ጥሩ ጓደኛ ካለህ በተኛህበት አላህ ሊምርህ ይችላል!
▪️ قال كعب الأحبار رحمه الله تعالى፡-【«رُب قائم مشكورٌ له، ورب نائم مغفور له؛ وذلك أن الرجلين يتحابان في الله، فقام أحدهما يصلي؛ فـ رضي الله صلاته ودعاءه، فلم يرد عليه مِن دعائه شيئًا، فذكر أخاه في دعائه من الليل، فقال:يا ربّ أخي فلان اغفر له؛ فغفر الله له وهو نائم】
ከዕብ አል-አሕባር አላህ ይዘንለትና እንዲህ ብሏል፥
«አንደኛው በሰራው የሚመሰገንና ሌላኛው ደሞ በተኛበት ወንጀሉ የሚማርለት አለ።
ይህም የሚሆነው ሁለት ለአላህ ብለው በጣም የሚዋደዱ ጓደኛሞች ነበሩ። አንደኛው ሌሊት ሊሰግድ ቆመ። አላህም ሶላቱና ዱዓውን ወደደለት። ከዱዓውም ምንም ነገር ሳይመልስ አላህ ተቀበለው። በዚህ በሚሰግድ ጊዜ ዱዓእ ሲያደርግ የተኛውን ወንድሙን አረሳውም ዱዓእ አደረገለት። "ጌታዬ ሆይ! እገሌ የሚባለው ወንድሜን ወንጀሉን ማረው!" አለ። በዚህ ወንድሙ ዱዓእ አማካኝነት በተኛበት አላህ ወንጀሉን ማረው።»
📚[ حلية الأولياء (٦ /٣١)]
@ya_muhammad_saw