†
† 🕊 መንፈሳዊው መሰላል 🕊 †
💖
[ ዓ ለ ም ን ስ ለ መ ተ ው ! ]
[ ክፍል አምስት ]
▬▬▬▬▬▬ ♱ ▬▬▬▬▬▬
አሳባችንን ወደ የውሃት .... !
❝ የሆነ አሳባችንን ወደ የውሃት ፣ ወደ ጥልቅ ቍጣ አልባነት፣ ወደ ንቍነትም በማምጣት ፣ የንጽሕናና የንቍነት ወዳጅ እስካላደረግነው ድረስ በተለይ በቸልታ ሕይወት በሚኖሩ ዘንድ ፣ በርካታ የሚሆኑ የማይታዩ መከራትን የሚያመጣ ነውና ይህ በእውነት ታላቅ ፣ በእውነት እጅግ ታላቅ መከራ ነው፡፡
ሆኖም ግን ደካማና በፈቃደ ሥጋ የምንመላለስ እኛ ጽናት የለሽነታችንንና ደካማ ጠባያችንን ጥርጥር በሌለበት እምነት ወደ ክርስቶስ እናቀርብ ፣ ይህንም ለእርሱ እንናዘዝ ዘንድ እንበርታ ፤ ሳናቋርጥ ጥልቅ ወደ ሆነ ትሕትና ራሳችንን የምንጥል ከሆነ ብቻ ፣ ለእኛ ከሚገባው በላይ የሆነውን የእርሱን ርዳታ እንኳ እንደምናገኝ ርግጠኛ እንሆናለን፡፡
ወደ እዚህ አስደናቂ ፣ ጽኑና አስቸጋሪ ቢሆንም ቅሉ ፣ ነገር ግን ደግሞ ቀላል ወደ ሆነው መልካም ተጋድሎ የገቡ ሁሉ ፣ በእውነት ሰማያዊ የሆነው እሳት በውስጣቸው ያድር ዘንድ የሚጠብቁ ከሆነ ወደ እሳቱ ዘለው መግባት እንዳለባቸው ሊገነዘቡ ይገባል፡፡ ነገር ግን እያንዳንዱ ሰው አገልግሎቱ ወደ ገዛ ፍርዱ ወደ ገዛ ፍርዱ እንዳይመራው ፣ ራሱን ይመርምር እንጀራውንም ከመራራ ቅጠል ጋር ይብላ ፣ ጽዋውንም ከእንባ ጋር ይጠጣ፡፡ ተጠምቆ የነበረ ሰው ሁሉ ድኅነት ያላገኘ ከነበረ ተከትሎ ስለሚሆነው ነገር ዝም እላለሁ፡፡
ወደዚህ ተጋድሎ የገቡ ጽኑ መሠረትን ማኖር ይችሉ ዘንድ ሁሉንም ነገር መተው ፣ ሁሉንም ነገሮች መናቅ ፣ በሁሉም ነገሮች ላይ መዘበትና ሁሉንም ነገሮች አራግፈው መጣል አለባቸው፡፡ ለሦስቱ ንጣፎችና ለሦስቱ ምሰሶዎች ግሩም መሠረት የውሃነት ፣ ጾም ፣ ራስንም መግዛት ነው፡፡ በተፈጥሮ ሕፃናት የሆኑትን አርአያነት በመንሣት ፣ በክርስቶስ ሕፃናት የሆኑ ሁሉ በእሊህ ምግባራት ይጀምሩ፡፡ በእነርሱ [በሕፃናት] ዘንድ ከቶም አንዳች ተንኮል ወይም ማታለል አታገኝምና፡፡ እነሱ የማይረካ ፍላጎት ፣ የማይጠግብ ሆድ ፣ የሚቃጠል ወይም እንደ አውሬ ቍጡ የሆነ ሰውነት የላቸውም ፤ ምናልባት ግን አድገው የበዛ ምግብ የሚመገቡ እንደ መሆናቸው መጠን ፣ ተፈጥሮአዊ ፈቃዶቻቸው [ምኞታቸው] ደግሞ ይጨምራሉ፡፡ ❞
[ ዮሐንስ ክሊማኮስ [ ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰዋስው ]
🕊 💖 🕊
† 🕊 መንፈሳዊው መሰላል 🕊 †
💖
[ ዓ ለ ም ን ስ ለ መ ተ ው ! ]
[ ክፍል አምስት ]
▬▬▬▬▬▬ ♱ ▬▬▬▬▬▬
አሳባችንን ወደ የውሃት .... !
❝ የሆነ አሳባችንን ወደ የውሃት ፣ ወደ ጥልቅ ቍጣ አልባነት፣ ወደ ንቍነትም በማምጣት ፣ የንጽሕናና የንቍነት ወዳጅ እስካላደረግነው ድረስ በተለይ በቸልታ ሕይወት በሚኖሩ ዘንድ ፣ በርካታ የሚሆኑ የማይታዩ መከራትን የሚያመጣ ነውና ይህ በእውነት ታላቅ ፣ በእውነት እጅግ ታላቅ መከራ ነው፡፡
ሆኖም ግን ደካማና በፈቃደ ሥጋ የምንመላለስ እኛ ጽናት የለሽነታችንንና ደካማ ጠባያችንን ጥርጥር በሌለበት እምነት ወደ ክርስቶስ እናቀርብ ፣ ይህንም ለእርሱ እንናዘዝ ዘንድ እንበርታ ፤ ሳናቋርጥ ጥልቅ ወደ ሆነ ትሕትና ራሳችንን የምንጥል ከሆነ ብቻ ፣ ለእኛ ከሚገባው በላይ የሆነውን የእርሱን ርዳታ እንኳ እንደምናገኝ ርግጠኛ እንሆናለን፡፡
ወደ እዚህ አስደናቂ ፣ ጽኑና አስቸጋሪ ቢሆንም ቅሉ ፣ ነገር ግን ደግሞ ቀላል ወደ ሆነው መልካም ተጋድሎ የገቡ ሁሉ ፣ በእውነት ሰማያዊ የሆነው እሳት በውስጣቸው ያድር ዘንድ የሚጠብቁ ከሆነ ወደ እሳቱ ዘለው መግባት እንዳለባቸው ሊገነዘቡ ይገባል፡፡ ነገር ግን እያንዳንዱ ሰው አገልግሎቱ ወደ ገዛ ፍርዱ ወደ ገዛ ፍርዱ እንዳይመራው ፣ ራሱን ይመርምር እንጀራውንም ከመራራ ቅጠል ጋር ይብላ ፣ ጽዋውንም ከእንባ ጋር ይጠጣ፡፡ ተጠምቆ የነበረ ሰው ሁሉ ድኅነት ያላገኘ ከነበረ ተከትሎ ስለሚሆነው ነገር ዝም እላለሁ፡፡
ወደዚህ ተጋድሎ የገቡ ጽኑ መሠረትን ማኖር ይችሉ ዘንድ ሁሉንም ነገር መተው ፣ ሁሉንም ነገሮች መናቅ ፣ በሁሉም ነገሮች ላይ መዘበትና ሁሉንም ነገሮች አራግፈው መጣል አለባቸው፡፡ ለሦስቱ ንጣፎችና ለሦስቱ ምሰሶዎች ግሩም መሠረት የውሃነት ፣ ጾም ፣ ራስንም መግዛት ነው፡፡ በተፈጥሮ ሕፃናት የሆኑትን አርአያነት በመንሣት ፣ በክርስቶስ ሕፃናት የሆኑ ሁሉ በእሊህ ምግባራት ይጀምሩ፡፡ በእነርሱ [በሕፃናት] ዘንድ ከቶም አንዳች ተንኮል ወይም ማታለል አታገኝምና፡፡ እነሱ የማይረካ ፍላጎት ፣ የማይጠግብ ሆድ ፣ የሚቃጠል ወይም እንደ አውሬ ቍጡ የሆነ ሰውነት የላቸውም ፤ ምናልባት ግን አድገው የበዛ ምግብ የሚመገቡ እንደ መሆናቸው መጠን ፣ ተፈጥሮአዊ ፈቃዶቻቸው [ምኞታቸው] ደግሞ ይጨምራሉ፡፡ ❞
[ ዮሐንስ ክሊማኮስ [ ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰዋስው ]
🕊 💖 🕊