Christian tweet


Гео и язык канала: Эфиопия, Английский
Категория: Telegram


በዚህ ቻናል በየቀኑ ለ
➜ #Profile_picture
➜ #Instagram_story
➜ #Facebook
➜ #Telegram_story
የሚሆኑ #መንፈሳዊ_ጥቅሶች እና #መፅሐፍ_ቅዱሳዊ መልእክቶችን (በአማርኛ እና ENGLISH) ወደእናንተ እናደርሳለን ቻናሉን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ 😊
ⒸSince 5-11-2015
Buy ads: https://telega.io/c/christian_tweet

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Английский
Категория
Telegram
Статистика
Фильтр публикаций


.     “He is not here: for he is risen,
as he said. Come, see the place
where the Lord lay.”
— Matthew 28፥6 (KJV)
             ✨ HAPPY EASTER ✨
               ▷@Christian_tweet


ሉቃስ 24
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁴ እነርሱም በዚህ ሲያመነቱ፥ እነሆ፥ ሁለት ሰዎች የሚያንጸባርቅ ልብስ ለብሰው ወደ እነርሱ ቀረቡ፤
⁵ ፈርተውም ፊታቸውን ወደ ምድር አቀርቅረው ሳሉ፥ እንዲህ አሉአቸው፦ ሕያውን ከሙታን መካከል ስለ ምን ትፈልጋላችሁ? ተነሥቶአል እንጂ በዚህ የለም።
⁶-⁷ የሰው ልጅ በኃጢአተኞች እጅ አልፎ ሊሰጥና ሊሰቀል በሦስተኛውም ቀን ሊነሣ ግድ ነው እያለ ገና በገሊላ ሳለ ለእናንተ እንደ ተናገረ አስቡ።


Luke 24 (KJV)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁴ And it came to pass, as they were much perplexed thereabout, behold, two men stood by them in shining garments:
⁵ And as they were afraid, and bowed down their faces to the earth, they said unto them, Why seek ye the living among the dead?
⁶ He is not here, but is risen: remember how he spake unto you when he was yet in Galilee,
⁷ Saying, The Son of man must be delivered into the hands of sinful men, and be crucified, and the third day rise again.

@Christian_tweet
@Christian_tweet


ሉቃስ 5
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁶ ደግሞም ምሳሌ እንዲህ ሲል ነገራቸው፦ የአዲስ ልብስ እራፊ ባረጀ ልብስ ላይ የሚያኖር የለም፤ ቢደረግ ግን አዲሱን ይቀደዋል ደግሞም አዲስ እራፊ ለአሮጌው አይስማማውም።
³⁷ ባረጀ አቁማዳም አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር የለም፤ ቢደረግ ግን አዲሱ የወይን ጠጅ አቁማዳውን ያፈነዳል፥ እርሱም ይፈሳል አቁማዳውም ይጠፋል።
³⁸ አዲሱን የወይን ጠጅ ግን በአዲስ አቁማዳ ማኖር ይገባል፥ ሁለቱም ይጠባበቃሉ።
³⁹ አሮጌ የወይን ጠጅ ሲጠጣ አዲሱን የሚሻ ማንም የለም፤ አሮጌው ይጣፍጣል ይላልና።

Luke 5 (KJV)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁶ And he spake also a parable unto them; No man putteth a piece of a new garment upon an old; if otherwise, then both the new maketh a rent, and the piece that was taken out of the new agreeth not with the old.
³⁷ And no man putteth new wine into old bottles; else the new wine will burst the bottles, and be spilled, and the bottles shall perish.
³⁸ But new wine must be put into new bottles; and both are preserved.
³⁹ No man also having drunk old wine straightway desireth new: for he saith, The old is better.

@Christian_tweet
@Christian_tweet


#የእርዳታ_ጥሪ

ቀና ልብ ላላችሁ ወገኖች በሙሉ  የወንድማችንን ነፍስ ከሞት እንታደግ🙏

ይህ ከላይ በምስሉ ላይ የምትመለከቱት ወጣት ኤርምያስ ፍቅሬ ይባላል።

   ተወልዶ ያደገዉም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣በሀድያ ዞን፣በፎንቆ ከተማ ስሆን፤ #ከልጅነቱም ጀምሮ ትሁትበስነ-ምግባሩ የታነፀበትምህርቱም ጎበዝና ለሌሎችም እንደ አራአያ የምታይ ወጣት ነዉ።

   የ2ተኛ ደረጃ ትምህርቱን በከፍተኛ ውጤት አጠናቆ በ2009ዓ.ም ወደ #ሀዋሳ_ዩንቨርስቲ በመግባት በቴክስታይል ኢንጅነርንግ(Textile Engineering) ት/ት ክፍል ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ ተመርቆ #በሀዋሳ እንደስትርያል ፓርክ ውስጥ እየሰራ ባለበት ወቅት ድንገት ባጋጠመዉ የኩላሊት ህመም ምክንያት ስራውን አቋርጦ ህክምናዉን እየተከታተለ እያለ ህመሙ ብሶበት ሁለቱም ኩላሊቶቹ መስራት ስላቁመ ዶክተሮቹ በአፋጣኝ ወደ ውጭ ሀገር ሄዶ የኩላሊት ንቅለ ተከላ እንዲደረግ ወስነዋል።

እናም ወደ ውጭ ሀገር ወስደን ለማሳከም የተጠየቅነዉ ብር ከአቅማችን በላይ በመሆኑ እናንተ በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭም የምትኖሩ ደጋግ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን እጃችሁን በመዘርጋት ወይም በምትችሉት ነገር ሁሉ ከጎናችን በመሆን ይህንን ወጣት ህይወት እንድትታደጉ ስንል እንማፀናለን🙏።

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ:-1000268155938
በአዋሽ ባንክ:- 013201523182800
ERMIAS FIKRE MESSELE

ለመደወልና ኤርምያስን ለማናገር ለምትፈልጉ
📞 0941414057
📞0920992184 ወይም
📞0939580869

የተቻላችሁን ብትረዱንና የወንድማችንን ህይወት በማትረፍ ትተባበሩን ዘንድ በአክብሮት እንጠይቃለን🙏

ለምታደርጉልን ማንኛውም ቀና ትብብር እናመሰግናለን ፈጣሪ ጨምሮ ይስጥልን።

🙏ቻሌንጃችንን ለመቀላቀል👇

@Go_Fund1


“እግሮች እንዳይናወጡ አረማመዴን በመንገድህ አጽና።”
— መዝሙር 17፥5

“Hold up my goings in thy paths, that my footsteps slip not.”
— Psalms 17:5 (KJV)

@Christian_tweet
@Christian_tweet


ምሳሌ 5
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ልጄ ሆይ፥ ወደ ጥበቤ አድምጥ፤ ጆሮህን ወደ ትምህርቴ መልስ፥
² ጥንቃቄን ትጠብቅ ዘንድ ከንፈሮችህም እውቀትን እንዲጠብቁ።


Proverbs 5 (KJV)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ My son, attend unto my wisdom, and bow thine ear to my understanding:
² That thou mayest regard discretion, and that thy lips may keep knowledge.

@Christian_tweet
@Christian_tweet


'ዕብራውያን 9:25 - ሊቀ ካህናት የራሱ ያልሆነውን ደም ይዞ በየዓመቱ ወደ ቅድስተ ቅዱሳን እንደሚገባ፣ ክርስቶስ ራሱን ብዙ ጊዜ መሥዋዕት ለማድረግ ወደ ሰማይ አልገባም።'


“ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፦ የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ፤ ወደ እኔ የሚመጣ ከቶ አይራብም በእኔ የሚያምንም ሁልጊዜ ከቶ አይጠማም።”
— ዮሐንስ 6፥35


“And Jesus said unto them, I am the bread of life: he that cometh to me shall never hunger; and he that believeth on me shall never thirst.”
— John 6:35 (KJV)

@Christian_tweet
@Christian_tweet


መዝሙር 1
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ምስጉን ነው በክፉዎች ምክር ያልሄደ፥ በኃጢአተኞችም መንገድ ያልቆመ፥ በዋዘኞችም ወንበር ያልተቀመጠ።
² ነገር ግን በእግዚአብሔር ሕግ ደስ ይለዋል፥ ሕጉንም በቀንና በሌሊት ያስባል።
³ እርሱም በውኃ ፈሳሾች ዳር እንደ ተተከለች፥ ፍሬዋን በየጊዜዋ እንደምትሰጥ፥ ቅጠልዋም እንደማይረግፍ ዛፍ ይሆናል፤ የሚሠራውም ሁሉ ይከናወንለታል።
⁴ ክፉዎች እንዲህ አይደሉም፥ ነገር ግን ነፋስ ጠርጎ እንደሚወስደው ትቢያ ናቸው።
⁵ ስለዚህ ክፉዎች በፍርድ፥ ኃጢአተኞችም በጻድቃን ማኅበር አይቆሙም።
⁶ እግዚአብሔር የጻድቃንን መንገድ ያውቃልና፥ የክፉዎች መንገድ ግን ትጠፋለች።


Psalms 1 (KJV)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ Blessed is the man that walketh not in the counsel of the ungodly, nor standeth in the way of sinners, nor sitteth in the seat of the scornful.
² But his delight is in the law of the LORD; and in his law doth he meditate day and night.
³ And he shall be like a tree planted by the rivers of water, that bringeth forth his fruit in his season; his leaf also shall not wither; and whatsoever he doeth shall prosper.
⁴ The ungodly are not so: but are like the chaff which the wind driveth away.
⁵ Therefore the ungodly shall not stand in the judgment, nor sinners in the congregation of the righteous.
⁶ For the LORD knoweth the way of the righteous: but the way of the ungodly shall perish.

@Christian_tweet
@Christian_tweet


“የሠራዊት አምላክ ሆይ፥ ማደሪያዎችህ እንደምን የተወደዱ ናቸው!”
— መዝሙር 84፥1

“(To the chief Musician upon Gittith, A Psalm for the sons of Korah.) How amiable are thy tabernacles, O LORD of hosts!”
— Psalms 84:1 (KJV)

@Christian_tweet
@Christian_tweet


ኢየሱስ....ኢየሱስ....ኢየሱስ... ኢየሱስ...ኢየሱስ ኢየሱስ ኢየሱስ ኢየሱስ ኢየሱስ

Yidnekachew Teka

@Christian_tweet
@Christian_tweet


“እግዚአብሔርን በመተማመን የሚጠባበቁ ግን ኃይላቸውን ያድሳሉ፤ እንደ ንስር በክንፍ ይወጣሉ፤ ይሮጣሉ፥ አይታክቱም፤ ይሄዳሉ፥ አይደክሙም።”
— ኢሳይያስ 40፥31

“But they that wait upon the LORD shall renew their strength; they shall mount up with wings as eagles; they shall run, and not be weary; and they shall walk, and not faint.”
— Isaiah 40:31 (KJV)

@Christian_tweet
@Christian_tweet


ይሰማ በዓለም እምነቴ ኢየሱስ ነው።✝

Amen

@Christian_tweet
@Christian_tweet


የከበረ ከሁሉ የተሻለ
የከበረ ከሁሉ የተሻለ
ሰውነቴ ለአንተ አቀርባለሁ (2x)
እኔነቴን ለአንተ አቀርባለሁ (2x)

መሰዊያን ሰራሁ ልሰዋልህ በፊትህ ላቀርበው
ያለኝን በሙሉ ታውቀዋለህ የቱን ነው ምትሻው
እያልኩኝ ስደረድር ምድርና ሞላዋ ለካስ የአንተ ነው
የሚቃጠል መስዋዕት ደስ እንዳያሰኝህ ይህንን ተረዳሁ

ታዲያ እኔም ምኔን ልስጥህ
ምን ሰጥቼ/ሰውቼ ደስ ላሰኝህ
እያልኩኝ ስጠይቅ ቃልህን
ስጠው/ሰዋው አለኝ እራስህን (2x)

@Christian_tweet
@Christian_tweet


ሕዝቅኤል 16
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁵ ስለዚህ፥ ጋለሞታ ሆይ፥ የእግዚአብሔርን ቃል ስሚ።
³⁶ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ከውሽሞችሽ ጋር ባደረግሽው በግልሙትናሽ ርኵሰትሽ ስለ ፈሰሰ ኀፍረተ ሥጋሽም ስለ ተገለጠ፥ ስለ ርኵሰትሽም ጣዖታት ሁሉ ስለ ሰጠሻቸውም ስለ ልጆች ደም፥
³⁷ ስለዚህ፥ እነሆ፥ ከእነርሱ ጋር ደስ ያለሽን የወደድሻቸውንም ውሽሞችሽ ሁሉ ከጠላሻቸው ሁሉ ጋር እሰበስባቸዋለሁ፤ በአንቺ ላይ በዙሪያሽ እሰበስባቸዋለሁ፥ ኀፍረተ ሥጋሽንም ሁሉ እንዲያዩ በፊታቸው ኀፍረተ ሥጋሽን እገልጣለሁ።
³⁸ በአመንዝሮችና በደም አፍሳሾች ላይ የሚፈረደውን ፍርድ እፈርድብሻለሁ፥ የመዓትንና የቅንዓትን ደምም አመጣብሻለሁ።
³⁹ በእጃቸውም አሳልፌ እሰጥሻለሁ፥ የምንዝርናሽንም ስፍራ ያፈርሳሉ ከፍ ያለውንም ቦታሽን ይገለብጣሉ፤ ልብስሽንም ይገፉሻል የክብርሽንም ጌጥ ይወስዳሉ፥ ዕርቃንሽን አድርገው ዕራቁትሽን ይተዉሻል።

@Christian_tweet
@Christian_tweet


በአንተ የተጠራ ወገን
በአንተ የተወደደ
ከጥፋት ባህር ንዳድ በስምህ የተጋረደ
ክብሩ ኢየሱስ የሆንክለት መጠሪያ የዘውድ ስሙ
በኪዳንህ የሚራመድ በደምህ የገባህ ከደሙ
በክብርህ እሳት የሚነድ በህልውናህ ዓለም
በእረፍት ጠል የረሰረሰ ከህዝብህ በቀር የለም

የለም ከእኛ በቀር የለም
የለም ከህዝብህ በቀር የለም
የታደልን ህዝብ በአንተ ታየን
ተመረጥን ተወደድን
መስዋዕት በሆንክ በተነሳህ ከሞት ከሞት አመለጥን
ክብራችን ነህ ሞገሳችን
ብንዘምርልህ ብንዘምር የማይደክመን
ለሰማዩም ለምድሩም መጠጊያ
የታመንብህ ጽኑ መጠለያ
ክብራችን ነህ ሞገሳችን
ብንዘምርልህ ብንተርክህ የማይደክመን
ለሰማዩም ለምድሩም መጠጊያ
የታመንብህ ጽኑ መጠለያ
እናመልክሃለን (×፭)


ሐዋርያት 4
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁰ እናንተ በሰቀላችሁት እግዚአብሔርም ከሙታን ባስነሣው በናዝሬቱ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይህ ደኅና ሆኖ በፊታችሁ እንደ ቆመ፥ ለእናንተ ለሁላችሁ ለእስራኤልም ሕዝብ ሁሉ የታወቀ ይሁን።
¹¹ እናንተ ግንበኞች የናቃችሁት፥ የማዕዘን ራስ የሆነው ይህ ድንጋይ ነው።
¹² መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና።


Acts 4 (KJV)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁰ Be it known unto you all, and to all the people of Israel, that by the name of Jesus Christ of Nazareth, whom ye crucified, whom God raised from the dead, even by him doth this man stand here before you whole.
¹¹ This is the stone which was set at nought of you builders, which is become the head of the corner.
¹² Neither is there salvation in any other: for there is none other name under heaven given among men, whereby we must be saved.

@Christian_tweet
@Christian_tweet


ሮሜ 4
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ እንግዲህ በሥጋ አባታችን የሆነ አብርሃም ምን አገኘ እንላለን?
² አብርሃም በሥራ ጸድቆ ቢሆን የሚመካበት አለውና፥ ነገር ግን በእግዚአብሔር ዘንድ አይደለም።
³ መጽሐፍስ ምን አለ? አብርሃምም እግዚአብሔርን አመነ ጽድቅም ሆኖ ተቈጠረለት።
⁴ ለሚሠራ ደመወዝ እንደ ዕዳ ነው እንጂ እንደ ጸጋ አይቈጠርለትም፤
⁵ ነገር ግን ለማይሠራ፥ ኃጢአተኛውንም በሚያጸድቅ ለሚያምን ሰው እምነቱ ጽድቅ ሆኖ ይቆጠርለታል።

Romans 4 (KJV)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ What shall we say then that Abraham our father, as pertaining to the flesh, hath found?
² For if Abraham were justified by works, he hath whereof to glory; but not before God.
³ For what saith the scripture? Abraham believed God, and it was counted unto him for righteousness.
⁴ Now to him that worketh is the reward not reckoned of grace, but of debt.
⁵ But to him that worketh not, but believeth on him that justifieth the ungodly, his faith is counted for righteousness.


@Christian_tweet
@Christian_tweet


ኃጥያተኛ ነበርኩ ዓለም ጉድ ያለልኝ
ለሰራሁት በደል ሞት የፈረዱብኝ
ገበናዬን ገልጠው እየገፈተሩኝ
ለፍርድ አቀረቡኝ በድንጋይ ሊወግሩኝ

ዳኛው ግን ስለ እኔ በእውነት አዘነልኝ
ውስጡን እያወቀ ለእኔ ፈረደልኝ
ከከሳሾቼ እጅ በጥበብ አስጥሎኝ
በእኔ ፋንታ እርሱ ሞቶ ከፈለልኝ

አዝ:- በምህረቱ ዛሬ ቆሜያለሁ
ስለ እኔ ሞቶ እኔ ድኛለሁ
ነፍሴን ከሚሹ ከከሳሾቼ
ማምለጥ ችያለሁ ምህረት አግኝቼ

ኣሜን


“የጠገበች ነፍስ የማር ወላላ ትረግጣለች፤ ለተራበች ነፍስ ግን የመረረ ነገር ሁሉ ይጣፍጣታል።”
— ምሳሌ 27፥7


“The full soul loatheth an honeycomb; but to the hungry soul every bitter thing is sweet.”
— Proverbs 27፥7 (KJV)

@Christian_tweet
@Christian_tweet

Показано 20 последних публикаций.