በኃላ ከሸዋል ወር ስድስት ቀናትን በመጾም ያስከተለው አንድ አመት የጾመ ያህል ነው። ” ማለታቸው የሚያመላክተው እንዲሁም የአብዛኞቹ ዑለማዎች አቋምም ቢሆንም። ነገር ግን አሁንም በዚህ ሀዲስ እና ሌሎች ተመሳሳይ ሀዲሶች አረዳድ ላይ የሸዋልን ስድስት ቀናት መፆም ይወደዳል የሚል አቋም የያዙት ዑለማዎች እራሳቸው ሌሎች ጥያቄዎችን አንስተዋል። ለምሳሌ ረመዳንን አሟልተው ያልፆሙ ሰዎች ቅድሚያ ቀዷእ ነው የሚፆሙት ወይስ ሸዋልን መፆም ይችላሉ? አይችሉም ካልንስ የሸዋል ወር ከወጣ በኃላ ቀዷቸውን ከጨረሱ የሸዋልን ሰድስት ቀን መፆም እንዴት ይታያል? እና ሌሎችንም ጥያቄዎች ማንሳት ይቻላል።
👉 ይህንን ሀሳብ በመንደርደሪያዬ ላይ የጠቀስኩበትን ምክንያት ምን እንደሆነ ሳትረዱኝ የቀራችሁ አይመስለኝም። ምንም እንኳ እንደጥቅል በመልካም ስራ ላይ መቻኮል የተወደደ ስለሆነ በቶሎ መፆሙ አስፈላጊ እንደሆነ መምከሩ ተገቢ ቢሆንም ከርእሱ ጋር በተያያዘ ዑለማዎች ጋር ያለውንም ልዩነት ማወቁ አሁን ለምንነጋገርበት ርእስ ወሳኝ ነው። ያም እንኳን ለሸዋል ዒድ የሚባል ሊኖረው አይደለም ከጅምሩ ፆሙ የተወደደ ነው ወይስ አይደለም? የሚፆመው ከመቼ ጀምሮ እና እንዴት ነው? በሚለው ጉዳይ ላይ አራቱ ኢማሞች እና ተከታዮቻቸው ያላቸውን ልዩነት ማወቁ በእርግጠኝነት "የሸዋል ዒድ" የሚባል ርእስ በነሱ ዘመን ያልነበረ መሆኑን በማያሻማ መልኩ ያስረዳል።
እንደውም ኢማሙ አቡ‐ሀኒፋ እና ማሊክ ዛሬ ሰዎች የወደቁበት ችግር ላይ ወይም እርሱን ተከትሎ ከሚመጣ ቢደዓ ላይ እንዳይወድቁ በመፍራት ነበር መፆሙኑም ይጠሉት የነበረው። ይህንንም በንግግራቸው ውስጥ እንረዳዋለን።
✍️ ጣሀ አህመድ - (1441 የተፃፈ)
🌐 https://t.me/hidaya_multi