Y T
Forward from: Ethio telecom
ኢትዮ ቴሌኮም እና ሲንቄ ባንክ የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎቶችን ለማስፋት ያለመ ስትራቴጂያዊ ምክክር አደረጉ!
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ እና የሲንቄ ባንክ ፕሬዚዳንት ነዋይ መገርሳ የሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት የሚያቀርቡትን አካታችነትን እና ተደራሽነትን የሚያረጋግጡ የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎቶችን ለማስፋት ያለመ ስትራቴጂያዊ ውይይት አደረጉ፡፡
ዋና ሥራ አስፈጻሚያችን ኢትዮ ቴሌኮም ከፋይናንስ ተቋማት ጋር በአጋርነት ዜጎች የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎቶች ተጠቃሚ በማድረግ አካታች የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ቀጣይነት ላለው ሀገራዊ እድገት የበኩሉን ሚና በመጫወት ላይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አክለውም ከሲንቄ ባንክ ጋር በአጋርነት በማህበረሰባችን ህይወት ላይ ትርጉም ያለው ለውጥ የሚያመጡ አዳዲስ የፋይናንስ አገልግሎቶችን በማቅረብ ሁሉን አቀፍ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ የሚያፋጥኑ ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን ገልጸዋል፡፡
የሲንቄ ባንክ ፕሬዚደንት ነዋይ በበኩላቸው ባንካቸው በአጭር ጊዜ ሁሉን አቀፍ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን በማድረግ ፈጣን ለውጥ በማስመዝገብ ላይ መሆኑን በመግለጽ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር አጋርነት ማጠናከር የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት በፍጥነት ለማረጋገጥ አስቻይ መደላድል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አክለውም ኢትዮ ቴሌኮም ከቅርብ አመታት ወዲህ በተለይም በዲጂታል ፋይናንስ ስነ-ምህዳሩ ላይ እያደረገ ያለው ፈጣን ለውጥ በማድነቅ ለዚህም አመራሩ ለባንካቸው መልካም አርአያና መበረታቻ እንደሆነ በአጽንኦት ገልጸዋል፡፡
#DigitalEthiopia #DigitalAfrica #SmartAfrica #GSMA #ITU #Ethiotelecom #Siinqee #telebirr
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ እና የሲንቄ ባንክ ፕሬዚዳንት ነዋይ መገርሳ የሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት የሚያቀርቡትን አካታችነትን እና ተደራሽነትን የሚያረጋግጡ የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎቶችን ለማስፋት ያለመ ስትራቴጂያዊ ውይይት አደረጉ፡፡
ዋና ሥራ አስፈጻሚያችን ኢትዮ ቴሌኮም ከፋይናንስ ተቋማት ጋር በአጋርነት ዜጎች የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎቶች ተጠቃሚ በማድረግ አካታች የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ቀጣይነት ላለው ሀገራዊ እድገት የበኩሉን ሚና በመጫወት ላይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አክለውም ከሲንቄ ባንክ ጋር በአጋርነት በማህበረሰባችን ህይወት ላይ ትርጉም ያለው ለውጥ የሚያመጡ አዳዲስ የፋይናንስ አገልግሎቶችን በማቅረብ ሁሉን አቀፍ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ የሚያፋጥኑ ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን ገልጸዋል፡፡
የሲንቄ ባንክ ፕሬዚደንት ነዋይ በበኩላቸው ባንካቸው በአጭር ጊዜ ሁሉን አቀፍ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን በማድረግ ፈጣን ለውጥ በማስመዝገብ ላይ መሆኑን በመግለጽ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር አጋርነት ማጠናከር የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት በፍጥነት ለማረጋገጥ አስቻይ መደላድል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አክለውም ኢትዮ ቴሌኮም ከቅርብ አመታት ወዲህ በተለይም በዲጂታል ፋይናንስ ስነ-ምህዳሩ ላይ እያደረገ ያለው ፈጣን ለውጥ በማድነቅ ለዚህም አመራሩ ለባንካቸው መልካም አርአያና መበረታቻ እንደሆነ በአጽንኦት ገልጸዋል፡፡
#DigitalEthiopia #DigitalAfrica #SmartAfrica #GSMA #ITU #Ethiotelecom #Siinqee #telebirr