አትሮኖስ


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።

Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций


Репост из: Wave boy
🔴 ሰበር ዜና ዛሬ ትምህርት ሚኒሰትር ያወጣው አዲስ ያልተጠበቀ መግለጫ   ‼️

ሙሉ መግለጫውን ለማንበብ ከስር open ሚለውን ይጫኑ 👇👇


ከ17 ደቂቃ ቦኃላ ይጠፋል


የ 200 ብር ካርድ የሚያስሸልም ጥያቄ!

በኢትዮጵያ በጣም አስቸጋሪ የነበረዉ  ረሀብ መች አመተምህረት ነበረ


Репост из: Wave boy
✅ህጋዊ የሆነ ለ 11ኛ ና የ 12ኛ ክፍል ተማሪዎች የተከፈተ ና ከ ትምህርት ሚኒስተር እንዲሁም የፈተናዎች ኤጀንሲ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያለው የተማሪዎች የፈተና መዘጋጃ ቻናል።👇👇

ትምህርት ሚኒስቴር JOIN


​​ደርግ ዘጠነኛውን የአብዮት በዓል አስመልክቶ በጳጉሜ ወር 1975 ዓ.ም ለፖለቲካ እሥረኞች ይቅርታ ሲያደርግ ወጣቷ ልዕልት ምሕረት መኮንን ከንጉሳዊ ቤተሰብ እሥረኞች መካከል ለመለቀቅ የመጀመሪያዋ ሆነች፡፡ የደርግ “አብዮታዊ ምህረት” ሁሉንም እሥረኛ ንጉሳዊ ቤተሰብ ያካተተ ባይሆንም እሥረኞቹ እንዲፈቱ ለሚማፀኑት ዓለም አቀፍ ተቋማት ግን እንደ በጐ እርምጃ ተደርጐ ተወስዷል፡፡ ተቋማቱ ምህረቱን አስመልክተው ለኢትዮጵያ መንግሥት ምስጋናቸውን በማቅረብ ቀሪዎቹ እሥረኛ ንጉሳዊ ቤተሰቦች እንዲለቀቁ የተለመደውን ልመና አቅርበዋል፡፡

ደርግ ለንጉሳዊ እሥረኞቹ ያደረገው 2ኛ ምህረት የተከናወነው ከመጀመሪያው ምህረት አምስት አመት ያህል ቆይቶ ሚያዝያ 13 ቀን 1980 ዓ.ም ነበር፡፡ ከአሥራ ሁለት አመት በኋላ ከእሥር የተለቀቁት የ75 አመቷ አዛውንት ልዕልት ተናኘ ወርቅ ኃይለሥላሴ፣ ልዕልት ሰብለ ደስታ፣ ልዕልት ሒሩት ደስታ፣ ልዕልት አይዳ ደስታ፣ ልዕልት ሶፍያ ደስታ እና ልዕልት ሳራ ግዛው ነበሩ፡፡

ደርጉ ለንጉሳዊ ቤተሰብ 2ኛውን ምህረት ከሰጠ ከአንድ አመት ከአራት ወራት በኋላ ደግሞ ሦስተኛውንና የመጨረሻውን ምህረት ጳጉሜ 2 ቀን 1981 ዓ.ም አደረገ፡፡ ከ13 አመታት በኋላ የተለቀቁት የንጉሳዊ ቤተሰብ እሥረኞች፣ ወርቃማውን የወጣትነት ጊዜያቸውን በወህኒ ቤት ያሳለፉት፡- ልዑል በዕደማርያም መኮንን ፣ ልዑል ሚካኤል መኮንን እና ልዑል ወሰንሰገድ መኮንን ነበሩ።


የግርማዊ ጃንሆይ ቤተሰቦች በዓለም በቃኝ ወሕኒ ቤት ፤አሳዛኝ ቆይታ😔

ዘውዳዊ ሥርዓትን አስወግዶ ስልጣን መያዙን መስከረም 2 ቀን 1967 ዓ.ም በይፋ ያወጀው የደርግ ወታደራዊ መንግስት ፣ በዚሁ እለት ንጉሠ ነገሥቱን ከቤተመንግሥታቸው ይዞ 4ተኛ ክፍለ ጦር በተባለው የወታደር ሰፈር እንዲታሰሩ በማድረግ ፣ እስከ ጊዜ ሞታቸው ድረስ ለአንድ አመት ያህል አቆይቷቸዋል፡፡

ከለውጡ ማግስት ጀምሮ ንጉሳዊ ቤተሰቡ በጃንሆይ ልጅ በልዕልት ተናኘወርቅ ኃይለሥላሴ መኖሪያ ቤት ውስጥ በቁም እስር እንዲጠበቁ የተደረገ ሲሆን ከነዚህ መካከል አረጋውያን ፣ ሴቶች እና ሕፃናት ይገኙበት ነበር፡፡ ደርጉ የጃንሆይ ቤተሰቦች በቁም እስር የሚጠበቁት ምክንያት “ሰፊው ሕዝብ በግብታዊነት ተነሳስቶ የበቀል እርምጃ እንዳይወስድባቸው ነው” በማለት ለውጪ ተመልካቾች ገልፆ ነበር፡፡

ሕዳር 14 ቀን 1967 ዓ.ም “ስልሳዎቹ” ተብለው ከሚታወቁት ከዘውድ መንግሥት ባለስልጣናት ጋር የተሰውት፣ የኢትዮጵያ የባህር ኃይል ጠቅላይ አዛዥና የጃንሆይ የልጅ ልጅ፣ ሪል አድሚራል እስክንድር ደስታ በደርግ የተገደሉ የመጀመሪያው የጃንሆይ ቤተሰብ አባል ናቸው፡፡ ንጉሠ ነገሥቱ በነሐሴ 1967 ዓ.ም ያረፉት ግድያ ተፈፅሞባቸው ከሆነ ደግሞ ጃንሆይ በደርግ የተገደሉ ሁለተኛው የንጉሳዊ ቤተሰብ አባል ናቸው ማለት ነው፡፡

ደርግ በመስከረም ወር 1968 ዓ.ም በቁም እሥር የሚገኙትን ንጉሳዊ ቤተሰቦች በአዲስ አበባ ወህኒ ቤት ውስጥ የእድሜ ልክ ፍርደኞች ከሚታሰሩበትና ዓለም በቃኝ ከተባለው ክልል ውስጥ በማዘዋወር አያያዛቸውም በእሥረኛ ደንብ እንዲሆን መወሰኑ ታወቀ፡፡ ከእነዚህ የንጉሳዊ ቤተሰብ እሥረኞች ውስጥ የሚበዙት ሴቶች የነበሩ ሲሆን ወጣት ወንዶችም ይገኙበት ነበር፡፡

እሥረኞቹ ልዑላን የአፄ ኃይለሥላሴ የቅርብ ዘመዶች ከመሆናቸው በስተቀር በዘውድ መንግሥት ውስጥ የያዙት ሥልጣን ወይም ሹመት አልነበረም። ለአንድ ዓመት በቁም እስር ሲቆዩም በወንጀል አልተከሰሱም ወይም ፍርድ አልተፈረደባቸውም፡፡ ከአንድ አመት የቁም እስር በኋላ ደግሞ ይባስ ብሎ ለረጅም ጊዜ ወደሚቆዩበትና የእድሜ ልክ ፍርደኞች ወደሚታሰሩበት የአለም በቃኝ የወህኒ ክልል ውስጥ እንዲዘዋወሩ ተደረገ፡፡

በዓለም በቃኝ ከታሰሩት ንጉሳዊ ቤተሰቦች ውስጥ ልዕልት ተናኘወርቅ ኃይለሥላሴ እና ልጆቻቸው ልዕልት ሰብለ ደስታ ፣ ልዕልት አይዳ ደስታ ፣ ልዕልት ሒሩት ደስታ ፣ ልዕልት ሶፍያ ደስታ እንዲሁም ልዕልት ሳራ ግዛውና ልጆቻቸው ልዑል ወሰንሰገድ መኮንን ፣ ልዑል ሚካኤል መኮንን ፣ ልዑል በዕደማርያም መኮንንና ልዕልት ምሕረት መኮንን በተጨማሪም የልዑል አልጋ ወራሽ አስፋ ወሰን የመጀመሪያ ልጅ ልዕልት እጅጋየሁ ይገኙበት ነበር፡፡

ከእስረኞቹ በእድሜ ዝቅተኛው የ 17 አመቱ ወጣት ልዑል በዕደማርያም መኮንን ሲሆን ከፍተኛ እድሜ የነበራቸው ደግሞ የ63 አመቷ ልዕልት ተናኘወርቅ ኃይለሥላሴ ነበሩ፡፡ በወህኒ ቤት ደንብ መሰረት ልዑላኑ ወንዶችና ሴቶች በዓለም በቃኝ የታሰሩት ተለያይተው በልዩ ልዩ ክፍሎች ውስጥ ነበር፡፡

የወህኒ ቤቱ ክፍሎች ከድንጋይ የተሰሩ እና የሚያዡ በመሆናቸው ዘወትር ቅዝቃዜ አይለያቸውም፡፡ ከጥቂት የመመገቢያ ቁሳቁሶች በስተቀር ሌላ መገልገያ እንዳያስገቡ የተከለከሉት እሥረኞች የሚተኙትም በወለሉ ላይ ፍራሽ ብቻ በማንጠፍ ነበር፡፡

የደርግ መንግስት የልዑላኑን ቤትና ንብረት የወረሰ በመሆኑ፣ በምትኩ በየወሩ ብር 120 እየቆረጠላቸው ለጥቂት ጊዜ ሲቀበሉ የቆዩ ሲሆን በኋላ ላይ “ይበዛል” ተብሎ ወደ 50 ብር ዝቅ እንዲል ተደርጓል፡፡ እሥረኞቹ ከዘመዶቻቸው በቀን አንድ ጊዜ ምግብ ለመቀበል፣ በሳምንት አንድ ጊዜ አጭር ደብዳቤ ለመፃፍ እንዲሁም ለጥልፍ የሚያገለግሉ ቁሳቁስ ለማስገባት የሚችሉ ቢሆንም ጠያቂ ለማነጋገር የሚፈቀድላቸው ግን በአመት ሁለት ወይም ሦስት ጊዜ ብቻ ነበር፡፡

እሥረኞቹ ንጉሳዊ ቤተሰቦች በጣም በሚያስጨንቅ አካላዊና ሥነ ልቡናዊ ሁኔታ ላይ እንደነበሩ በጊዜው የፖለቲካ እሥረኞችን ሁናቴ እየተከታተለ መንግሥትን ይማፀን የነበረው አለም አቀፉ የሰብአዊ መብት ተሟጋች አምነስቲ ኢንተርናሽናል በጊዜው ያወጣቸው ተከታታይ ሪፖርቶች ይጠቁማሉ፡፡

የንጉሳዊ ቤተሰቡ ከነበሩባቸው በርካታ ችግሮች አንዱ የመሰረታዊ ሕክምና እጦት ነበር፡፡ ምንም እንኳን በወህኒ ቤቱ ውስጥ የጤና አገልግሎት የሚሰጥ ክሊኒክ የነበረ ቢሆንም ፣ የንጉሳዊ ቤተሰቡ ሕክምና ሆነ ተብሎ እንዲዘገይ ይደረግ ነበር፡፡ ስለዚህም በጊዜ ቢደረስበት መፍትሄ ያገኝ የነበረ ቀላል ሕመም እየተባባሰ እሥረኞቹን ለከፋ አደጋ ሲያጋልጣቸው ተስተውሏል፡፡

ለዚህም አይነተኛ ምሳሌ የሚሆኑት ልዕልት እጅጋየሁ አስፋ ወሰን ናቸው፡፡ እኒህ ሴት በወህኒ ቤት በተቆራኛቸው ደዌ ለረጅም ጊዜ ሲሰቃዩ አሳሪዎቻቸው ሕክምና እንዲያገኙ አልፈቀዱላቸውም ነበር፡፡ ህመማቸው ተባብሶ ከፍተኛ ደረጃ ከደረሰ በኋላ ግን በፖሊስ ሆስፒታል ተኝተው እንዲታከሙ ተወሰነ። ሐኪሞች ልዕልቷን ኦፕራሲዮን ቢያደርጉዋቸውም ያደረባቸው ደዌ ለረጅም ጊዜ መፍትሄ ሳያገኝ የቆየ በመሆኑ፣ ጥር 23 ቀን 1970 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

እሥረኞቹን ያሰቃዩዋቸው የነበሩት ሕመሞች የመነጩት ወይም ሥር ሰደው የተባባሱት ለረጅም ጊዜ ያለ ሕክምና በቆዩበት በዚህ ወህኒ ቤት ውስጥ ነበር። በከባድ ህመም ይሰቃዩ ከነበሩት መካከል ልዕልት ሒሩት ደስታ አንዷ ናቸው፡፡ እኒህ ልዕልት በእሥር ላይ እያሉ ከተከሰተባቸውና ከባድ ደረጃ የደረሰ የቆዳ ካንሰር የተነሳ ኦፕራሲዮን የተደረገላቸው ሲሆን በሕመሙ ሳቢያ የሰውነት ክብደታቸው በአደገኛ ሁኔታ አሽቆልቁሎ ነበር፡፡

ሌላዋ የእሥር ቤት ሕመም ሰለባ ደግሞ ልዕልት አይዳ ደስታ የነበሩ ሲሆን ሕመማቸው ደግሞ የማያቋርጥና ብርቱ ራስ ምታት ነበር፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የሰውነታቸው አንዱ ክፍል እዚያው ወሕኒ ቤት ውስጥ ፓራላይዝድ በመሆኑ ከቦታ ወደ ቦታ ለመንቀሳቀስ የሚችሉት በከፍተኛ ችግር ነበር፡፡ የልዑል መኮንን ባለቤት የነበሩት ልዕልት ሣራ ግዛው በበኩላቸው፤ በወሕኒ ቤት በለከፋቸው የሄፒታይተስ በሽታ ክፉኛ ታመው ለረጅም ጊዜ ተሰቃይተዋል፡፡

መሰረታዊ የሕክምና እጦት፣ ከዛሬ ነገ ልንገደል እንችላለን የሚል ብርቱ ስጋት እንዲሁም በውጪ እና እዚያው እሥር ቤት ካሉ ልጆቻቸውና ዘመዶቻቸው ጋር ለመገናኘት አለመቻል፣ ተደራርቦ እሥረኞቹን ለአስከፊ ስነልቡናዊ ስቃይ ዳርጓቸዋል። የደረሰባቸውን የመንፈስ ጭንቀት ለማስታገስም ቤተሰቦቻቸው እንቅልፍ እንዲያስወስድ የሚያደርጉ እና አእምሮን የሚያረጋጉ እንክብሎች እንዲያመጡላቸው በመጠየቅ፣ ያለ ሐኪም ፈቃድ ይወስዱ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል፡፡

እነዚህ እሥረኞች ያለ ፍርድ ወደ ወህኒ የተወረወሩ በመሆኑ ለፍርድ እንዲቀርቡ ወይም እንዲለቀቁ፤ እንዲሁም አያያዛቸውም የሕግ እሥረኞች በሚጠበቁበት አግባብ ሆኖ መሰረታዊ ሕክምና ሳይዘገይ እንዲሰጣቸው፤ በማለት አምነስቲ ኢንተርናሽናል ከታሰሩበት ጊዜ ጀምሮ ባለማቋረጥ የደርጉን መንግሥት ሲማፀን ቆይቷል፡፡

ይሁን እንጂ ሕክምናን ማዘግየት ወይም መከልከል እንደ መደበኛ ቅጣት ተቆጥሮ፣ እሥረኞቹ እስከ 1980 ዓ.ም ድረስ መሰረታዊ ሕክምናን ተነፍገው ቆይተዋል። ንጉሳዊ ቤተሰቡ ከእሥር እንዲለቀቅ ከዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችና የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ሳያቋርጥ ለደርጉ ይቀርብ የነበረው ተማፅኖ ፍሬ ማሳየት የጀመረው እሥረኞቹ ወደ ወህኒ ከተወረወሩ ከስምንት አመታት በኋላ ነበር፡፡


ከሆነ ጊዜ በኋላ እኮ ምንም ነን ፥
ምድር አታስታውሰንም ፤
ከብታቿ ቀብራ በተረኛ ታስረግጠናለች ። 😔


አንድ ፊደል መሆን ነበረባት!
ብቸኝነት እንዴት በጥንድ ፊደል
ይወከላል.


#ህልም-የትሪ እንጀራ

#አቅም-የጣባ ዱለት

አብቃቃለሁ ማለት
ዘበት።

red-8


በደለችኝ ብዬ ሲነደኝ ሲቆጨኝ

ልወግራት ፈልጌ
ጠጠር ብወረውር  አለት  ኾኖ ፈጨኝ
በቃጣሁት ልምጭ ጀርባዬ ታረሰ
ቱፍ ባልኩት ምራቅ ጎጆዬ ፈረሰ

አልገባኝም እንጂ ልክ ነው ነገሩስ....

ንጹህ ነኝ ለማለት የወረወሩት ክስ

  ዞሮ የመጣ እለት
  አያድርስ....አያድርስ....

🔘red 8🔘


#ሞልቶ_አደር

እኛ ሀበሻዎች
የቁጥር ቅኔዎች
እጥፍ አባባሎች
ድርብ ህብረ ቃሎች
ወርቃችን ድብቅ ነው ሰማችንም ሚስጥር
ተርፈን እናድራለን ባጎደሉን ቁጥር
ያንዣበበን ጭልፊት ራርቶልን ባያውቅም
እንደ ተዝካር ቀይ ወጥ ተጨልፈን አናልቅም

🔘በሙሉቀን🔘


#አምስቱ_የስሜት_ህዋሳት_ስንት_ናቸው?

.
እኔና እሷ ሳንፋቀር..
ስለ ስሜት ህዋሳቶች ፥ የምናውቀው አምስት ነገር
በአይናችን እናያለን
በእጃችን እንዳስሳለን
በምላሳችን እንቀምሳለን
በጆሯችን እንሰማለን
ባፍንጫችን እናሸታለን ፣ የሚል ነበር፡፡
።።።
እኔና እሷ ስንፋቀር..
ካንደበቷ ቃል ሳይወጣ ፣ በዝምታ ስትናገር
የከንፈሯን ንቅናቄ
እያየሁኝ የምሰማት ፣ ያለችኝን አንዳች ነገር.
አይን ማለት
በዚያ ሰአት ፥ መስሚያ ነበር፡፡
።።።
እኔና እሷ ስንጣላ
ስለጃችን ከተማርነው ፤ ከመዳሰስ ስሜት ሌላ
ሌላ ስሜት ተፈጥሮብኝ ፥ ያንደበቴን ቃል ሰስቼ
አነዳች ነገር ስናገራት ፤ የመሀል ጣቴን አውጥቼ
ስድብ መሆኑ ሲገባት
ምላሷን ስታወጣብኝ
ስላቅ መሆኑ ሚገባኝ
እጅ ማለት ሌላ ስሜት ፥ ምላስ ማለት ሌላ ነገር
መቅመስ መዳበስ ያልሆነ ፥ ያልተማርነው ነገር ነበር፡፡
ብቻ
ብቻ
እኔና እሷ ስንጣላ ፥ እኔና እሷ ስንፋቀር
ስለ ስሜት ህዋሳቶች ፥ ብንማርም አምስት ነገር
እኛ ኖረን ያሳለፍነው ፥ ቁጥር አልባ ስሜት ነበር፡፡

🔘በላይ በቀለ ወያ🔘


እግዜሄር የጨበጣቸው ''ሳያቅፈን'' ብለው ሲቆጡ

እግዚሄር ያቀፋቸው
እልፍኙ ገብተን ካልበላን- ብለው በኩርፊያ ሲመጡ

የግዚያብሄር እልፍኝ የገቡት

እንጀራ ሳይሰጠን ብለው-ቂም ዘግነው ይዘው ሲወጡ

ባይ ..ደነቀኝ....ባይ ገረመኝ..

ምናለ እኔን ላ'ንድዜ
ገላምጦኝ ደስታ ቢገድለኝ።

🔘red-8🔘


......የሚጠብቀን ባያንቀላፋም
ባለ ቁጥር መንቃት አይከፋም...

🔘red-8🔘


#እኔ
በፀጉሮችሽ መሐል እልፍ ፂም ባገኝም
የት ነበረች ብዬ ሳስብ አልገኝም

#እኔ
የሺ ወንድ ጠረን ብስብም ከአንገትሽ
እከራከራለሁ አይደለም ካንጀትሽ

#እኔ
በጡቶችሽ ጫፎች እያየሁ አሻራ
እጠርግልሻለሁ ቆጥሬ እንዳቧራ
ይልቅስ የእኔ
ስጋቴ
ፍርሃቴ
ያ ሁሉ ተባዕት እንዳያስጨንቁሽ
ያ ሁሉ ተባዕት ቀምሰው እንዳይርቁሽ
የሚያብሰከሰከኝ ሲስሙ እንዳያንቁሽ
(ነበር)

#እኔ
ሁሉን ደስታ አይተሽ
እንደፀሀይ ገላ ሙቀሽ
ስትጨርሺ
እንዳላይሽ አዝነሽ
እንዳንላይሽ ደርቀሽ
(ነበር)
እንጂ
ያዘንሽ ቀንም ከአጠገብሽ አለሁ
የደስታሽን ቀብር አብሬ እውላለሁ
ያንቺን የሀዘን ቀን እንደኔ ቆጥሬ
እንጀመር እላለሁ መውደድን ከዛሬ
ከዛሬ
ከአሁን
ከቅፅበት
ህይወት ስታበቃ እኛ እንጀምረበት
እላለሁ፡፡
እላለሁ
እንዳዲስ እንጀምር እንዳልተለመደው
ይሰፋል እላለሁ የተቀዳደደው
ይፀናል እላለሁ የተንገዳገደው
እላለሁ፡፡
እንደማቱሳላ
አኑረኝ
ቀኔን ሳላሰላ
አክርመኝ፡፡
ላቧን እስክትጨርስ
በወንድ እንክትርስ
ዓይኗ እስከሚሟሟ
እስከሚደባለቅ እውንና ህልሟ
አኑረኝ እላለሁ
አክረመኝ እላለሁ
እድሜ ስጠኝ ብዬ እለማመናለሁ
ለምን
ሁሉም የጣለሽ ቀን እኔ አነሳሻለሁ፡፡
(እስከዛ ግን አለሁ)

🔘ኤልያስ ሽታኹን🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose


#የባርነት_አዚም

ኑ ባንዲራ እንሰቀል አንድ ላይ እናዚም፡፡
ኑ  ሰነደቅ እንስቀል
በሰው ስም ይነገድ በሰው ስም ይሸቀል፡፡

ቁስልን በማከክ ባይሽርም ህመሙ
ሀበሻን ግን ስሚው
ጥፍርን ሲለምን ለቁስል ለደሙ፡፡
"እከክ የሰጠ አምላክ
ጥፍርን ደግሞ ይላክ::"
እያለ የሚኖር
ብሂል ነው ሀበሻ ያውም ቃል አጋኖ
ሞኝ ሆኖ  አየደለም
ኑሮ ሆነበት ነው መቁሰል ደምቡ ሆኖ፡፡
መቁሰል የለመደ የሀበሻ ገላ
ጥፍር ይለምናል ማከክ ላይሆን መላ::
ግን ምን ታደርጊዋለሽ?
ደዌ ነፍስ
ደዌ ስጋ
ደዌ መንፈስ
ተጣብቆት ሰንብቶ
ባይሽርም በኮሶ ባይሽርም ባረቄው
መቁስል ስለማይቆሞ ጥፍር ነው ጥያቄው፡፡
ጥፍር
ጥፍር
(ጠብቆም ይነበብልኝ)
ጥፍር
እስር
እስርስር
ጥፍርፍር::
ጥፍር
ለእከክ የጠየቅነው ደግሞ ሲወጣልን
የፀብ አምሮታችን ይኸው ተነሳልን
ጥፍር
ጥፍር
ጥፍር
አንድም ለቁስላችን
አንድም ለፀባችን፡፡
ሀበሻ ብልጥ ነው የመቁሰል ዘመኑ ስለማያበቃ
የሰርክ  ልመናው ጥፍር ሆነ በቃ፡፡
  
🔘ኤልያስ ሽታኹን🔘


#ሀና_እና_እያቄም

ልጅ ቢሰጠን ብለው ቢያስገቡ ስለትን፣ እግዚአብሔር ሰጣቸው የእግዚአብሔር እናትን።

ሚካኤል ፣ ገብርኤል ፣ ዑራኤል …)

ስላሴ መንበር ፊት
ሰርክ የሚላላኩት፣
ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ብለው የሚያመልኩት።

(አምላክ ሰው)

እንደሚሆን ያኔ ትንቢቱን የሚያምኑ፣ ማርያም ስትወለድ እርግጠኛ ሆኑ።

ከአምላክ የራቁት፣
መዳን የናፈቁት፣
ከገነት ቤታቸው የወጡት በራቁት።

( አዳም እና ሄዋን )

ስትወለድ ቢያዩ ድንግል ከሊባኖስ፣
ከሲኦል ታያቸው የድህነት ፋኖስ።


#ፀሎተ_ግንቦት

ለተቀረው አመት...ደግሞም እስካመቱ
አንድ ሲል ልደታ...ዘጠኝ ሲል ወራቱ
ቅዬው ሲሰበሰብ ...
ላድባር የሚጀ'በት ፥ ሸክፎ ከቤቱ
ዛሬ ያልጠገብ ፥  አይኑና ፣ አንጀቱ
በማጣት ይታሻል...ጓዳና ፣ ማጀቱ
እንዲለን ልማዱ...
ጋን..እጋን ሲጋባ...መብሉ ሲመሰኳ
ማቲ ሲተራመስ ...ጨዋታው ሲውኳኳ
ቡኑ ሲከታትም ...ጢሱ ሲትጎለጎል
አጥንት ፣ ጉልጥምቱ ...ከሳቱ ሲታጎል
እንኳንስ ያዳም ከርስ...ያሞራው ሲረካ
ይህን የለመደ ...
ለላመት ድረሱ ፥ ብሎ ይመርቃል ፥ ሆድና መለይካ።
ልማድ መጥፎ ህመም ...
ሲነጠሉ ግዜ ..  ትዝታው በሽታ
የቀረ ለት ያማል...
ቀን በቀኑ ሲደርስ ...ክርሚያው በሽውታ
የሰው ልደት እንኳ ፥ ሲኮስስ ይከፋል ፥ እንኳን #ያዛኝቷ
እናም .... #እመቤቴ
ልማድሽ እንዳይቀር... #እመብርሀኒቱ
በለትሽ ምህላ ፥ እንዲሽር ፍጥረቱ
እንዳምና እንድንውል ፥ ለቀጣይ ለፊቱ
ጠርገሽ ወድያ ይጣል ...ነቀርሳ ልክፍቱ ።          

   🔘አብርሀም_ተክሉ🔘


የጨነቀው ሁሉ
"ማርያም ማርያም" ይላል ምጥም እንዳያቄም
በማን ስም ወለዱሽ ሀናና ኢያቄም?

~     ~     ~     ~       ~     ~

ቤት የለውምና
አዳም ወጥቶ ቀርቶ ከፈጣሪ ደጁ
ምንድነው ሚስጥሩ?
ቤት አትልተወለዱም እናትና ልጁ።


መስዋዕቱ ቀረ ርግብና ዋኖስ
ልጇን ልትሰጥ ነው እናት ከሊባኖስ።

የሊባኖስ ዝግባ ንፋስ የማይገፋው
ማርያም ስትወለድ እግዜር ዙፋን ሰፋው።


እመብዙሃኗ
የሄኖክ የራስ ወርቅ ኢሳይያስ ትንቢቱ
የዳዊት የልጅ ልጅ  የኖኅ መርከቢቱ።


ምስጢሩ ነችና  ሰምና ወርቅ ቃል
ቀራንዮን ያየ ሊባኖስን ያውቃል።


የጨነቀው ሁሉ
"ማርያም ማርያም" ይላል ምጥም እንዳያቄም
በማን ስም ወለዱሽ ሀናና ኢያቄም?

🔘ኤልያስ ሽታኹን🔘


አንቺን እንዲሰጠኝ ሆንኩኝ አምላክ ለማኝ
ጧፍ መባ ገዛሁ ልሰጠው ከሰማኝ፡፡
አንቺዬ
ፀሎቴን ሳልጨርስ ብትይ እመጣለሁ
እኔ እኮ ሞኝ ነኝ
ፈጣሪዬን ትቼ እጠብቅሻለሁ፡፡
እጠብቅሻለሁ
በተገተርኩበት
እጠብቅሻለሁ
በተፈጠረኩበት፡፡
ጊዜ አይፈራረቅ አይጮኹም አእዋፍ
አንቺን ስጠብቅሽ
ለኮስኩት ጨክኜ ለስለት እንዲሆን የገዛሁት ጧፍ፡፡
ትመጫለሽ አይደል?


🔘ኤልያስ ሽታኹን🔘


#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose


ኢትዮጵያ በራሷ ገዳይ ነገር አላት እንዴ?
ድንቄም ትርጓሜ
ቅኔና ዝማሜ
ድንቄም ሶላት አዛን
ሁሌ መለካካት ሁል ጊዜ ሚዛን፡፡
ድንቄም ሀዘን  ዕንባ
ሞትን ሰው ካረባ፡፡፡
አይ ቀስተደመና
ምደረ መና፡፡
ድንቄም ገዳም
እየተናከሰ አደምና አዳም፡፡
ድንቄም ገዳ
እንደወይን ግብዣ ደም እየተቀዳ፡፡
ድንቄም አክሱም አወይ ላሊበላ
እንደቅርጫ ስጋ ሰው እየተባላ፡፡
አይ አይ
ዋይ ዋይ፡፡
አይ እድገት
አይ ሰላም
በሰማይ አለኝ ላም፡፡
አወየው ሶፍ ዑመር
ሞት በሰው ቢከመር፡፡
አወይ አልነጃሺ
ስንቱን ተቀብሎ ዛሬ እሱ ቢሸሽ፡፡
(አናሳዝንም)
አይ ሸገር ፊነፊኔ
ለወያኔም ወይኔ
ለ..... ወይኔ፡፡
የዘሬ ያንዘርዝረኝ እንደተባባለነው
ይኸው....
ህይወት ድፍን ሲሆን በሞት ዘረዘርነው፡፡
ደሞ አለን በለኝ ተስፋና ዕድሉ
ታሪክና ባህል
ሲቆም አያምርበት ሰው እየገደሉ፡፡
አናሳዝንም???

🔘ኤልያስ ሽታኹን🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose

Показано 20 последних публикаций.