ስለ ሃይማኖታዊ ውይይት አንዳንድ ነገሮች
ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በማኅበራዊ ሚዲያው ሃይማኖታዊ ክርክሮች በረከት እያሉ መጥተዋል። እነርሱን ተከትሎ ደግሞ በአንድ ቤት ውስጥ ባሉትም መካከል ውይይቶች አለፍ ሲልም መነቃቀፎች አንዳንድ ጊዜም ደግሞ በእወቀትም ይሁን ያለዕውቀት መጠላለፍ የሚመስሉ ሁኔታዎች እንዳሉ ይታያል። በእንዲህ ያለው ጊዜ ማድረግ የሚገባን ምንድን ነው የሚሉ ድምፆችም ይሰማሉ። የምናደርገው ነገር በዚህ ጊዜ በዚያ ጊዜ የሚባልበት መሆኑ ባይቀርም በእኔ እምነት በአግባቡ ከተጠቀምንበት እና ከተማርንበት ከሁሉም ልንጠቀም እና መንገዳችንን ትክክል የሆነልን እርሱኑ ልናጸና ፈንገጥ ያልነው ወይም የመንገድ ጠርዝ በመርገጥ የተንሸራተትን ካለንም ልንመለስ እና በመሐል መንገድ እንድንጓዝ ሊጠቅመን ይችላል። እጅግ በትንሹ ከሰማኋቸው ተነሥቼ አጠቃላይ መርሕ ተኮር ሁኔታዎች በዚህ ጽሑፍ ልጠቁምና እንዳስፈላጊነቱ ደግሞ በመከራከሪያ ነጥቦቹም ላይ ላክል እችላለሁ። ከዚህ በፊት “አድማሱ ጀንበሬ ሕይወቱ እና ትምህርቱ” የሚለው መጽሐፍ ሲታተም በመቅድምነት የወጣ አጭር ጽሑፍ ላይ ከንባቦቼ ከቀራረምኩት የተወሰኑ ሀሳቦችን ማጋራቴ ይታወቃል። እነዚያን ያላየ ቢያያቸው አንድ ነገር እንኳ የሚጠቅም ሊያገኝ ይችላል ብዬ አምናለሁ። እነዚያን ያነሣሁበት ምክንያት ግን እነዚህን ጉዳዮች የእነዚያ ቀጣይ አድርጋችሁ እንድትወስዷቸው ለማሳሰብ ያህል ነው።
በውይይትም ሆነ በክርክር ውስጥ ያለን አገልጋዮች ልንጠነቀቅባቸው የሚገቡን ጉዳዮች መካከል
1) በራስ ማስተዋል አለመደገፍ
በመጽሐፍ ቅዱስ ቅዱስ ከተጻፉት ታሪኮች፣ ምክሮች እና ትርጓሜዎች መካከል አንደኛው በራሳቸን መረዳት፣ ማስተዋል (reasoning) ላይ እንዳንደገፍ እና በዚህ ምክንያት ወደ ፈተና እናዳንገባ መጠበቅን የሚመለከት ነው። ለምሳሌ ያህል ያዕቆብ ከዔሳው ብኩርናውን የወሰደበትን ሒደት ስንመለከተው በምንም ዓይነት ተፈጥሮአዊ አመክንዮ ይሠራል ይሆናል ለማለት የሚቻል አይደለም። የአብርሃምና ሣራ እንዲሁም የዘካርያስ እና የኤልሳቤጥ በዕርጅና ልጅ መውለድ የሚያስተምረንም ይህንኑ ነው። ዋናው ጉዳይ ግን እግዚአብሔር እርሱ ባወቀ ኤሳው ቀድሞ እንዳይወለድ እና ያዕቆብ ቀድሞ እንዲወለድ ማድረግ እየቻለ ከተወለደ በኋላ በኩርናውን እንዲወስድ ለምን አደረገ? ለእነ አብርሃም እና ለእነ ዘካርያስ ልጆችን ቀድሞ ለምን አልሰጣቸውም ብለን ብንጠይቅ ዋናው መልስ እግዚአብሔር ሊያስተምረን የፈለገው ከተፈጥሮ ሕግ እና ከየትኛውም አመክንዮ ወይም የሰው የሕሊና መረዳት የሚያልፉ ነገሮችን የሚያደርግ መሆኑን ለማሳየት ነው። በመጽሐፍም “በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ፤” /ምሳ 3 ፡ 5/ ተብሎ የተጻፈው ለዚህ ነው።
በርግጥ ሃይማኖት የሚባለውም ይህ ነው። ከመረዳታችን እና ከሎጂካችን ባሻገር እግዚአብሔር የሠራውንና የሚሠራውን ማመን። ጌታችን ከእመቤታችን ከንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያም የተጸነሰበት፣ የተወለደበት፣ የሞተበት፣ ድኅነታችን የፈጸመበት፣ የእመቤትችን በሁለንተና ንጽሕት መሆን እና የመሳሰሉትን ነገሮች መረዳት የሚቻለው ያዕቆብ ከዔሳው ብኩርናውን በወሰደበት መንገድ ብቻ ነው። ይህም ማለት ከሎጂክና ከአመክንዮ ተላልቅቆ እግዚአብሔር አምላክነቱን በየዘመኑ ትውልድ እግዚአብሔርነቱን የገለጸባቸውንና በአእምሮ ከመታሰብ፣ በሎጂክ ከመረዳት በላይ የሆኑትን በመቀበል ነው። ያዕቆብ ብኩርናን የወሰደበት መንገድ በእምነት የምንቀበለው ብቻ ነውና። እነዚህ ነገሮች የተፈጸሙት፣ እና በቅዱሳት መጻሕፍት የተመዘገቡበት ዋና ዓላማም የአካላዊ ቃል ሰው መሆን ጋር ተያይዞ ለሚነሱ ጥያቄዎች በሙሉ አስቀድመው የተዘጋጁ መልሶች እንዲሆኑ ነው።
በራስ ማስተዋል ወይም በራስ የመረዳት ችሎታ ላይ መደገፍ ቢያንስ ሁለት ታላላቅ ፈተናዎችን ወደ እኛ ያመጣል። የመጀመሪያው ከእምነት መጉደል ነው። ይህ ደግሞ እንኳን በእኔ ቢጤዎች ይቅርና ጻድቁ ዘካርያስንም ፈትኖታል። ዘካርያስ ቅዱስ ገብርኤልን የተከራከረው ዕውቀት ወይም የተፈጥሮ ሕግ ገድቦት ነውና። ሰው ካረጀ ካፈጀ በኋላ አይወልድም የሚለው ዕውቀቱ ወይም የተፈጥሮ ሕጉ ስሕተት ሆኖ አልነበረም። የእግዚአብሔር የማዳን ሥራ ግን ከእነዚህ የሚያልፍ ነበረ። ስለዚህ በመረዳት ወይንም በማስተዋላችን ላይ መደገፍ መጀመሪያ የሚያመጣው ፈተና እንኳን ሰዎች መላእክትም ቢናገሩን እንድንከራከር ሊያደርገን ይችላል ማለት ነው። ሌላው ቀርቶ ትናንት ያከበርነው የልደተ ስምዖን ታሪክ የሚያስታውሰንም ይህንኑ ገጠመኝ ነው። ሴት እንጂ ድንግል አትወልድም የሚል ሀሳብ ይዞ ድንግል ትጸንሳለች የሚለውን የነቢዩን የኢሳይያስን ቃል ሴት ወደሚል ለመቀየር ሞክሮ ከእግዚአብሔር ይህን ሳያይ እንዳይሞት የተረዳው የእግዚአብሔር አሠራር ከሰው ማስተዋል እና መረዳት ባሻገር ስለሆነ ነው። በዚህች መንገድ መጓዝ የጀመረ ሰው አይሁድ ከመስቀል ውረድና እንመንብህ እንዳሉት በራስ መረዳት ቅድመ ሁኔታ አስቀመጦ እግዚአብሔርን መፈተኑ የማይቀር ነው።
ሁለተኛው እና ከባዱ ፈተና ደግሞ ሌሎች ይህን መረዳት እንደማይችሉ በማሰብ የዲያብሎስ ረቂቅ ወጥመድ በሆነው የትዕቢት ወጥመድ ውስጥ መውደቅን ሊያስከትል ይችላል። ይህ ደግሞ ብዙ ጥፋቶችን አከታትሎ ያመጣብናል። ሰሎሞን “በልቡ የታበየ ሁሉ በእግዚአብሔር ዘንድ ርኩስ ነው፥ እጅ በእጅም ሳይቀጣ አይቀርም” /ምሳ 16 ፡ 5/ ሲል እንደገለጸው ቅጣቱም ቀጥታ ከእግዚአብሔር ይሆናል። ለሰውየው ግን እያወቀ ወይንም እውቀቱ ትክክል ስለሆነ እንጂ እየታበየ እና እየተጎዳ እንደሆነ አይሰማውም። ለዚህም ነው “ለሰው ቅን የምትመስል መንገድ አለች፤ ፍጻሜዋ ግን የሞት መንገድ ነው” /ምሳ 16 ፡ 25/ ተብሎ የተጻፈው ። ስለዚህ ከሁለቱም ለመጠበቅ በራስ መረዳት ላይ አለመደገፍ ትልቁ መፍትሔ ነው። የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች እና ምክሮች ያረጋገጡልንም ይህንኑ ነው።
2) ከትዕቢት / ካለመሸነፍ መንፈስ መራቅ
የትዕቢት ነገር ከላይም የተጠቆመ ቢሆንም በዓለም ለተፈጠሩት ችግሮች ሁሉ መሠረቱ ትዕቢት ነው። በተለይ በሰው ፊት ተሸናፊ መባልን፣ አያውቅም መባልን መፍራት፣ ተሳስቷል መባልን መሸሽ ወደ ማስረዳት እና ራስን ነጻ ለማውጣት ሲባል ወደ ተለጠጠ ክርክር ይስባል፣ ከዚያም ወደ ባሰው ችግር ወይም ፈተና ሊያደርስ ይችላል። ስለዚህ ጥያቄዎች ሲፈጠሩ ቆም ብሎ ማድመጥ ፣ መጸለይ እና ቅዱሳት መጻሕፍትን እያጠኑ ሊቃውንትን ደጋግሞ መጠየቅ ብዙ ችግሮችን ያስወግዳል። ይልቁንም ልሳሳት እችላለሁ በሚል ትሑት ሰብእና ውስጥ ሆኖ እግዚአብሔርን የሚለምን ሰው እግዚአብሔር በፍጥነት ከዚህ ችግር እንደሚያወጣው የታመነ ነው።
3) የምንጮችን ዐውድ በአግባቡ ለመራዳት መጣር
ብዙ ጊዜ ወደ ክርክር ተይዘው የሚወጡት ምንጮች ወይም ማስረጃዎች በራሳቸው ምንም ችግር የለባቸውም። ሆኖም ከተነገሩበት ወይም ከተጻፉበት ዐውድ አውጥተን ከተመለከትናቸው ችግር ውስጥ ልንወድቅ እንችላለን። ለምሳሌ ያህል ጥንተ አብሶን በተመለከተ የሚነሣው ክርክር ለዚህ ጥሩ ምሳሌ ሊሆን ይችላል። የጥንት ሊቃውንት ጌታ ሥጋውን ከሰማይ ይዞ ወርዷል፣ በእመቤታችን አደረባት እንጂ ሥጋን ከእርሷ አልነሣም ለሚሉ የዚያ ዘመን መና/ፍቃን የተሰጡ መልሶች ያንኑ የበደለውን ሰው የአዳምን ሥጋ ነው የተዋሐደ ሲሉ ያንን የሳተውን፣ የወደቀውን፣ የጎሰቆለውን የእዳም ሥጋ እንደተዋሐደ ተከራክረው አስረድተዋል። ሆኖም እነዚህ አገላለጾች እመቤታችንን ጥንተ አብሶ አለባት ሊያስብሉ አይችሉም። (ይህን ጉዳይ
ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በማኅበራዊ ሚዲያው ሃይማኖታዊ ክርክሮች በረከት እያሉ መጥተዋል። እነርሱን ተከትሎ ደግሞ በአንድ ቤት ውስጥ ባሉትም መካከል ውይይቶች አለፍ ሲልም መነቃቀፎች አንዳንድ ጊዜም ደግሞ በእወቀትም ይሁን ያለዕውቀት መጠላለፍ የሚመስሉ ሁኔታዎች እንዳሉ ይታያል። በእንዲህ ያለው ጊዜ ማድረግ የሚገባን ምንድን ነው የሚሉ ድምፆችም ይሰማሉ። የምናደርገው ነገር በዚህ ጊዜ በዚያ ጊዜ የሚባልበት መሆኑ ባይቀርም በእኔ እምነት በአግባቡ ከተጠቀምንበት እና ከተማርንበት ከሁሉም ልንጠቀም እና መንገዳችንን ትክክል የሆነልን እርሱኑ ልናጸና ፈንገጥ ያልነው ወይም የመንገድ ጠርዝ በመርገጥ የተንሸራተትን ካለንም ልንመለስ እና በመሐል መንገድ እንድንጓዝ ሊጠቅመን ይችላል። እጅግ በትንሹ ከሰማኋቸው ተነሥቼ አጠቃላይ መርሕ ተኮር ሁኔታዎች በዚህ ጽሑፍ ልጠቁምና እንዳስፈላጊነቱ ደግሞ በመከራከሪያ ነጥቦቹም ላይ ላክል እችላለሁ። ከዚህ በፊት “አድማሱ ጀንበሬ ሕይወቱ እና ትምህርቱ” የሚለው መጽሐፍ ሲታተም በመቅድምነት የወጣ አጭር ጽሑፍ ላይ ከንባቦቼ ከቀራረምኩት የተወሰኑ ሀሳቦችን ማጋራቴ ይታወቃል። እነዚያን ያላየ ቢያያቸው አንድ ነገር እንኳ የሚጠቅም ሊያገኝ ይችላል ብዬ አምናለሁ። እነዚያን ያነሣሁበት ምክንያት ግን እነዚህን ጉዳዮች የእነዚያ ቀጣይ አድርጋችሁ እንድትወስዷቸው ለማሳሰብ ያህል ነው።
በውይይትም ሆነ በክርክር ውስጥ ያለን አገልጋዮች ልንጠነቀቅባቸው የሚገቡን ጉዳዮች መካከል
1) በራስ ማስተዋል አለመደገፍ
በመጽሐፍ ቅዱስ ቅዱስ ከተጻፉት ታሪኮች፣ ምክሮች እና ትርጓሜዎች መካከል አንደኛው በራሳቸን መረዳት፣ ማስተዋል (reasoning) ላይ እንዳንደገፍ እና በዚህ ምክንያት ወደ ፈተና እናዳንገባ መጠበቅን የሚመለከት ነው። ለምሳሌ ያህል ያዕቆብ ከዔሳው ብኩርናውን የወሰደበትን ሒደት ስንመለከተው በምንም ዓይነት ተፈጥሮአዊ አመክንዮ ይሠራል ይሆናል ለማለት የሚቻል አይደለም። የአብርሃምና ሣራ እንዲሁም የዘካርያስ እና የኤልሳቤጥ በዕርጅና ልጅ መውለድ የሚያስተምረንም ይህንኑ ነው። ዋናው ጉዳይ ግን እግዚአብሔር እርሱ ባወቀ ኤሳው ቀድሞ እንዳይወለድ እና ያዕቆብ ቀድሞ እንዲወለድ ማድረግ እየቻለ ከተወለደ በኋላ በኩርናውን እንዲወስድ ለምን አደረገ? ለእነ አብርሃም እና ለእነ ዘካርያስ ልጆችን ቀድሞ ለምን አልሰጣቸውም ብለን ብንጠይቅ ዋናው መልስ እግዚአብሔር ሊያስተምረን የፈለገው ከተፈጥሮ ሕግ እና ከየትኛውም አመክንዮ ወይም የሰው የሕሊና መረዳት የሚያልፉ ነገሮችን የሚያደርግ መሆኑን ለማሳየት ነው። በመጽሐፍም “በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ፤” /ምሳ 3 ፡ 5/ ተብሎ የተጻፈው ለዚህ ነው።
በርግጥ ሃይማኖት የሚባለውም ይህ ነው። ከመረዳታችን እና ከሎጂካችን ባሻገር እግዚአብሔር የሠራውንና የሚሠራውን ማመን። ጌታችን ከእመቤታችን ከንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያም የተጸነሰበት፣ የተወለደበት፣ የሞተበት፣ ድኅነታችን የፈጸመበት፣ የእመቤትችን በሁለንተና ንጽሕት መሆን እና የመሳሰሉትን ነገሮች መረዳት የሚቻለው ያዕቆብ ከዔሳው ብኩርናውን በወሰደበት መንገድ ብቻ ነው። ይህም ማለት ከሎጂክና ከአመክንዮ ተላልቅቆ እግዚአብሔር አምላክነቱን በየዘመኑ ትውልድ እግዚአብሔርነቱን የገለጸባቸውንና በአእምሮ ከመታሰብ፣ በሎጂክ ከመረዳት በላይ የሆኑትን በመቀበል ነው። ያዕቆብ ብኩርናን የወሰደበት መንገድ በእምነት የምንቀበለው ብቻ ነውና። እነዚህ ነገሮች የተፈጸሙት፣ እና በቅዱሳት መጻሕፍት የተመዘገቡበት ዋና ዓላማም የአካላዊ ቃል ሰው መሆን ጋር ተያይዞ ለሚነሱ ጥያቄዎች በሙሉ አስቀድመው የተዘጋጁ መልሶች እንዲሆኑ ነው።
በራስ ማስተዋል ወይም በራስ የመረዳት ችሎታ ላይ መደገፍ ቢያንስ ሁለት ታላላቅ ፈተናዎችን ወደ እኛ ያመጣል። የመጀመሪያው ከእምነት መጉደል ነው። ይህ ደግሞ እንኳን በእኔ ቢጤዎች ይቅርና ጻድቁ ዘካርያስንም ፈትኖታል። ዘካርያስ ቅዱስ ገብርኤልን የተከራከረው ዕውቀት ወይም የተፈጥሮ ሕግ ገድቦት ነውና። ሰው ካረጀ ካፈጀ በኋላ አይወልድም የሚለው ዕውቀቱ ወይም የተፈጥሮ ሕጉ ስሕተት ሆኖ አልነበረም። የእግዚአብሔር የማዳን ሥራ ግን ከእነዚህ የሚያልፍ ነበረ። ስለዚህ በመረዳት ወይንም በማስተዋላችን ላይ መደገፍ መጀመሪያ የሚያመጣው ፈተና እንኳን ሰዎች መላእክትም ቢናገሩን እንድንከራከር ሊያደርገን ይችላል ማለት ነው። ሌላው ቀርቶ ትናንት ያከበርነው የልደተ ስምዖን ታሪክ የሚያስታውሰንም ይህንኑ ገጠመኝ ነው። ሴት እንጂ ድንግል አትወልድም የሚል ሀሳብ ይዞ ድንግል ትጸንሳለች የሚለውን የነቢዩን የኢሳይያስን ቃል ሴት ወደሚል ለመቀየር ሞክሮ ከእግዚአብሔር ይህን ሳያይ እንዳይሞት የተረዳው የእግዚአብሔር አሠራር ከሰው ማስተዋል እና መረዳት ባሻገር ስለሆነ ነው። በዚህች መንገድ መጓዝ የጀመረ ሰው አይሁድ ከመስቀል ውረድና እንመንብህ እንዳሉት በራስ መረዳት ቅድመ ሁኔታ አስቀመጦ እግዚአብሔርን መፈተኑ የማይቀር ነው።
ሁለተኛው እና ከባዱ ፈተና ደግሞ ሌሎች ይህን መረዳት እንደማይችሉ በማሰብ የዲያብሎስ ረቂቅ ወጥመድ በሆነው የትዕቢት ወጥመድ ውስጥ መውደቅን ሊያስከትል ይችላል። ይህ ደግሞ ብዙ ጥፋቶችን አከታትሎ ያመጣብናል። ሰሎሞን “በልቡ የታበየ ሁሉ በእግዚአብሔር ዘንድ ርኩስ ነው፥ እጅ በእጅም ሳይቀጣ አይቀርም” /ምሳ 16 ፡ 5/ ሲል እንደገለጸው ቅጣቱም ቀጥታ ከእግዚአብሔር ይሆናል። ለሰውየው ግን እያወቀ ወይንም እውቀቱ ትክክል ስለሆነ እንጂ እየታበየ እና እየተጎዳ እንደሆነ አይሰማውም። ለዚህም ነው “ለሰው ቅን የምትመስል መንገድ አለች፤ ፍጻሜዋ ግን የሞት መንገድ ነው” /ምሳ 16 ፡ 25/ ተብሎ የተጻፈው ። ስለዚህ ከሁለቱም ለመጠበቅ በራስ መረዳት ላይ አለመደገፍ ትልቁ መፍትሔ ነው። የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች እና ምክሮች ያረጋገጡልንም ይህንኑ ነው።
2) ከትዕቢት / ካለመሸነፍ መንፈስ መራቅ
የትዕቢት ነገር ከላይም የተጠቆመ ቢሆንም በዓለም ለተፈጠሩት ችግሮች ሁሉ መሠረቱ ትዕቢት ነው። በተለይ በሰው ፊት ተሸናፊ መባልን፣ አያውቅም መባልን መፍራት፣ ተሳስቷል መባልን መሸሽ ወደ ማስረዳት እና ራስን ነጻ ለማውጣት ሲባል ወደ ተለጠጠ ክርክር ይስባል፣ ከዚያም ወደ ባሰው ችግር ወይም ፈተና ሊያደርስ ይችላል። ስለዚህ ጥያቄዎች ሲፈጠሩ ቆም ብሎ ማድመጥ ፣ መጸለይ እና ቅዱሳት መጻሕፍትን እያጠኑ ሊቃውንትን ደጋግሞ መጠየቅ ብዙ ችግሮችን ያስወግዳል። ይልቁንም ልሳሳት እችላለሁ በሚል ትሑት ሰብእና ውስጥ ሆኖ እግዚአብሔርን የሚለምን ሰው እግዚአብሔር በፍጥነት ከዚህ ችግር እንደሚያወጣው የታመነ ነው።
3) የምንጮችን ዐውድ በአግባቡ ለመራዳት መጣር
ብዙ ጊዜ ወደ ክርክር ተይዘው የሚወጡት ምንጮች ወይም ማስረጃዎች በራሳቸው ምንም ችግር የለባቸውም። ሆኖም ከተነገሩበት ወይም ከተጻፉበት ዐውድ አውጥተን ከተመለከትናቸው ችግር ውስጥ ልንወድቅ እንችላለን። ለምሳሌ ያህል ጥንተ አብሶን በተመለከተ የሚነሣው ክርክር ለዚህ ጥሩ ምሳሌ ሊሆን ይችላል። የጥንት ሊቃውንት ጌታ ሥጋውን ከሰማይ ይዞ ወርዷል፣ በእመቤታችን አደረባት እንጂ ሥጋን ከእርሷ አልነሣም ለሚሉ የዚያ ዘመን መና/ፍቃን የተሰጡ መልሶች ያንኑ የበደለውን ሰው የአዳምን ሥጋ ነው የተዋሐደ ሲሉ ያንን የሳተውን፣ የወደቀውን፣ የጎሰቆለውን የእዳም ሥጋ እንደተዋሐደ ተከራክረው አስረድተዋል። ሆኖም እነዚህ አገላለጾች እመቤታችንን ጥንተ አብሶ አለባት ሊያስብሉ አይችሉም። (ይህን ጉዳይ