በአብክመ ፖሊስ ኮሚሽን ተቋማዊ የሪፎርም ዳሰሳ ጥናትና ፍኖተ ካርታ ሰነድ ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ ተካሄደ።
የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን እንደተቋም የተለያዩ ተቋማዊ የሪፎርም ተግባራትን ያከናወነ ሲሆን በእነዚህና በነበረረው የህግ ማስከበር ተግባራት ዙሪያ የየዞኖቹ የመደበኛና የአድማ መከላከል ፖሊስ አመራሮች በተገኙበት ውይይት ተደርጓል።
በህግ ማስከበርና በመደበኛ ተግባራት የተከናወኑ ተግባራትን አስመልክቶ መነሻ ሰነድ ያቀረቡት የአብክመ ፖሊስ ኮሚሽን ዕቅድና ዝግጅት መምሪያ ኃላፊ የሆኑት ምክትል ኮማንደር ዘመን ዩሐንስ እንደተናገሩት ባለፈው ግማሽ ዓመት ውስጥ ከመደበኛ ተግባራዊ ጎን ለጎን በመስዕዋትነት የታጀበ በርካታ የህግ ማስከበር ተከናውነዋል፤ጥሩ ውጤትም ተመዝቦባቸዋል ብለዋል።
በመደበኛ የፖሊስ ተግባራትም ከወቅቱ ነባራዊ ሁኔታ ጋር ተያይዞ ጫናዎች ቢኖሩም የተሻሉ ስራዎች ተሰርተዋል።በተለይም በወንጀል ምርመራ ስራ ላይ ከበፊቱ በበለጠ ሁኔታ በርካታ የምርመራ መዝገቦች መመዝገባቸውን ነው ሰነዱ ያመላከተው።
በህግ ማስከበር ረገድም የህዝብ ለህዝብ ውይይትና የፅንፈኛውን ሴል በመጣጠስ በኩል የተከናወኑ የኦፕሬሽን ስራ አመርቂ ውጤት ታይቶበታል ነው ያሉት ምክትል ኮማንደር ዘመን ዩሐንስ።
የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን እንደተቋም የተለያዩ ተቋማዊ የሪፎርም ተግባራትን ያከናወነ ሲሆን በእነዚህና በነበረረው የህግ ማስከበር ተግባራት ዙሪያ የየዞኖቹ የመደበኛና የአድማ መከላከል ፖሊስ አመራሮች በተገኙበት ውይይት ተደርጓል።
በህግ ማስከበርና በመደበኛ ተግባራት የተከናወኑ ተግባራትን አስመልክቶ መነሻ ሰነድ ያቀረቡት የአብክመ ፖሊስ ኮሚሽን ዕቅድና ዝግጅት መምሪያ ኃላፊ የሆኑት ምክትል ኮማንደር ዘመን ዩሐንስ እንደተናገሩት ባለፈው ግማሽ ዓመት ውስጥ ከመደበኛ ተግባራዊ ጎን ለጎን በመስዕዋትነት የታጀበ በርካታ የህግ ማስከበር ተከናውነዋል፤ጥሩ ውጤትም ተመዝቦባቸዋል ብለዋል።
በመደበኛ የፖሊስ ተግባራትም ከወቅቱ ነባራዊ ሁኔታ ጋር ተያይዞ ጫናዎች ቢኖሩም የተሻሉ ስራዎች ተሰርተዋል።በተለይም በወንጀል ምርመራ ስራ ላይ ከበፊቱ በበለጠ ሁኔታ በርካታ የምርመራ መዝገቦች መመዝገባቸውን ነው ሰነዱ ያመላከተው።
በህግ ማስከበር ረገድም የህዝብ ለህዝብ ውይይትና የፅንፈኛውን ሴል በመጣጠስ በኩል የተከናወኑ የኦፕሬሽን ስራ አመርቂ ውጤት ታይቶበታል ነው ያሉት ምክትል ኮማንደር ዘመን ዩሐንስ።