ኦርቶዶክስ ተዋህዶ


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана



Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций


ምስባክ ዘነግህ አመ ፳፰ ለጥር

👉👉@misbakze👈👈


ግጻዌ አመ ፳፰ ለጥር

👉👉@misbakze👈👈






ጥር 24

ኢትዮጲያዊው ጻድቅ አባታችን አቡነ ተክለ ሐይማኖት እግራቸው በጸሎት ብዛት የተሰበረበት ዕለት ነው
አባታችን በጸሎታቸው ሀገራችንን ከመከራ ይጠብቁልን

መልካም በዓል

✝ኦርቶዶክስ ተዋህዶ✝

#መልካም_እለት

https://t.me/OrtoPicture
https://t.me/OrtoPicture
https://t.me/OrtoPicture


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

††† ጥር 24 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1አቡነ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት
2.ቅድስት ማርያ ግብጻዊት
3.ታላቁ አባ ቢፋ
4.አባ አብሳዲ ቀሲስ
5.ቅዱሳን ጻድቃነ ሐውዚን

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን




[ጥር ፳፩ የእመቤታችን ዕረፍትና የሊቃውንት ውዳሴ]
✍ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
💥የቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት እንደገለጹልን የቅድስት ድንግል ማርያም መላ ዕድሜዋ 64 ሲኾን ይኸውም በእናት ባባቷ ቤት 3 ዓመት፤ በቤተ መቅደስ 12 ዓመት፤ ጌታን ፀንሳ በቤተ ዮሴፍ 9 ወር ከ5 ቀን፤ ከልጇ ጋር 33 ዓመት ከ3 ወር፤ በቤተ ዮሐንስ 15 ዓመት ከቆየች በኋላ፤ ልጇ ክርስቶስ ለእናቱ ተገልጾ ከኀላፊው ዓለም ወደ ማያልፈው ሰማያዊዉ ዓለም ሊወስዳት እንደኾነ ነገራት።

💥 ርሷም ይኽነን ለሐዋርያት ነገረቻቸው፤ እነርሱም “አይቴ ተሐውሪ እግዝእትነ” (እመቤታችን ወዴት ትኼጃለሽ) ብለው ሲጠይቋት “ኀበ ጸውአኒ ወልድየ” (ልጄ ወደጠራኝ) በማለት ወደዚያኛው ዓለም የመኼጃዋ ጊዜ እንደደረሰ ነገረቻቸው፤ ይኽነን ሰምተው “ወበከዩ ኲሎሙ ሐዋርያት” ይላል ሐዋርያት በእጅጉ ዐዘኑ አለቀሱ፤ ያን ጊዜ የአምላክ እናት ፊት ተሰብስበው ከእጆቿ በረከትን አገኙ፡፡

💥 ያን ጊዜ ቅዱሳን መላእክት ተገልጸው ሐዋርያትን ማዕጠንታቸውን ይዘው ደስ አሰኝተው እንዲሸኝዋት እንጂ እንዳያዝኑ እንዳያለቅሱ በመንገር አረጋጓቸው፤ ጌታም ተገልጾ "ዛሬ ለዘጠኝ ወራት በምድር ላይ መኖሪያዬ ኾና የቆየችውን ድንግል እናቴን የምቀበልበት እና ከእኔ ጋር ወደ ሰማያት ሰማያዊ ቦታዎች ይዤያት በመውሰድ ለመልካሙ አባቴ በስጦታ የማስረክባት ቀን ነው፣ ዳዊትም እንኳን “በኋላዋ ደናግሉን ለንጉሥ ይወስዳሉ፤ ባልንጀሮችዋንም ወደ አንተ ያቀርባሉ” (መዝ ፵፬፥፲፬) እንዳለ በማለት ተናገረ።

💥 ከዚያም ጌታ እናቱን "የኔ ውድ እናት ሆይ ተነሥተሽ ወደ እኔ ነዪ፤ በመጠቅለያ ጨርቆች እንደጠቀለልሽኝ ኹሉ የእኔ ድንግል እናት ማርያም ሆይ በወለድሽኝ ዕለት በከብቶች በረት ከላም እና አህያ ጋር በአንድ ላይ ከብበውኝ እንዳኖርሽኝ ኹሉ (ኢሳ ፩፥፫፤ ሉቃ ፪፥፯)፤ እኔ ደግሞ ዛሬ ከእኔ ጋር ከሰማያት ባመጣዋቸው በሰማይ መጐናጸፊያ ሰውነትሽን እጠቀልለዋለኊ፤ ከዚያም ከሕይወት ዛፍ ሥር አስቀምጠዋለኊ፣ ኪሩቤልም በነበልባላማ ሰይፋቸው እንዲጠብቁት አደርጋለኊ (ዘፍ ፫፥፳፬)፡፡

💥 የተባረከችውን ነፍስሽን የሰማያዊቷ ኢየሩሳሌም መንበር በተሸፈነችበት መሸፈኛዎች እንድትሸፈን አደርጋለኊ፡፡ እኔን በሚያሳድድበት ጊዜ ሥርዓት አልባውን ሄሮድስ በመፍራት ወደ ግብጽ ምድር እንደተሰደድሽው ኹሉ (ማቴ ፪፥፲፫-፲፰)፤ መላእክቶቼ ኹልጊዜም በክንፎቻቸው እያጠሉብሽ እና መልካም ዝማሬያቸውን እንዲዘምሩልሽ አደርጋለኊ አላት፡፡

💥 ይኽን ከልጇ በሰማች ጊዜ ጥር 21 እሑድ ዕለት በልጇ ፈቃድ በመዐዛ ገነት፣ በመዝሙረ ዳዊት፣ በይባቤ መላእክት የእመቤታችን ነፍሷ ከሥጋዋ ተለየ።

♥❖♥ ቅዱስ ያሬድም በመጽሐፈ ድጓው ላይ፡-
“ጊዜ ዕረፍታ ለሶልያና (ለማርያም)
ወረደ ወልድ እምዲበ ልዕልና
ጠሊሳነ ንግሥ ሶቤሃ ከደና”

(በማርያም ዕረፍት ጊዜ ወልድ ከልዕልና ወረደ፤ የንግሥና (የክብር) መጐናጸፊያን በዚያን ጊዜ ሸፈናት) በማለት የዕረፍቷን ነገር አስተምሯል፡፡

♥❖♥ የመልክአ ማርያምም ጸሐፊ በአድናቆት፦
“ሰላም ለፀአተ ነፍስኪ እንበለ ጻዕር ወጻማ
ለነቢር ዘልፈ በየማነ ወልድኪ ፌማ”

(ከሃሊ (ማእምር፣ ጠቢብ) በሚኾን ልጅሽ ቀኝ ዘወትር ለመቀመጥ ያለ ድካምና ያለ ጣር ለኾነ የነፍስሽ መለየት ሰላምታ ይገባል) ብሏታል፨

💥 ጌታም እንደ በረዶ ጸዐዳ የኾነውን የድንግል ማርያምን ነፍስ በዕቅፉ ውስጥ እንደያዘ ለነፍሷ ሰላምታውን ሰጥቶ ባማረው ሸማ ጠቅልሏት ለሊቀ መላእክት ለቅዱስ ሚካኤል በብርሃናማ ክንፎቹ እንዲሸከማት ሰጠው፤ የከበረ ሥጋዋም የጠራና መዐዛው ድንቅ ነበር።

♥❖♥ የመልክአ ማርያም ደራሲው ሊቁ፦
“ሰላም እብል በድነ ሥጋኪ ጽሩየ
ዘተመሰለ ባሕርየ"

(ዕንቊን ለተመሰለ የጠራ የሥጋሽ በድን ሰላም እላለኊ) በማለት ያመሰግናል።

💥 ከዚያም ቅዱሳን ሐዋርያት በዚያ አስደናቂ መጎናጸፊያ በክቡራን ሽቱዎች የከበረ ሥጋዋን አጅ እየነሡ ገንዘዋታል።

💥 ሊቁም በመልክአ ማርያም ላይ፦
“ሰላም ለግንዘተ ሥጋኪ በእደ ሐዋርያት አርጋብ
በአፈወ ዕፍረት ቅድው ዘሐሳበ ሤጡ ዕጹብ"

(የዋጋው ስሌት እጅግ ውድ በኾነ ያማረ ሽቱ ርግቦች በተባሉ በሐዋርያት እጅ ለተደረገ የሥጋሽ አገናነዝ ሰላምታ ይገባል) በማለት ያመሰግናል።

♥❖♥ ከኢትዮጵያ ሊቃውንት መኻከል ስለዚኽ በቅዱሳን ሐዋርያት ስለተደረገው የከበረ የሥጋዋ ግንዘት ቅዱስ ያሬድ አምልቶ አስፍቶ የጻፈ ሲኾን፤ በነሐሴ ፲፭ በአጫብሩ ድጓ ውስጥ በአስደናቂ መልኩ እንዲኽ ተጽፈዋል፡-

♥ “ሐዋርያት አመድበሉ
ሥጋ ድንግል ጠብለሉ
በሰንዱነ ብርሃን ዘላዕሉ
ልብሳ ተካፈሉ”

(ሐዋርያት ተሰበሰቡ፤ ከላይ በመጣ በፍታ (መጐናጸፊያ) የድንግል ሥጋን ጠቀለሉ፤ ልብሷንም ተካፈሉ)፨

♥ “በደመና ተጋቢኦሙ ሐዋርያት ለድንግል ንጽሕት
ገነዝዋ በክብር ወበስብሐት
ለቀበላሃ ወረዱ ኀይላት
ወቀበርዋ ውስተ ገነት”

(ሐዋርያት በደመና ተሰብስበው ንጽሕት ድንግልን በክብር በምስጋና ገነዟት፤ ለአቀባበሏ ኀይላት ወረዱ፤ በገነት ውስጥም ቀበሯት)፨

♥ “ተጋቢኦሙ ሐዋርያት እምኲለሄ
በደመናት ዘምሉእ ሡራኄ
ገነዙ በክብር ወበስባሔ
ሥጋ ድንግል ዘይምዕዝ እምርሔ”

(ብርሃንን የተመላ በኾነ በደመናት ሐዋርያት ከአራቱ ማእዝን ተሰብስበው ልብን ከሚመስጥ ሽቱ ይልቅ የሚሸትት የድንግልን ሥጋ በክብርና በምስጋና ገነዙ)፨

♥ “ተጋቢኦሙ በደመና ሰማይ
ሐዋርያት ሥርግዋን በዕበይ
ገነዝዋ ለድንግል በብዙኅ ግናይ
ዳዊት ዘመራ በመሓልይ”

(በገናንነት የተጌጡ ሐዋርያት በሰማይ ደመና ተሰብስበው ድንግልን በብዙ ምስጋና ገነዟት፤ ዳዊትም በምስጋና አመሰገናት)፨

♥ “ተጋቢኦሙ አርድዕተ ወልዳ
በደመና ብርሃን ጸዐዳ
ገነዝዋ በስብሐት ለጽርሕ ሳይዳ”

(ጸዐዳ በኾነ በብርሃን ደመና የልጇ ደቀ መዛሙርት ተሰብስበው፤ ውቢቱ አዳራሽን በምስጋና ገነዟት)፨

♥“ተጋብኡ በቅጽበት ለግንዘተ እሙ ቅድስት
ብፁዓን ሐዋርያት
ቦኡ ኀቤሃ በሰላም አምኁ ኪያሃ
በስብሐት ገነዙ ሥጋሃ”

(ንኡዳን ክቡራን ሐዋርያት ቅድስት የምትኾን የጌታ እናቱን ለመገነዝ በቅጽበት ተሰበሰቡ፤ ወደ ርሷ ገብተው በሰላምታ ርሷን እጅ ነሧት፤ ሥጋዋንም በምስጋና ገነዙ) በማለት ሊቁ ማሕሌታይ በሐዋርያት እጅ የተደረገ የሥጋዋን ግንዘት አምልቶ አስፍቶ ጽፏል፡፡

♥ ከዚያም ወዲያውኑ የድንግልን የከበረ አካል ወደ ላይ በማንሣት ቅዱስ ጴጥሮስ ራሷን፣ ቅዱስ ዮሐንስ እግሮቿን ተሸክመው የተቀሩት ሐዋርያት በእጆቻቸው የዕጣን ማዕጠንት ይዘው በታላቅ ግርማ በአምላክ እናት ሥጋ ፊት ምስጋናን እያሰሙ ዝማሬን እየዘመሩ ሥጋዋን እጅ እየነሡ ጌቴሴማኒ ሊቀብሯት ሲኼዱ አይሁድ አይተው “ንዑ ናውዒ ሥጋሃ ለማርያም ምስለ ዓራታ” በማለት በምቀኝነት ተነሡባቸው፤ ታውፋንያ የሚባል ከአይሁድ ወገን በድፍረት የአልጋዋን አጎበር ሊነካ ሲሞክር ቅዱስ ገብርኤል በሰይፈ እሳት ቀጣው፡፡

♥ ያን ጊዜ ቅዱስ ዮሐንስ በዕለተ ዐርብ ከአምላኩ በስጦታ የተሰጠችውን የአምላክ እናትን ሥጋዋን በድፍረት ሊነኩ መምጣታቸውን አይቶ “ዐደራዬን አላፈርስም፤ ከርሷ ጋር እሞታለኊ" በማለት ይኽነን ተናግሮ በላይዋ ላይ ወደቀ፡፡

♥ ከዚያም “ወወረዱ ሚካኤል ወገብርኤል እምሰማይ በዐቢይ ግርማ” ይላል ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል በታላቅ ግርማ ወርደው የቅድስት ድንግል ማርያምን ሥጋዋንና ቅዱስ ዮሐንስን በደመና ነጥቀው በገነት በሕይወት ዛፍ ሥር አኖሯት፡፡


ቅዳሜ ይጾማል ወይ ?

ጥምቀት እሑድ ቀን በሚውልበት ጊዜ የራሱ አዋጅ አለው ። የጥምቀት በዓል ደግሞ የዋለው እሑድ ነው ። በዚህም መሰረት አዋጁ ቅዳሜን እንድንጾም ያዝዘናል ። ስንጾምም ጥሉላት ምግቦችን ከመብላት ነው ።ስለዚህም ቅዳሜ ከቅዳሴ በሗላ ጥሉላት ያልሆኑትን ምግቦችን መብላት እንችላለን ። ነገር ግን ቀድሞ ያለውን አርብ እስከ 12 ሰአት እንጾማለን ።


https://t.me/geeZzlekulu


#በዓለ_ጥምቀት_ቅዳሜ_እሑድ_ቢውል
ጾመ ጋድ_ይጾማል
ብዙዎቻችን ስለ ጾመ ጋድ ስናስብ በዓለ ልደትና በዓል ጥምቀት ረቡዕ እና አርብ ከዋሉ ብቻ የሚጾም አድርገን እንወስዳለን። ጾመ ጋድ ከሰባቱ አጽዋማት መካከል አንዱ ነው። በልደትና በጥምቀት ዋዜማ ላይ ይጾማል። ጋድ ማለት ለውጥ ማለት ነው። በዓላቱ ረቡዕና አርብ ቢውሉ የዚያ ለውጥ ማክሰኞና ሐሙስን ጾመን በዕለቱ ጥሉላትን እንመገባለንና እንዲህ ተብሏል አንድም ገሀድ ይባላል መገለጫ ማለት ነው በልደቱ አምላክ ሰው ሆኖ በጥምቀቱ ደግሞ ብርሃነ መለኮቱን ገልጦ አይተነዋልና
ወደ መነሻ ሀሳባችን ስንመለስ በቤተ ክርስቲያናችን የሕግና የሥርዓት መጽሐፍ በሆነው ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ 15 ላይ ስለ አጽዋማት በሚናገርበት ሐተታው ጾመ ጋድ ከረቡዕና ከአርብ ውጭ ባሉት ቀናት ቢውሉ ዋዜማው እንደሚጾም « ሥርዓት አንድ ጊዜ ከተሠራ አይፈርስምና አንድም አንድ ጊዜ ሲጾም አንድ ጊዜ ሲቀር እንዳይረሳ » በማለት በዓመት በዓመት ጾመ ጋድ እንዳለ ይነግረናል

የሰንበታቱን (የቅዳሜና የእሑድን) ለየት የሚያደርገው ደግሞ ለምሳሌ ልክ ዘንድሮው በዓለ ጥምቀት እሑድ ቢውል ቅዳሜ ሰንበት ስለሆነ ሰዓት እንደሌሎች የአጽዋማት ዕለታት እህል ሳንቀምስ ባንውልም ከጥሉላት ምግቦች ግን ተከልክለን መቆየት እንዳለብን ይደነግጋል። ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንም በዚሁ ላይ ሲጨምሩ በዓለ ጥምቀት ቅዳሜ ወይም እሑድ እንዲሁም ሰኞ ቢውል ቀድሞ ባለው ዕለተ አርብ የጾማችንን ሰዓት ከፍ አድርገን በመቆየት የጾመ ጋድን ጾም ደርበን እንድንጾም ያስተምራሉ።

ጥር - 9-2017 ዓ,ም
◈⊰───── © እሱዬ ይማም

✝ኦርቶዶክስ ተዋህዶ✝

#መልካም_እለት

https://t.me/OrtoPicture
https://t.me/OrtoPicture
https://t.me/OrtoPicture




Репост из: የአእላፋት ዝማሬ | Melody of Myriads
የአእላፋት ዝማሬ ለፓሪስ ኦሎምፒክ ጸያፍ ትርዒት ምላሽ ሠጠ
| ጃንደረባው ሚድያ | ታኅሣሥ 2017 |
አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ

የ2017 ዓ.ም. የአእላፋት ዝማሬ ላይ "የገና መልእክት ከኢትዮጵያውያ ሰዎች ወደ ኦሎምፒከኞች" (A Christmas Message from Myriads to Olympiads) በሚል ርእስ የሁለት ደቂቃ አኒሜሽን ታየ:: የዚህ መልእክትም ዋነኛ ሃሳብ ከአራት ወራት በፊት በፓሪስ ኦሎምፒክ መክፈቻ ላይ የጸሎተ ሐሙስ ሥዕል ላይ ጸያፍ መልእክቶችን በማስተላለፍ የተደረገውን ተሳልቆ ለጸሎተ ሐሙስ ሥዕልና ለከበረው የክርስቶስ ደም ክብር የምትሠጠው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንን ምን ያህል እንዳስቆጣ ለማሳየት ነው:: "እነርሱ በስሙ ሲዘብቱ ኢትዮጵያ ግን ዳግመኛ እጆችዋን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች" (When they mock his name in vain, Ethiopia lifts her hands to God again) የሚል መልእክት ያለው ይህ ቪድዮ የፓሪስ ኦሎምፒክ አዘጋጆችን ድርጊት በክርስቶስ ላይ የጥላቻ ጦር ከሰበቀው ከንጉሥ ሔሮድስ ድርጊት ጋር በማመሳሰል የተሠራ መሆኑን የአኒሜሽኑ ዳይሬክተር ወ/ሪት ቅድስት ፍስሓ ገልጻለች::

"ዓለም አቀፍ መክፈቻ ሥነ ሥርዓቶችና ምርቃቶች በተካሔዱ ቁጥር በክርስትና መቀለድና ሰይጣናዊ ትርዒቶችን ማሳየት እየተለመደ መጥቶአል" ያሉት የአኒሜሽኑ ክሪኤቲቭ ዳይሬክተር ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ በበኩላቸው "ዓለም አቀፍ ሚድያዎች ከፍተኛ ሽፋን እየሠጡት ባለው በአእላፋት ዝማሬ ላይ ለዓለም አቀፉ ተመልካች የሚሆን መልእክት ለማስተላለፍ አጋጣሚውን ተጠቅመንበታል" ብለዋል::


♥♥♥ እናትኽ በደስታ ተመልታለች፣ ዮሴፍም በደስታ ተመልቷል፤ አንተም በደስታ የተመላኽ ነኽ፤ የፋሲካ ደስታ ጠቦት የኾንኽ ሆይ! (፩ኛ ቆሮ ፭፥፯) አንተን የወለደች ማርያም አንተን ስትስምኽ ደስ ይላታል! ቀበሮ ሰነፍ ንጉሥ የነበረው ሄሮድስ በድምፁ የሚርበተበትበት የአንበሳ ደቦል ነኽ (ዘፍ ፵፱፥፱፤ ማቴ ፪፥፫) አገዛዙን አበቃኽለት በርሱ ቁጥጥር ሥር የነበረው የራስኽን አገዛዝ ተረከብኽ (ማቴ ፪፥፳)፤ አንተ ንጉሥና የነገሥታት ኹሉ ንጉሥ ነኽ (ራእ ፲፯፥፲፬)፡፡

♥♥♥ አዳምን ከዐቧራ ፈጥረኸዋል (ዘፍ ፪፥፯) የራስኽንም እናት ፈጥረኻል (ሉቃ ፩፥፴፰)፤ ቀዳማዊ ልደትኽ ከአብ የኾንኽ የአንተ ፈቃድ የአንተን ኲለንታ ትስብዕት ቀረጸ፤ የራስኽን መለኮታዊ አኗኗር ሊታወቅ አይቻልም አንተ መዠመሪያ የለኽምና (ዮሐ ፩፥፩)፤ አንተ ስለፈቀድኽ ራስኽን በማርያም ውስጥ አኖርኽ፡፡

♥♥♥ እዚያም እናትኽ፣ ምርጥኽ፣ የእጅኽ ሥራ አገልጋይኽ ማርያም ተንበርክካ አንተን ወልዳለች (ሉቃ ፪፥፯)፤ አንተም ስትወልድኽ፣ ዕቅፍ አድርጋ ስትስምኽ በምስጋናና በጸሎት ታመሰግንኻለች አንተን ስታቅፍኽ ወተቷን ታጠባኻለች ለአንተ በመዘመርና በሕፃንነትኽ መንገድ ፈገግ በማለት፣ አንተ ወተቷን እየጠባኽ በደስታ ስትመላ፣ አንተን የወለደችኽ ለአንተ ወተት ያጠባችኽ በአድናቆት ትዋጣለች፤ አንተ የፈጠርኻት እጅግ ተደምማለች።

♥♥♥ ወልድ ሆይ በአንተም አማካይነት የእናትኽ አእምሮ ይረፍ፤ የእናቱ አስተማሪ፣ የእናቱ አምላክ፣ የእናቱ ጌታ፣ ከእናቱ ወጣትም አዛውንትም የኾነ፣ እስከአኹንም ድረስ በአድናቆት የመላኸኝ አንተ ነኽ (ሉቃ ፪፥፲፱)፤ የአንተ ዕውቀት ያስጨንቀኛል፤ በአንተ ላይ ዐይኑን ሊያሳርፍና በአንተ መዐዛ ሊተነፍስ የማይችል ማን አለ? ድክ ድክ ስትል ተመልካቾች ኹሉ ይደነቃሉ (ሉቃ ፪፥፵፮-፶፩)።

♥♥♥ እናም የአንተ አገላለጽ ኹናቴ ዐዋቂዎችን ፍጥረታትን ያስገርማል፤ ታስገርማለኽም፣ ታናናሾች እጆችኽ ያጨበጭባሉ፣ እግሮችም ይመታሉ፤ በማንኛውም መንገድ እንዴት ተፈቃሪ ነኽ፤ የአንደበትኽ ጒርምርምታ እንኳን ስለአባትኽ ይናገራል (ሉቃ ፪፥፵፱)፡፡

♥♥♥ ውበትኽ ምን ያኽል ታላቅ ነው (መዝ ፵፬፥፪)፤ ብላቴና የኾንኸው እግዚአብሔር ሆይ፣ አፍኽ እንደ ማር ወለላ በጣም ጣፋጭ ነው! ከአፍኽ የሚወጣው ኀይል የሰማያት አካላት እንዲርበደዱ ያደርጋል፤ በአንተ አንድ ድምፅ ይኽ ኹሉ ፍጥረት እንዴት ይሸበራል ብላ ማርያም ተደንቃ ትቆማለች (ሉቃ ፪፥፲፲፱)፤ አንተ በአንተ ጸጋ (ቸርነትን) ለኹለቱም ዓለማት የምትሰጥ ስትኾን ግን በዚኽ ላይ ከፈጠርካት እናትኽ ወተቷን ትጠባለኽ፡፡

♥♥♥ ያንተን ልደት በመዝሙር እንድናገር ላበቃኸኝ አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ሆይ ምስጋና ይግባኽ፤ ለእኔ ጒድለት ራራ ይቅር በል፤ ለአንተ ለጌታዬ ምስጋና ላቀርብና ላመስግንኽ ምክንያቱም ከአንተ ስጦታ የተነሣ ምስጋናኽን እዘምራለኊ፤ በተወለድኽበት ቀን ኀጢአታችንን ይቅር በል፣ እናም በቸርነትኽ ለተበላሸው ሕይወታችን ፈውስን አምጣልን፤ ሰላም ይኹን ጌታዬ፤ በሕዝብኽና በቤተ ክርስቲያንኽ ላይ ግዛ፤ በጣም ክቡር የባሕርይ አምላክ ለኾንኸው አምላክ በአንተ የበዓል ቀን ጌታ ምስጋና ይግባኽ!)”  ይላል ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ
[ሙሉውን ከነገረ ማርያም በሊቃውንት መጽሐፌ አንብቡ]

♥እናንተም ዘምሩ አመስግኑ ድንቅ ስለኾነው የአምላክ ልደት♥




Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
የገና መልእክት ከኢትዮጵያ ሰዎች ወደ ኦሎምፒከኞች


ሦስቱ የእምነት መመሪያዎች
1.ዶግማ ምንድነው
2.ቀኖና ምንድነው
3.የቀኖና ቤተ ክርስቲያን መገለጫዎች
4. ቀኖና በመጽሐፍ ቅዱስ
5.የቀኖና ቤተ ክርስቲያን ምንጮች
6.የቀኖና ቤተ ክርስቲያን ጥቅሞች
7.ትውፊት ምንድነው


1.ዶግማ ምንድነው
ዶግማ ፡- ዶከይን ከሚለው የግሪክ (የጽርእ) ቃል የተገኘ ሲሆን በጥሬው አመለካከት፣ አስተሳሰብ፣ አዋጅ ማለት ቢኾንም በምሥጢራዊ ማለትም እንደ ቤተ ክርስቲያን አተረጓገም ግን የማይለወጥ፣ የማይቀየር፣ የማይሻሻል፣ የማያረጅ መሠረተ እምነት ማለት ነው፡፡ በመኾኑም ዶግማ የተደነገገ ሳይኾን የተገለጠ ነው፡፡ መገኛውም እግዚአብሔር ነው፡፡ ከሰው ሊፈጠር አይችልም፡፡ ከእግዚአብሔር የተሰጠ እውነት ነው፡፡ በማኝኛውም አካል (በሲኖዶስም ጭምር)፣ በየትኛውም ዘመን፣ በየትኛውም ኹኔታ (በሞትም በሕይወትም) የማይለወጥ ማንነት አለው፡፡
ዶግማ የቤተ ክርስቲያን መሠረታዊ ትምህርተ ሃይማኖት ነው ብለናል፡፡ ስለ ቅድስት ሥላሴ፣ ስለ ምሥጢረ ሥጋዌ ፣ ስለ ምሥጢረ ጥምቀት፣ ስለ ምሥጢረ ቁርባን፣ ስለ ቤተ ክርስቲያንና ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን፣ ስለ ክብረ ድንግል ማርያምና ክብረ ቅዱሳን የምንማረው ነው እንጂ ማናችንም ልናሻሽለው አንችልም፡፡ እንኳንስ አንድ ግለሰብ ይቅርና ሲኖዶስም ቢኾን አለመለወጡን፣ አለመፋለሱን መርምሮ ሃይማኖታችን ይህ ነው በማለት ያሳውቃል እንጂ መጨመር ወይም መቀነስ አይችልም፡፡ ሐዋሪያው ቅዱስ ጳውሎስ፡- ‹‹ነገር ግን (ሐሳባችንን ቀይረን) እኛ ብንኾን ወይም ከሰማይ መልአክ ከሰበክንላችኁ ወንጌል የሚለይ ወንጌልን የሚሰብክላችኁ የተረገመ ይኹን›› ያለውም ስለዚኹ ነው /ገላ.1፡8/፡፡

✝ኦርቶዶክስ ተዋህዶ✝

#መልካም_እለት

https://t.me/OrtoPicture
https://t.me/OrtoPicture
https://t.me/OrtoPicture


✝ኦርቶዶክስ ተዋህዶ✝

#መልካም_እለት

https://t.me/OrtoPicture
https://t.me/OrtoPicture
https://t.me/OrtoPicture


“ሶበ  ጸሐፈ ደቅስዮስ ተአምረኪ ቅዱሰ
መንበረ ወዐጽፈ ዕሤተ ጻማሁ ወረሰ
ማርያም ድንግል ዘታብእሊ ፅኑሰ
ዐስበ ማሕሌትየ  ዐቅመ ልብየ ኀሠሠ
ጸግውኒ አትሮንሰ ወጽጉየ ልብሰ”

(ደቅስዮስ ልዩ የኾነ ተአምርሽን በጻፈ ጊዜ የድካሙን ዋጋ ልብስንና ወንበርን አገኘ፤ ድኻውን ባለጠጋ የምታደርጊ (ነዳየ አእምሮውን በቃል ኪዳንሽ ባለ አእምሮ የምታደርጊ) ድንግል ማርያም ልቡናዬ በፈለገ መጠን የምስጋናዬን ደሞዝ ወንበርንና የክብር ልብስን ስጪኝ)  በማለት የሿሚ የክርስቶስ እናት የቅድስት ድንግልን በረከት ልክ እንደ አባ ጊዮርጊስ ሽተዋል፡፡

Показано 18 последних публикаций.