የመግባቢያ ሰነድ ተፈረመንብ ኢንተርናሽናል ባንክ ከሁለት መንግሥታዊ ካልሆኑ፣ ከፊኒሽ ሪፍዩጅ ካውንስል እና ኦርጋናይዜሽን ፎር ሶሻል ሰርቪስስ ሔልዝ ኤንድ ዴቨሎፕመንት ከተባሉ ድርጅቶች ጋር አብሮ ለመሥራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ሰነድ በዛሬው ዕለት በባንኩ ዋና መሥሪያ ቤት ተፈራርሟል፡፡
ፊኒሽ ሪፍዩጅ ካውንስል ከስደተኞች ጋር በተያያዘ በአዲስ አበባ፣ በጋምቤላና በአማራ ክልል እንደሚሠራ ተመላክቷል፡፡
በተመሳሳይ ዜና፣ ኦርጋናይዜሽን ፎር ሶሻል ሰርቪስስ ሔልዝ ኤንድ ዴቨሎፕመንት የተባለው ደግሞ በአዲስ አበባ፣ ባሕር ዳር፣ ደሴ፣ ድሬዳዋ፣ ጋምቤላ፣ ጎንደር፣ ሐዋሣ፣ ሆሳዕና፣ ጂማ፣ ነቀምትና ትግራይ በጤና ላይ ትኩረት አድርጎ እንደሚሚሠራ በስምምነት ፊርማ ሥነ ሥርአቱ ላይ ተገልጿል፡፡
#Nib #Nibbank #bank #Banksinethiopia #FinnishRefugeeCouncil #OSSHD #OrganizationforSocialServicesHealthandDevelopment #Partnership #MoUAgreement #Banking
Facebook / Instagram / linkedin / X / Youtube / Tiktok / Website