ከአንድ ሳምንት በፊት ደውላ እንደደበራትና ከቻልኩ እንዳገኛት ጠይቃኝ ነበር!....እኔም በሰዓቱ “ውይ አንቺና ድብርት ግን ስትዋደዱ!... ወይ ለምን ተጋብታችሁ አብራችሁ አትኖሩም እ'? ብዬ ቀለድሁባት
...እሷም “ ሰርግ ደግሰን እወቁልን አላልንም እንጂ ከተጋባንማ ቆየን እኮ"አለችኝ...ያው ሁሌ ስለምንቀላለድ ንግግሯን ከ ቁም ነገር ሳልቆጥረው ሰሙኑን እንደማገኛት ነግሪያት ስልኩን ዘጋሁት!
ከሁለት ቀን በኋላ ደግማ ደወለችልኝ...ጫጫታ ቦታ ነበርኩ!...ስልኬ ሶስት ግዜ እንደ ጠራ አነሳሁትና “ቤቲዬ ጫጫታ ቦታ ላይ ነኝ ያለሁት አይሰማኝም መልሼ ልደውልልሽ!?...አልኳት!
"እዮብ በጣም ከፍቶኛል ምትችል ከሆነ አሁን ቤት ና በናትህ..አለችኝ
ያለሁበት ቦታ ጫጫታ ብዙም እያሰማኝ ስላልነበር “ቆይ ቤቲዬ ከ 5 ደቂቃ በኋላ ደውልልሻለሁ እሺ' ብዬ ስልኩን ዘጋሁት!....ቀኔ አድካሚ ስለነበር መደወሉን ረስቼ ቤቴ እንደገባሁ እራቴን እንኳ ሳልበላ ተኛሁ!...ጠዋት ተነስቼ ስልኬን ሳየው ቴክስት ገብቶልኛል... ቤቲ ነበር የላከችው!..ሰዓቱን አየሁት!... ትናንት ምሽት ሁለት ሰዓት
ነው የተላከው….. “ቻው እሺ እዮብዬ የማልደበርበት ቦታ ሄጃለሁ" ይላል!...ምን ለማለት ፈልጋ ነው? ግራ ገባኝ...ስልኳ ላይ ደወልኩ አይነሳም!...ደጋግሜ ሞከርኩ መልስ የለም!...ጫማዬን አደረኩና የቤቴን በር እንኳ ሳልቆልፍ በፍጥነት ወጣሁ!
የነ ቤቲ በር ላይ ስደርስ ድንኳን ተጥሏል! ልቤ ለሁለት ሲሰነጠቅ ተሰማኝ!...እግሬ እየተንቀጠቀጠ ወደ ውስጥ ገባሁ!...እናትየው የቤቲን ፎቶና የሆነ ወረቀት በእጃቸው ይዘው ግራና ቀኝ በሁለት ሰዎች ተይዘው እያቃሰቱ ቁጭ ብለዋል! ...ሰማይ ምድሩ ተደበላለቀብኝ!...የግዴን “ም… ምንድነው ማዘር'' ብየ ጠየኳቸው!...ምንም መልስ አልሰጡኝም!...ከ ጎን ያለችው ልጅ እምባ በተናነቀው ድምፅ! ልጃቸው አርፋለች አለችኝ!....''ማ ..ቤቲ?'' አልኳት...''አዎ'' አለችኝ!....''እራሷን ከ ማጥፋቷ በፊት ይሄን ወረቀት ፅፋ ነበር'' ብላ ከ እናትየው እጅ ላይ ወረቀቱን ወስዳ ሰጠችኝ!...እጄ እየተንቀጠቀጠ ተቀበልኳትና አየሁት ....''አይዞሽ የሚለኝ ሰው ብቻ ነበር የፈለኩት ....'' ይላል! ምንም አላልኩም.... ወረቀቱን እንደያዝኩ እግሬን እየጎተትኩ ከድንኳኑ ወጣሁ!...በእርግጥ ወዴት እንደምሄድ አላውቅም!
! ይሄ ፅሁፍ የሚያስተምረን በሂወታችን ችላ የምንለው ነገር እስከ ሂወት ማጣት ድረስ ዋጋ እንደሚያስከፍለን ነው
::አንበበው ከወደደት👍👍 ተጭናችሁ እለፉ
✍እንማር
ይ 🀄️ላ🀄️ሉን! 😀
💔 https://t.me/yefikirtelegramet 💔
...እሷም “ ሰርግ ደግሰን እወቁልን አላልንም እንጂ ከተጋባንማ ቆየን እኮ"አለችኝ...ያው ሁሌ ስለምንቀላለድ ንግግሯን ከ ቁም ነገር ሳልቆጥረው ሰሙኑን እንደማገኛት ነግሪያት ስልኩን ዘጋሁት!
ከሁለት ቀን በኋላ ደግማ ደወለችልኝ...ጫጫታ ቦታ ነበርኩ!...ስልኬ ሶስት ግዜ እንደ ጠራ አነሳሁትና “ቤቲዬ ጫጫታ ቦታ ላይ ነኝ ያለሁት አይሰማኝም መልሼ ልደውልልሽ!?...አልኳት!
"እዮብ በጣም ከፍቶኛል ምትችል ከሆነ አሁን ቤት ና በናትህ..አለችኝ
ያለሁበት ቦታ ጫጫታ ብዙም እያሰማኝ ስላልነበር “ቆይ ቤቲዬ ከ 5 ደቂቃ በኋላ ደውልልሻለሁ እሺ' ብዬ ስልኩን ዘጋሁት!....ቀኔ አድካሚ ስለነበር መደወሉን ረስቼ ቤቴ እንደገባሁ እራቴን እንኳ ሳልበላ ተኛሁ!...ጠዋት ተነስቼ ስልኬን ሳየው ቴክስት ገብቶልኛል... ቤቲ ነበር የላከችው!..ሰዓቱን አየሁት!... ትናንት ምሽት ሁለት ሰዓት
ነው የተላከው….. “ቻው እሺ እዮብዬ የማልደበርበት ቦታ ሄጃለሁ" ይላል!...ምን ለማለት ፈልጋ ነው? ግራ ገባኝ...ስልኳ ላይ ደወልኩ አይነሳም!...ደጋግሜ ሞከርኩ መልስ የለም!...ጫማዬን አደረኩና የቤቴን በር እንኳ ሳልቆልፍ በፍጥነት ወጣሁ!
የነ ቤቲ በር ላይ ስደርስ ድንኳን ተጥሏል! ልቤ ለሁለት ሲሰነጠቅ ተሰማኝ!...እግሬ እየተንቀጠቀጠ ወደ ውስጥ ገባሁ!...እናትየው የቤቲን ፎቶና የሆነ ወረቀት በእጃቸው ይዘው ግራና ቀኝ በሁለት ሰዎች ተይዘው እያቃሰቱ ቁጭ ብለዋል! ...ሰማይ ምድሩ ተደበላለቀብኝ!...የግዴን “ም… ምንድነው ማዘር'' ብየ ጠየኳቸው!...ምንም መልስ አልሰጡኝም!...ከ ጎን ያለችው ልጅ እምባ በተናነቀው ድምፅ! ልጃቸው አርፋለች አለችኝ!....''ማ ..ቤቲ?'' አልኳት...''አዎ'' አለችኝ!....''እራሷን ከ ማጥፋቷ በፊት ይሄን ወረቀት ፅፋ ነበር'' ብላ ከ እናትየው እጅ ላይ ወረቀቱን ወስዳ ሰጠችኝ!...እጄ እየተንቀጠቀጠ ተቀበልኳትና አየሁት ....''አይዞሽ የሚለኝ ሰው ብቻ ነበር የፈለኩት ....'' ይላል! ምንም አላልኩም.... ወረቀቱን እንደያዝኩ እግሬን እየጎተትኩ ከድንኳኑ ወጣሁ!...በእርግጥ ወዴት እንደምሄድ አላውቅም!
! ይሄ ፅሁፍ የሚያስተምረን በሂወታችን ችላ የምንለው ነገር እስከ ሂወት ማጣት ድረስ ዋጋ እንደሚያስከፍለን ነው
::አንበበው ከወደደት👍👍 ተጭናችሁ እለፉ
✍እንማር
ይ 🀄️ላ🀄️ሉን! 😀
💔 https://t.me/yefikirtelegramet 💔