የ25 ዓመት ረዥም ጉዞ የተጀመረው በዚህ ነው!!
ውድ የአዲስ አድማስ ቤተሰቦች፡- የመጀመሪያው አዲስ አድማስ ጋዜጣ ታትሞ ለንባብ የበቃው ታህሳስ 29 ቀን 1992 ዓ.ም ነበር - የዛሬ 25 ዓመት በዕለተ ቅዳሜ፡፡ ከዚያን ጊዜ አንስቶ ያለ አንድ ቅዳሜ በስተቀር ጋዜጣው ያልወጣበት ቀን የለም፡፡ እሱም ቢሆን የተከሰተው በ97 ምርጫ ማግስት በተከሰተው ፖለቲካዊ ቀውስ ሳቢያ ነበር፡፡
የዛሬ 20 ዓመት፣ የአዲስ አድማስ ጠንሳሽ፣ መሥራችና ባለቤት አሰፋ ጎሳዬ (አሴ) በድንገተኛ ህመም ህይወቱ ባለፈበት ወቅት እንኳን ጋዜጣው ሳይታተም አልቀረም፡፡ ረቡዕ ከቀብር በኋላ ቢሮ ገብተን የቅዳሜውን ጋዜጣ ስናዘጋጅ ትዝ ይለኛል፡፡ እያነባንም ቢሆን የቅዳሜውን ሳምንታዊ ጋዜጣ በጉጉት ለሚጠብቀን ውድ አንባቢ አድርሰናል፡፡
አሁን ሳስበው ታዲያ ያኔ ትክክለኛ ሥራ ነው የሰራነው፡፡ የአሴ ነፍስ በዚያ ተግባራችን ጮቤ እንደረገጠች አልጠራጠርም፡፡ እርሱ በህይወት ባይኖርም አዲስ አድማስ መታተሟ፣ ህልምና ራዕዩን ማስቀጠያ ብቸኛ መንገድ ነበር፡፡
እነሆ ከዚያም በኋላ ሁለት አሰርት ዓመታትን አስቆጥራ፣ በብዙ ውጣ ውረዶችና ተግዳሮቶች አልፍ እነሆ ለ25ኛ ዓመቷ በቅታለች፡፡ በግሉ ፕሬስ ሩብ ክፍለዘመን ቀላል ጊዜ አይደለም፡፡ ቀላል ዕድሜ አይደለም፡፡ የ25 ዓመት ጉዞ ሀ ብሎ የተጀመረው ግን በዚህ ነው፡፡ ታህሳስ 29 ቀን 1992 ዓ.ም በታተመችው አዲስ አድማሰ ጋዜጣ፡፡
እንኳን አደረሳችሁ፤ አደረሰን!!
ውድ የአዲስ አድማስ ቤተሰቦች፡- የመጀመሪያው አዲስ አድማስ ጋዜጣ ታትሞ ለንባብ የበቃው ታህሳስ 29 ቀን 1992 ዓ.ም ነበር - የዛሬ 25 ዓመት በዕለተ ቅዳሜ፡፡ ከዚያን ጊዜ አንስቶ ያለ አንድ ቅዳሜ በስተቀር ጋዜጣው ያልወጣበት ቀን የለም፡፡ እሱም ቢሆን የተከሰተው በ97 ምርጫ ማግስት በተከሰተው ፖለቲካዊ ቀውስ ሳቢያ ነበር፡፡
የዛሬ 20 ዓመት፣ የአዲስ አድማስ ጠንሳሽ፣ መሥራችና ባለቤት አሰፋ ጎሳዬ (አሴ) በድንገተኛ ህመም ህይወቱ ባለፈበት ወቅት እንኳን ጋዜጣው ሳይታተም አልቀረም፡፡ ረቡዕ ከቀብር በኋላ ቢሮ ገብተን የቅዳሜውን ጋዜጣ ስናዘጋጅ ትዝ ይለኛል፡፡ እያነባንም ቢሆን የቅዳሜውን ሳምንታዊ ጋዜጣ በጉጉት ለሚጠብቀን ውድ አንባቢ አድርሰናል፡፡
አሁን ሳስበው ታዲያ ያኔ ትክክለኛ ሥራ ነው የሰራነው፡፡ የአሴ ነፍስ በዚያ ተግባራችን ጮቤ እንደረገጠች አልጠራጠርም፡፡ እርሱ በህይወት ባይኖርም አዲስ አድማስ መታተሟ፣ ህልምና ራዕዩን ማስቀጠያ ብቸኛ መንገድ ነበር፡፡
እነሆ ከዚያም በኋላ ሁለት አሰርት ዓመታትን አስቆጥራ፣ በብዙ ውጣ ውረዶችና ተግዳሮቶች አልፍ እነሆ ለ25ኛ ዓመቷ በቅታለች፡፡ በግሉ ፕሬስ ሩብ ክፍለዘመን ቀላል ጊዜ አይደለም፡፡ ቀላል ዕድሜ አይደለም፡፡ የ25 ዓመት ጉዞ ሀ ብሎ የተጀመረው ግን በዚህ ነው፡፡ ታህሳስ 29 ቀን 1992 ዓ.ም በታተመችው አዲስ አድማሰ ጋዜጣ፡፡
እንኳን አደረሳችሁ፤ አደረሰን!!