ኦርቶዶክስ ተዋህዶ


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана



Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций








በቅድስት ዐቢይ ጾም ዘዓርብ
ማርቆስ 12:29-38


ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፦ከትእዛዛቱ ሁሉ ፊተኛዪቱ፦እስራኤል ሆይ ስማ ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው አንተም በፍጹም ልብህ በፍጹምም ነፍስህ በፍጹምም ዐሳብህ በፍጹምም ኀይልህ ጌታ አምላክህን ውደድ የምትል ናት፡፡ፊተኛዪቱ ትእዛዝ ይህች ናት፡፡

☞ ኹለተኛዪቱም፦ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ የምትል ርሷን የምትመስል ይህች ናት፡፡ከነዚህ የምትበልጥ ሌላ ትእዛዝ የለችም፡፡ ጻፊውም፦መልካም ነው መምህር ሆይ አንድ ነው ከርሱም በቀር ሌላ የለም ብለህ በእውነት ተናገርህ

☞ በፍጹም ልብ በፍጹም አእምሮም በፍጹም ነፍስም በፍጹም ኀይልም እርሱን መውደድ ባልንጀራንም እንደ ራስ መውደድ በሙሉ ከሚቃጠል መሥዋዕትና ከሌላው መሥዋዕት ሁሉ የሚበልጥ ነው አለው፡፡

ኢየሱስም በአእምሮ እንደ መለሰ አይቶ፦አንተ ከእግዚአብሔር መንግሥት የራቅህ አይደለህም አለው፡፡ከዚህም በኋላ ማንም ሊጠይቀው አልደፈረም፡፡ ኢየሱስም በመቅደስ ሲያስተምር መልሶ እንዲህ አለ፦ጻፊዎች ክርስቶስ የዳዊት ልጅ ነው እንዴት ይላሉ ዳዊት ራሱ በመንፈስ ቅዱስ፦ጌታ ጌታዬን፦ጠላቶችህን የእግርህ መረገጫ እስካደርግልህ ድረስ በቀኜ ተቀመጥ አለው አለ.......


ሮሜ 13:8-11
1ዮሐንስ 4:18-21
ግብ፡ ሐዋ፡ሥራ 6:1-4


ምስባክ
መዝሙር ፻፲፰ : ፸ - ፸፩


ደለወኒ ዘአሕመምከኒ

ከመ አእምር ኵነኔከ

ይኄይሰኒ ሕገ አፉከ

ትርጉም


ሥርዐትኽን እማር ዘንድ

ያስጨነቅኸኝ መልካም ኾነልኝ

የአፍኽ ሕግ ይሻለኛል


✝ኦርቶዶክስ ተዋህዶ✝

#መልካም_እለት

https://t.me/OrtoPicture
https://t.me/OrtoPicture
https://t.me/OrtoPicture






በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን እንደምን ቆያችሁ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
መልስና ጥያቄ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
1⃣,ቤተ ክርስቲ ያን ማለት ምን ማለት ነው??

መልስ፦ -ቤተ ክርስቲያን ማለት የክርስቲያኖች አንድነት ጉባኤ ወይም ማህበር ማለት ነው።

2⃣,መንፈሳዊ ተጋድሎ ማለት ምን ማለት ነው??

መልስ፦ ተጋድሎ ማለት አንድ ሰው የሚያምንበትን እምነት፣የሚመራበትን ሕግ፣ የሚያልመውን ተስፋ ተከትሎ ሀሳቡን ከግብ ለማድረስ ማድረግ የሚገባውን በማድርግ፣ማድረግ የማይገባውን ባለማድረግ በነጻ ፈቃዱ ወስኖ በሙሉ ልቦናው እና በሙሉ ኃይሉ የሚያደርገው የውስጥ እና የውጭ ጥረት ነው።

3⃣, ጸጋ እግዚአብሔር ለማግኘት ምን ማድረግ አለብን???

መልስ፦ ጸጋ ማለት እግዚአብሔር ለልጆቹ በነጻ የሚያድላቸው ስጦታ ማለት ነው። ይኸውም የሚገኘው በመንፈሳዊ ተጋድሎ ነው።

4⃣,የቅዱስ ጴጥሮስ አባት ማን ይባላል??
ነው

መልስ፦ ዮና ይባላል።

5⃣, ከአስራሁለቱ (፩፪) ሐዋርያት መካከል በመጀመርያ የሰማዕትነን አክሊል የተቀዳጀ ሰማዕትነቱ በሐዲስ ኪዳን መጽሐፍ የተጻፈለት ብቸኛ ሐዋርያ ማን ነው??

መልስ፦ ሐዋርያው ቅዱስ ያዕቆብ /ወልደ ዘብዴዎስ/ ነው።
የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ቁጥር ፩ ገጽ 48 ላይ ማንበብ ይቻላል።

6⃣, ገድላት በስን ይከፈላሉ??

መልስ፦ ገድላት በ3 ይከፈላሉ እነሱም፦ 1) ገድለ ሰማዕታይ፦ ለምሳሌ ገድለ ጊዮርጊስመከራ ገድለ ፋሲለደስ፤ ገድለ ኢየሉጣ
2) ገድለ ሐዋርያት፦ በአንድነት የተሰበሰቡ የሐዋርያት አገልግሌት ተአምራት የያዘ መጽሐፍት
3) ገድለ ጻድቃን፦ ገድለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት፣ ገድለ ገብረ መንፈስ ቅዱስና የመሳሰሉት ናቸው።

7⃣, ህግ በስንት ይከፈላል??

መልስ ፦ በ3 ይከፈላል እነሱም
1ኛ ህግ ልቦና
2ኛ ህግ ኦሪት .
3ኛ ህግ ወንጌል ናቸው።

8⃣, መልአኩ ቅዱስ ገብሬኤል ለነብዩ ዳንኤል ስንት ሚስጥራት ገለጸለት??

//መልስ፦// 3 ሚስጥራትን ገልጾለታል 1ኛ የቤተ እስራኤልን ከ70 አመት በኋላ ወደ ኢየሩሳሌም መመለስ።
2ኛ የክርስቶስ ሰው መሆንና መሞት ዘመን
3ኛ የኃሳዊ መሲህን በመጨረሻው መምጣት ነው።

9⃣, በ8ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ታቃጥል የነበረች አይሁዳዊ ፈላሻ ማን ነበረች??

// መልስ// ዮዲት ጉዲት ነበረች።

የሚከተሉትን ጥያቄዎች ትክክለኛውን መልስ ምረጥ/ጭ/
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

10, አዕማደ ሐዋርያት (የምሥጢር ሐዋርያት) ከሚባሉት ውስጥ የሆነው የትኛው ነው??

ሀ) ዮሐንስ ለ) ያዕቆብ መ) ጴጥሮስ ሠ) ሁሉም መልስ ነው??

//መልስ// ሠ, ሁሉም መልስ ነው።

11, ቆስጠንጢኖስ ለቤተ ክርስቲያን ከሰጣቸው መብቶች ውስጥ የትኞቹ ናቸው??

ሀ) ቤተ ክርስቲያን ከግብር ነጻ ናት።
ለ) ከመንግሥት ገቢ ለቤተ ክርስቲያን የተወሰነ ድርሻ አላት።

ሐ) ዕለተ እሑድ /ሰንበት/ በንጉሠ ነገሥቱ ግዛት ውስጥ ሥራ እንዳይሠራበት አወጀ።

መ) ከክርስቲያን ወገን በሕይወቱም ሆነ በሞቱ ንብረቱን ለቤተ ክርስቲያን አወርሳለሁ የሚል ምእመን ካለ ቤተ ክርስቲያን ኑዛዜ የመቀበል፤ ውርስ የመውረስ መብት አላት።

ሠ) በክርስቲያኖች መካከል ለሚፈጠሩ አንዳንድ አለመግባባቶች ቢኖሩ ለኤጲስ ቆጶሳት የዳኝነት ሥልጣን ሰጥቷል።

ረ) ሁሉም መልስ ነው።

የተጀመረው
//መልስ// ረ, ሁሉም መልስ ነው።

1⃣2⃣, ክህደት በ-----------------ነው
.ሀ) በሳጥናኤል/ዲያብሎስ
ለ) በአርዮስ
ሐ) በይሁዳ
መ) አይታወቅም

//መልስ//፦ ሀ) በሳጥናኤል /ዲያብሎስ

ውድ የተወደዳችሁና የተከበራችሁ ወንድም እህቶቼ ጠቅላላ መልስ ይህንን ይመስላል ስተት ከአለበት አርሙኝ ለመታረም ዝግጁ ነኝ። ወስብኃት ለእግዚአብሔር
ወለ ለወላዲቱ ድንግል
ወለ ለመስቀሉ ክቡር።

✝ኦርቶዶክስ ተዋህዶ✝
       
     #መልካም_አዳር

https://t.me/OrtoPicture
https://t.me/OrtoPicture
https://t.me/OrtoPicture


አገልጋዮች በቅዳሴና ለሌሎች መንፈሳዊ አገልግሎት ሰዓት ሞባይል ስልክ ይዘው ወደ ቤተ ክርስቲያን እንዳይገቡ መከልከሉን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አስታወቀ።

ሀገረ ስብከቱ የዐቢይ ጾምን አስመልክቶ አገልግሎቱ እንዴት መከናወን እንዳለበት  ከሁሉም ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ ጸሐፊዎችና ሰባክያነ ወንጌል እንዲሁም ቄሰ ገበዞች ጋር ባደረገው ውይይትና ስምምነት መነሻነት  የተለያዩ መመሪያዎች  መተላለፋቸው ተገልጿል።

ከመመሪያዎች አንዱ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በሚከናወኑ  የጸሎተ ቅዳሴና ሌሎች መንፈሳዊ አገልግሎቶች የእጅ ሞባይል ስልክ ይዞ መግባት በጥብቅ  የተከለከተለ መሆኑን ለሁሉም  ገዳማትና አድባራት በተላከው የመመሪያ ደብዳቤ  ለማወቅ ተችሏል።

በኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እምነትና ሥርዓት መሠረት ቅዳሴ የሁሉም ጸሎታት ማጠናቀቂያ ፣ ቀራንዮ ላይ ምንገኝበት፣ የበጉ ሠርግ ላይ የምንታደምበት፣የጌታችንን የአምላካችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን በአንድነት ለሓጢአት ሥርየት፣ ለነፍስ ሕይወት፣ ለሃይማኖት ጽንዐትና ለመንግሥተ ሰማያት መውረሻ ይሆነን ዘንድ የምቀበልበት  ታላቅ የጸሎት ሰዓት ነው።

በመሆኑም አላስፈላጊ የእጅ ስልክ አጠቃቀም ጎልጎታን ከሚያስረሱ ፣በረከትን ከሚያሳጡና  ጸጋን ከሚያስወስዱ ድርጊቶች መካከል አንዱ በመሆኑ እንደተከለከለም  ተገልጿል።

ይህንን መመሪያም የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎችና ሰበካ ጉባኤያት ጥብቅ ክትትል በማድረግ እንዲያስፈጽሙ  መታዘዛቸውን በተጻፈ ደብዳቤ ለማወቅ ተችሏል።


✝ኦርቶዶክስ ተዋህዶ✝
       
     #መልካም_አዳር

https://t.me/OrtoPicture
https://t.me/OrtoPicture
https://t.me/OrtoPicture


✝ኦርቶዶክስ ተዋህዶ✝

#መልካም_እለት

https://t.me/OrtoPicture
https://t.me/OrtoPicture
https://t.me/OrtoPicture


✝ኦርቶዶክስ ተዋህዶ✝

#መልካም_እለት

https://t.me/OrtoPicture
https://t.me/OrtoPicture
https://t.me/OrtoPicture


 ገዳማዊያኑ እየሰሩ ቀጣይነት ያለው ገቢ እንዲያመነጩ ለማድረግ በማሰብ በሃሙሲት ከተማ የሸቀጣ ሸቀጥ እና የንዋያተ ቅዱሳት መሸጫ ሱቅ ተከፍቶ ወደ ስራ ተገብቷል።
 ለግንባታ የሚውል በሃሙሲት ከተማ 30 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ከመንግስት በሊዝ በመውሰድ በዚህም የአብነት ት/ቤት ፣ አለማዊ ት/ቤት እንዲሁም የመጀመሪያ ደረጃ ጤና ጣቢያ በተጨማሪም ሌሎችም ለገዳማዊያኑ አስፈላጊ የሆኑ የልማት ስራዎች የሚሰሩበት ይሆናል።

የልማት ስራዎች ከተጀመሩ አጭር ጊዜ በመሆኑ እስካሁን የተሰሩ ስራዎች አበረታች ቢሆኑም ከዚህ በተሻለ ፍጥነት መስራት እንዳይቻል የተለያዩ ተግዳሮቶች አጋጥመውናል፡፡
 በገዳሙ ውስጥ ስራ የሚሰራባቸው ቀናት ውስን መሆን፤ ማለትም ቅዳሜ እና እሁድን ጨምሮ ገዳማዊያኑም የሚያከብሯቸው በዓላት ሲጨማመሩ በወር ውስጥ የሚሰራባቸው ቀናት ከ 4(አራት) – 14(አስራ አራት) የሚሆኑ ቀናት ብቻ ናቸው።
 በግንባታ እቃዎች ላይ ከጊዜ ወደ ጊዜ የሚስተዋል የዋጋ ልዩነትም አንዱ ችግር ነው።

 ሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ ችግሮች ተጠቃሽ ሲሆኑ
 ከሚዲያው አካባቢ በተለይም ቲክቶክ አንዳንድ ቲክቶከሮች ፣ የገዳሙ አባቶችን ሆነ የቤተክርስቲያን መዋቅር ምንም አይነት መረጃ ሳይጠይቁና ያለ ምንም ተጨባጭ ማስረጃ በይመስለኛል ብቻ፣ የገዳሙንም የተከታዮቻቸውንም ክብር በማይመጥን መልኩ ተገቢና ትክክለኛ ያልሆኑ መረጃዎችን ማሰራጨት የሚሉት ከብዙዎቹ ተግዳሮቶች ጥቂቶቹ እነዚህ ናቸው።

እስካሁን የተከናወኑ ስራዎች በተለይም የእናቶችን ችግር በመቅረፍ ደረጃ ጥሩና አስደሳች ቢሆንም በአባቶች በኩል ገና ብዙ ስራዎች ይቀራሉ፡፡በመሆኑም በቀጣይ በትኩረት ከሚሰሩ ስራዎች መካከል፡-
 የአባቶች በዓት ግንባታ ሥራ
 የአባቶች ቤተ እግዚአብሔር ግንባታ ሥራ
 የአባቶች የመጸዳጃ ቤት ግንባታ ሥራ
 የእንጨት እና የብረታብረት ውጤቶችን ማምረቻ ሼድ ግንባታ ሥራ፣
 የእህል መጋዘን ግንባታ ሥራ
 የቅዱስ ሚካኤል ህንጻ ቤተክርስቲያን ግንባታ ሥራ
 የአብነት ት/ቤት ፣ ዓለማዊ ት/ቤት እና የመጀመሪያ ደረጃ ጤና ጣቢያ ግንባታ ሥራ
 የጸበልተኞች ማረፊያ ቤት ግንባታ ሥራ እንዲሁም
 የውሃ እና መብራት አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ በቀጣይ ከሚሰሩት ስራዎች መካከል ተጠቃሾች ናቸው፡፡
በቀጣይ ለሚሰሩት የልማት ሥራዎች ማከናወኛ የሚሆን ድጋፍን ለማሰባሰብ በቀጣይም የተለያዩ መርሀ-ግብሮች የሚከናወኑ ይሆናል።

ለአብነትም፡-
 ከመጋቢት 25 እስከ ሚያዝያ 2 ቀን 2017 ዓ.ም ምዕመኑ ከገዳሙ በረከት እንዲያገኙ እንዲሁም ገዳሙን እንዲጎበኙ የጉዞ መርሃግብር ተዘጋጅቷል።
 የድጋፍ ማሰባሰቢያ የቀጥታ ስርጭት መርሃ-ግብር በተለያዩ የሚዲያ ተቋማት የሚከናወን ይሆናል።
 ጥቅምት 16 ቀን 2018 ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ ብጹዓን ሊቃነ ጳጳሳት እና ሊቃውንተ ቤተክርስቲያ በተገኙበት ታላቅ የገቢ ማሰባሰቢያ ጉባኤ ይኖረናል፤
 የሚዲያ ንቅናቄ ዘመቻውም እንደተጠበቀ ሆኖ በተለይም ከቤተ-ክርስቲያን የሚዲያ አካላት ጋር በመነጋገርም ዶክሜንተሪዎችን እንዲሰሩና ምዕመኑ ገዳማዊያኑ ያሉባቸውን ችግሮች በመረዳት ድጋፍ እንዲያደርጉ ለማስቻል ስራዎች የሚሰሩ ይሆናል፡፡

‹ለድሃ ቸርነትን የሚያደርግ ለእግዚአብሄር ያበድራል፣በጎነቱንም መልሶ ይክፍለዋል› እንዲል ጠቢቡ ሰለሞን፣ ለዓለሙ ሰላም፣ ለሰው ልጆች ሁሉ ድህነት ዘወትር የሚማጸኑት እነዚህ ገዳማዊያን፣ ያሉባቸው ችግሮች ተፈተውላቸው፣ ዓለሙን ትተው የሄዱበትን ፈጣሪን መማጸን ላይ ብቻ እንዲያደርጉ፣ ሁሉም ምዕመን ድጋፍ እንዲያደርግ በልዑል እግዚአብሄር ስም ጥሪ እናቀርባለን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
የካቲት ፲፬ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም
አዲስ አበባ፤ዋቢ ሸበሌ ሆቴል

✝ኦርቶዶክስ ተዋህዶ✝

#መልካም_እለት

https://t.me/OrtoPicture
https://t.me/OrtoPicture
https://t.me/OrtoPicture


ከሙትአንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

 ብጹዕ አባታችን አቡነ እንጦስ የምዕራብ ሐረርጌ ሐገረስብከት ሊቀጳጳስ
 መንፈሳዊ ተልዕኮ ተቀብላችሁ ልዑል እግዚአብሄር በሰጣችሁ ጸጋ በተለያየ ስፍራ የምታገለግሉ ሊቃውንተ ቤተ-ክርስቲያን
 ጥሪ የተደረገላችሁ ተጋባዥ እንግዶች፣
 የመንግስት እና የግል የሚዲያ ተቋማት፣
 ዩትዩበሮች እና ቲክቶከሮች
 ጥሪያችንን አክብራችሁ ስለተገኛችሁ በልዑል እግዚአብሔር ስም ልባዊ ምስጋንችንን ለማቅረብ እንወዳለን፡፡

ወደ ጋዜጣዊ መግለጫው ከመግባታችን በፊት፣ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት እንዳለው መዝ 35-3 ‹‹ እኔስ እነርሱ በታመሙ ጊዜ ማቅ ለበስሁ ነፍሴንም በጾም አደከምኳት›› እንዳለው፣ ነፍስን ለማንቃት፣ፈቃደ ስጋን ለፈቃደ ነፍስ ለማስገዛት ተመራጩ መንገድ ጾም ነውና ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለኛ አብነት ለመሆን ለጾመው ለታላቁ ዐብይ ጾም ከወዲሁ እንኳን አደረሳችሁ እንኳን አደረሰን ለማለት እንወዳለን፡፡

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ፣ ገዳም የእኔ የግሌ የሚሉት ንብረት የሌለበት፣ ሁሉ በማኅበር በአንድነት በጸሎት በስራ እየተጉ ፍጹም የዓለምን አላፊነት ተረድተው፣ የማታልፍ የእግዚአብሄር መንግስት እንዳለች በመገንዘብ ዘወትር በቀኖና ተወስነው የሚኖሩበት የቅዱሳን መኖሪያና ጸጋ እግዚአብሔር የማይለይበት የዲያብሎስ ፈተና የሚበዛበት ሥፍራ ነው።

ገዳምና ገዳማዊ ሕይወት አስፈላጊ በመሆኑ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ አርአያ ሆኖን፣ በገዳመ ቆሮንቶስ ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ ተቀመጠ (ማቴ.4፡1-11) ፈታኝ ዲያብሎስንም ድል አደረገው፣ገዳምና ገዳማዊ ሕይወት አስፈላጊ ሆኖ የመሰረተልን አምላካችን አርአያችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ዛሬም እርሱን በመከተል ገዳማዊ ሕይወት ለትሩፋት መስሪያ፣ለንስሃ ሕይወት መቆያ፣ለበረከት ለረድኤት የአምላካችንን አረያነት ተከትለው አባቶች እናቶች በገዳም ተወስነው ይገኛሉ፡፡

ገዳማት የቤተ-ክርስቲያናችን ስውር ጓዳዎችና የሚስጢር መዝገቦች፣የመማጸኛ ቅዱስ ስፍራዎች፣የቤተ-ክርስቲያናችን ሁለንተናዊ አገልግሎት መሰረት፣ የተግባራዊ ክርስትና ምሳሌዎችም እና የታላላቅ የቤተ-ክርስቲያን ሊቃውንት መፍለቂያዎችም ናቸው።

እነዚህ አብያተ-ክርስቲያናት እና ገዳማት መንፈሳዊ አገልግሎታቸውን እየሰጡ፣ትውልድንም በክርስቲያናዊ ስነ-ምግባር እያነጹ ይቀጥሉ ዘንድ ገቢ ያስፈልጋቸዋል። ይህንን ገቢያቸውን ከሚያገኙባቸው መንገዶች መካከል በራሳቸው አቅም ገቢ የሚያመነጩ ስራዎችን ማከናወን እንዲሁም ምዕመኑ በሚሰጠው መባ እና አስራት በኩራ ይጠቀሳሉ።

ይሁንና አንዳንዴ ተፈጥሮ ፊቷን ስታዞርና ተፈጥሯዊ ችግሮች ሲበረቱ ሰው ሰራሽ ችግሮችም ሰጨመሩ ገዳማት የገቢ ምንጫቸውና ህልውናቸው ሙሉ በሙሉ ሕዝበ ክርስቲያኑ በሚያደርገው ድጋፍ ላይ የተንጠለጠለ የሚሆንበት አጋጣሚም ይፈጠራል ፤ሙትአንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም በአሁኑ ወቅት የገጠመው ችግር በዚህ ደረጃ የሚገለጽ ነው።
በማዕከላዊ ጎንደር ሐገረ ስብከት በምስራቅ በለሳ ወረዳ ቤተክህነት የሚገኘው ይህ ገዳም፣ ከዘጠና በላይ መነኮሳትና በመቶ የሚቆጠሩ ፀበልተኞች የሚገኙበት እጅግ ድንቅ ተዓምር ያለበት ታሪካዊ የአንድነት ገዳም ቢሆንም መነኮሳቱ በአሁኑ ወቅት ትልቅ ችግር ተጋርጦባቸው ይገኛሉ።

በአንድ በኩል አካባቢው በርሃማ በመሆኑ በበጋ ወቅት ለከፍተኛ ድርቅ ይጋለጣል፣በዚህም ምክንያት ምንም ዓይነት አዝዕርት አይበቅልበትም፣ይህን ተከትሎ ቀደም ሲል ድጋፍ ያደርጉ የነበሩት የአካባቢው ነዋሪዎች ሳይቀር ለገዳሙ ምንም አይነት ድጋፍ ለማድረግ ተቸግረዋል።

ገዳማዊያኑ የሚቀምሱት እህል፣የሚለብሱት ልብስ በመጠኑ የተሟላላቸው ቢሆንም ከጾም፣ ጸሎት መልስ ስጋቸውን የሚያሳርፉበት በዓት (ቤት) የላቸውም። በአንድ ደሳሳ ጎጆ በዓት ውስጥ ለሶስት ለአራት የሚያድሩበት በጣም አሳዛኝ ሁኔታ ዉስጥ ይገኛሉ።

በዚህ ገዳም የሚገኙ ገዳማዊያን ዛሬም ከጸሃይ፣ከብርድ፣ከዝናብ የሚከላከል መጠለያ አጥተው በከፍተኛ ችግር እየተፈተኑ የሚገኙ በመሆኑ፣ ገዳማዊያኑን ከነዚህ ችግሮች እንዲወጡና በቀጣይም ገዳሙ ራሱን እንዲችል ለማድረግ፣ በጠቅላይ ቤተክህነት እውቅና እና በሐገረ ስብከቱ ፍቃድ ገዳሙ ብቻ የሚጠቀመው በገዳሙ ስም የተከፈቱ የባንክ አካውንቶች ይፋ ተደርገው፣ በሕዝበ ክርስቲያኑ በሚደረገው ድጋፍ ስራዎች እየተሰሩ ሲሆን፣ ገዳሙም የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በወረዳ ቤተ-ክህነት፣በሐገረ ስብከትና በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጸድቆ በሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬና የቅርብ ክትትል እየተደረገበት በመሰራት ላይ ይገኛል።

እነዚህን የታቀዱ ለገዳሙ አስፈላጊ እና መሰረታዊ የሆኑትን የልማት ሥራዎችን ለማከናወን የሚያስችል ገቢ ለማሰባሰብ የሚረዱ የተለያዩ የገቢ ማሰባሰቢያ መንገዶችን ለመጠቀም ጥረት ተደርጓል።

ከነዚህም ውስጥ፦ ገዳሙ ያለበትን አሁናዊ ሁኔታ የሚገልጹ እና የሚያሳዩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ዶግማ፣ ቀኖና እንዲሁም ትሁፊት በጠበቀ መልኩ፡

 በቴሌቪዥንና ራዲዮን ማስታወቂያዎችን በማስተላለፍ ሕብረተሰቡ መረጃዉ ኖሮት የተቻለውን ድጋፍ እንዲያደርግ
 በማሕበራዊ ሚዲያ ማለትም፡ በፌስቡክ፣ በዩቲዩብ፣ በቲክቶክ፣ በቴሌግራም፣ በኢንስታግራምና ሌሎችንም በመጠቀም ለታቀዱት የልማት ሥራዎች የሚያስፈልገውን ገቢ ለማሰባሰብ ጥረት ተደርጓል።

በዚህም እስካሁን 11,000,000.00 (አስራ አንድ ሚሊዮን) ብር የሚያህል የገንዘብ ድጋፍ እንዲሁም 1,200,000.00(አንድ ሚሊዮን ሁለት መቶ ሺህ) ብር የሚሆን የአይነት ድጋፍ ማሰባሰብ ተችሏል።

ፕሮጀክቱ ከተጀመረ 11(አስራ አንድ) ወራትን ያስቆጠረ ሲሆን በነዚህ ጊዚያት በመጀመሪያው ምዕራፍ በርካታ ስራዎች ተከናውነዋል።

ከተሰሩ ስራዎች መካከል ፡-

 የእናቶች በዓት ወይም ቤት በጥሩ ሁኔታ ተሰርቷል።
 170 ሜትር ተራራ ተቦርቡሮ ለእናቶችም ለአባቶችም ለእንቅስቃሴ አስቸጋሪ የነበረው ቦታ በአርማታ ደረጃ ተሰርቶለት ለገዳማዊያን እንቅስቃሴ ምቹ እንዲሆን ተደርጓል።
 በአካባቢው ምንም አይነት የመብራት አገልግሎት ያልነበረ ሲሆን አሁን የሶላር መብራት ተሟልቶ የመብራት ተጠቃሚ ለማድረግ ተችሏል።
 ቤተ-እግዚአብሔር ወይም ማዕድ ቤት ተሰርቷል፤የሚያስፈልጉ ሙሉ ቁሳቁሶችም ተሟልተዋል።
 ገዳማዊያኑ በተደጋጋሚ የሚያጋጥማቸውን የምግብ አቅርቦት ችግር እና የአቅም ውስንነት በዘላቂነት ለመቅረፍ ጥረት እየተደረገ ይገኛል።
 ለገዳማዊያኑ የእደ-ጥበባት ውጤቶችን ማምረቻ ሼድ ግንባታ ተከናውኗል እንዲሁም የሸማ ስራ ሙያ እንዲሰለጥኑ በማድረግ ወደ ስራ እንዲገቡ ተደርጓል፣ ለስራው የሚያስፈልጉ መሳሪያዎች እና የጥሬ እቃ ግብዓቶችም ተሟልተዋል።
 የሻማ እና የጧፍ መስሪያ ማሽን ግዢ ተከናውኗል።
 አካባቢው በተደጋጋሚ በድርቅ የሚጠቃ በመሆኑ ለገዳማዊያኑ የተሻለ ለማድረግ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።
 ወደ ገዳሙ የሚያደርስ 8 (ስምንት) ኪሎ ሜትር ደረጃ አንድ የጠጠር መንገድ ሥራ ተሰርቷል

 የእናቶች የመጸዳጃ ቤቶች ግንባታ ተከናውኗል።
 ለግንባታ አገልግሎት የሚውል የሲምንቶ ማቡኪያ ማሽን፣የብረታ ብረትና የእንጨት መስሪያ ማሽነሪ ግዥ ተፈጽሟል።
 ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር የገዳሙ ይዞታ ህጋዊ የይዞታ ማረጋገጫ ያልነበረው በመሆኑ የገዳሙ ህጋዊ ይዞታው እንዲረጋገጥለት ተደርጓል።


የካቲት 6
ቅድስት ማርያም እንተ ዕፍረት

በዚህችም ቀን ጌታን ሽቱ ለቀባችው ማርያም የዕረፍቷ መታሰቢያ ነው ይችም ቅድስት አስቀድማ ኑሮዋን በዝሙት ያሳለፈች ኃጢአተኛ ነበረች እርሷም ጐልማሶችን ወደርሷ ትማርካቸው ዘንድ በየራሱ በሆነ ሽልማትና ጌጥ ትሸለም ነበር።

በአንዲትም ዕለት እንደ ልማድዋ ተሸልማ አጊጣ ሽቱም ተቀብታ ፊቷን በመስታዋት ተመለከተች የጉንጯ ቅላትና ደም ግባቷ የዓይኗም ወገግታና ጥራት ማማሩን አይታ እያደነቀች አንድ ሰዓት ያህል ቆየች ከዚህም በኋላ በጎ ኀሳብ በላይዋ መጣ ሞትንና የዚህን ዓለም ማለፍ አሰበች

የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስም ኃጢአተኞችን እንደሚቀበልና ኃጢኣትንም እንደሚአስተሰርይ ሰምታ ገንዘቧን ወስዳ የአልባስጥሮስን ሽቱ ገዝታ በስምዖን ዘለምጽ ቤት ለምሳ ተቀምጦ ሳለ ወደ ጌታችን ሔደች

ከእግሩ በታችም ሰግዳ ያንን ሽቱ ቀባችው እግሮቹን በዕንባዋ አጠበችውና በራስዋ ጠጉር ወለወለችው ጌታችንም የፍቅርዋን ጽናት አይቶ ኃጢኣቷን በደሏን ተወላት የመንግሥት ወንጌልም በሚሰበክበት ይህን ያደረገችውን እንዲአስቡ አዘዘ

በረከቷም ከእኛ ጋር ይኑር ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን አሜን

መልካም በዓል


ጾመ ነነዌ
የነነዌም ሰዎች እግዚአብሔርን አመኑ ጾምንም ዐወጁ ሰዎቹም ሁሉ ከትልቁ እስከ ትንሹ ማቅ ለበሱ
ወሬውም ወደ ነነዌ ንጉሥ በደረሰ ጊዜ ከዙፋኑ ወረደ ልብሱንም አወለቀ ማቅም ለብሶ በዐመድ ላይ ተቀመጠ
ከዚያም እንዲህ ሲል በነነዌ ዐዋጅ አስነገረ
ከንጉሡና ከመሳፍንቱ የወጣ ዐዋጅ “ማንም ሰው ወይም እንስሳ የከብት መንጋም ሆነ የበግ መንጋ ምንም ነገር አይቅመስ አይብላ ውሃም አይጠጣ
ነገር ግን ሰውም እንስሳም ማቅ ይልበስ ሁሉም አጥብቆ ወደ እግዚአብሔር ይጩኽ ሰዎችም ሁሉ ክፉ መንገዳቸውንና የግፍ ሥራቸውን ይተዉ
እኛ እንዳንጠፋ እግዚአብሔር ራርቶ ከጽኑ ቍጣው ይመለስ እንደ ሆነ ማን ያውቃል?”
10 እግዚአብሔርም ምን እንዳደረጉና ከክፉ መንገዳቸውም እንዴት እንደ ተመለሱ ባየ ጊዜ ራራላቸው በእነርሱም ላይ ሊያመጣ ያሰበውን ጥፋት አላደረገም
ትንቢተ ዮናስ 3:5-10

የነነዌ ህዝብን በምህረቱ የጎበኘ ቸር አምላክ እግዚአብሔር ለሀገራችንም ለህዝባችንም ምህረትና ቸርነቱን ያብዛልን ፆሙን የበረከት ፆም ያድርግልን አሜን

መልካም ጾም ይሁንልን

✝ኦርቶዶክስ ተዋህዶ✝

#መልካም_እለት

https://t.me/OrtoPicture
https://t.me/OrtoPicture
https://t.me/OrtoPicture


ጾመ ነነዌ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአጽዋማት ቀኖና መሠረት ሰባት የዐዋጅ ጾም አጽዋማት አሉ። ከሰባቱ አጽዋማት አንዷ በዕለታት ተወሳክና በዓመቱ መጥቅዕ ድምር ውጤት ወይም በመባጃ ሐመር የምትውለዋ ጾመ ነነዌ ናት።

ጾመ ሰብአ ነነዌ (የነነዌ ሰዎች ጾም) የምትጾመው ለሦስት ቀናት ነው፡፡ ጾሙ የሚጀመርበት ዕለትም ልክ እንደ ዐቢይ ጾም ሰኞን አይለቅም፡፡ ጾሙ የሚጀመርበት ቀን ደግሞ ሲወርድ ወይም ወደ ኋላ ሲመጣ እስከ ጥር ፲፯ ቀን ድረስ ነው፡፡ ሲወጣ ወይም ወደ ፊት ሲገፉ ደግሞ እስከ የካቲት ፳፩ ድረስ ነው፡፡ በእነዚህ ፴፭ ቀናት/ዕለታት/ ስትመላለስ ትኖራለች፡፡ ከተጠቀሱት ዕለታት አይወርድም፤ አይወጣም ማለት ነው፡፡ በዚህም ቀመር መሠረት የ፳፻፲፯ ዓ.ም ጾመ ነነዌ የካቲት ሦስት ጀምሮ በአምስት ያበቃል፡፡

ጾመ ነነዌን የጾሙት በነነዌ የሚኖሩ ሰዎች በአምላካችን እግዚአብሔር ትእዛዝ እና በነቢዩ ዮናስ ነጋሪነት ነው፡፡ የነነዌ ሰዎች ኃጢአታቸው ቅድመ እግዚአብሔር ደርሶ በኃጢአታቸው ምክንያት ሊያጠፋቸው ሲል ቸርነትና ምሕረቱ የማያልቅበት አምላካችም ነቢዩ ዮናስ መክሮ ዘክሮ እንዲመልሳቸውና ንስሐ እንዲገቡ ወደ ነነዌ ሕዝብ እንዲሄድ አዘዘው፡፡ (ዮናስ. ፬፥፲፩)

እግዚአብሔርም “ሄደህ በነነዌ ላይ ስበክ” ባለው ጊዜ “አንተ መሐሪ ነህ፤ ልትጠፉ ነው ብዬ ተናግሬ ብትምራቸው ሐሰተኛ ነቢይ እባላለሁ” ብሎ ላለመታዘዝ እስራኤልን ለቆ በመርከብ ወደ ተርሴስ ሸሸ፡፡ እግዚአብሔር ግን ታላቅ ነፋስን አስነሥቶ መርከቧ በማዕበል እንድትመታ አደረገ፡፡ ከዮናስ ጋር በመርከቧ ተሳፍረው የነበሩት ነጋድያንም ያላቸውን ሀብት ወደ ባሕሩ መጣል ሲጀምሩ ነቢዩ ዮናስ “በእኔ ምክንያት የመጣ ስለሆነ ንብረታችሁን ሳይሆን እኔን ወደ ባሕር ጣሉኝ” ብሎ ተማጸናቸው፡፡ እነርሱም “የሰው ደም በእጃችን እንይሆንብን አይሆንም” ብለው ዕጣ ተጣጣሉ፤ ዕጣውም በዮናስ ላይ ወጣ፡፡ ነጋድያኑም ዮናስን ወደ ባሕሩ ጣሉት፡፡ ወዲያው የእግዚአብሔርን የማዳን መልእክት ዮናስ እንዲያደርስ፣ የታዘዘ ታላቅ ዓሣ አንበሪ ዮናስን በአፉ ተቀብሎ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት አሳድሮ ነነዌ አደረሰው፡፡

ዮናስም ከእግዚአብሔር መኮብለል አለመቻሉን ሲረዳና ነነዌ መሬት ላይ መድረሱ ሲነገረው ለነነዌ ሰዎች “ንስሐ ግቡ” ብሎ መስበክ ጀመረ፤ (ዮናስ ፩ እና ፪)፡፡ መጀመሪያ ከተልእኮው ቢያፈገፍግም “ዮናስም የአንድ ቀን መንገድ ያህል ወደ ከተማይቱ ውስጥ ሊገባ ጀመረ፤ ጮኾም፦ በሦስት ቀን ውስጥ ነነዌ ትገለበጣለች አለ” እንደተባለው ነቢዩ ዮናስ የኋላ ኋላ ወደ ነነዌ ሄዶ የእግዚአብሔርን መልእክት ዐውጇል። (ዮናስ ፴፫፥፬) በዚያን ጊዜ የነበሩት ሰዎችም እንዲህ አደረጉ፤ “የነነዌም ሰዎች እግዚአብሔርን አመኑ፤ ለጾም ዐዋጅ ነገሩ፥ ከታላቁም ጀምሮ እስከ ታናሹ ድረስ ማቅ ለበሱ” (ቁጥ.፭) እንዲል፡፡

መጽሐፉ የነነዌ ሰዎች ንስሐ በገቡ ጊዜ እግዚአብሔር እንደማራቸው ይገልጻል፡፡ (ዮናስ ፫) ነቢዩ ዮናስም ውሸታም ላለመባል መኮብለሉ ስሕተት መሆኑን አምላካችን ቅልን ምሳሌ በማድረግ አስረዳው፡፡ (ዮናስ ፬) ነቢየ ሐሰት እንዳይባልም ለቅጣት የመጣው እሳት እንደ ደመና ሆኖ ታይቶአል፡፡ የታላላቅ ዛፎች ቅጠል እስኪጠወልግ ድረስ የእሳቱ ወላፈን ነክቷቸው ለሕዝቡ አሳይቷቸዋል፡፡ በንስሐ በጾምና ራሳቸውን ዝቅ በማድረግ ከእግዚአብሔር ጋር ታርቀው ከጥፋትና መዓት ድነዋል።

እኛንም ካለንበት መከራ፣ ችግርና ሥቃይ እንዲያወጣን፣ በሰላም፣ በፍቅርና በአንድነት እንዲያኖረን እንደ ነነዌ ሰዎች ንስሐ እንግባ፤ በጸሎት፣ በጾምና በበጎ ምግባር ተወስነን በሃይማኖት እንጽና! 

አምላካችን እግዚአብሔር ቸርነቱን ያብዛልን፤ አሜን!

#ጸሎተ ዮናስ ነቢይ

ጸራኅኩ በምንዳቤየ ኀበ እግዚአብሔር አምላኪየ

ወሰምዐኒ በውስተ ከርሠ ሲኦል

ወሰምዐኒ ቃልየ

ወገደፈኒ ውስተ ማዕምቀ ልበ ባሕር

ወአፍላግኒ ዐገቱኒ

ኵሉ ማዕበልከ ወሞገድከ እንተ ላዕሌየ ኀለፈ

ወእቤ ተኀጐልኩኑ እንጋ እምቅድመ አዕይንቲከ

ሀሎኩኑ እርአይ ጽርሐ መቅደስከ

አኅዘዘኒ ማይ እስከ ነፍስየ

ወቀላይኒ መልዐኒ

ናሁ ርዕስየ ውስተ ጥንቃቃተ ደብር

ወወረድኩ ውስተ ምድር ከመ መልሕቅ ታሕተ

ትዕርግ ሕይወትየ ዘእንበለ ሙስና ኀቤከ እግዚኦ አምላኪየ

ሶበ ኀልቀት ነፍስየ ተዘከርክዎ ለእግዚአብሔር

ትብጻሕ ጸሎትየ ቅድሜከ ጽርሐ መቅደስከ

እለሰ ዐቀቡ ከንቶ ወሐሰተ ገደፉ ሣሕሎሙ

አንሰ ምስለ ቃለ ስብሐት በተጋንዮ እሠውዕ ለከ

መጠነ ጸለይኩ በሕይወትየ አዐሥዮ ለእግዚአብሔር
https://t.me/mkpublicrelation
በማኅበረ ቅዱሳን የተዘጋጀና edit የተደረገ

✝ኦርቶዶክስ ተዋህዶ✝

#መልካም_እለት

https://t.me/OrtoPicture
https://t.me/OrtoPicture
https://t.me/OrtoPicture


ቅድስት ሶፍያ
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ጥር ሠላሳ በዚች ቀን
ቅድስት ሶፍያና እና የከበሩ ሶስቱ ደናግል ልጆቿ ጲስጢስ አላጲስና አጋጲስ ስለ ክርስቶስ ፍቅር በሰማዕትነት አረፉ
የተባረከች እናታቸው ሶፊያም ከአንፆኪያ ከከበሩ ወገኖች ውስጥ ናት የልጆቿም የስም ትርጉም ሃይማኖት ተስፋ ፍቅር ነዉ
የራሷ ስም ትርጓሜም ጥበብ ማለት ነው
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎታቸው ይማረን በርከታቸው ከኛጋር ትኑር ለዛላለሙ አሜን
መልካም በዓል

✝ኦርቶዶክስ ተዋህዶ✝

#መልካም_እለት

https://t.me/OrtoPicture
https://t.me/OrtoPicture
https://t.me/OrtoPicture

Показано 16 последних публикаций.