🔥#የጀሀነም_ቅጣትን_ሲያስታዉስ_የሞተዉ_ወጣት
✍ አሚር ሰይድ
መንሱር ኢብን አማር እንዲህ በማለት ተናግሯል፦ “አንድ ሌሊት የነጋ መስሎኝ ከቤቴ ወጥቼ ስሄድ ንጋቱ አለመቀረቡን ተገነዘብኩ፡፡ ከዚያም በአንድ ሰው ቤት አጠገብ ሳልፍ አንድ ወጣት ምርር ብሎ እያለቀሰ ጌታውን እንዲህ በማለት ሲማፀን ሰማሁት፡-
ጌታዬ ሆይ! እኔ ብዙ ሀጢያቶችን ፈፅሜያለሁ፡፡ በዚህም ድርጊቴ ራሴን መቀመቅ አውርጃለሁ። ዓላማዬ ያንተን ትዕዛዝ መጣስ አልነበረም። ሆኖም ግን ነፍሴ አሸነፈችኝ፡፡ ምንም እንኳን እኔ እራሴን ብበድልና መጥፎ ድርጊቶችን ብፈፅምም አንተ ግን ለዚህ ድርጊቱ የወሰድክብኝ ብቀላ የለም፡፡ በዚህ ቻይነትህና ይቅር ባይነትህም ተዘናግቼ ተወሰድኩ። ሀጢያቶቼንም የሠራኋቸው ባለማወቅ ነው፡፡ አሁን ግን መሳሳቴን ተገነዘብኩ። የምትቀጣኝ ከሆነ ምን ይውጠኛል? ወዮልኝ ለራሴ! ጌታዬ ሆይ! ባሮችህን ሁሉ በሲራጥ ድልድይ ላይ እንዲያልፉ በምታደርግበት ቀን የተወሰኑት ወድቀው ጀሀነም ሲገቡ የቀሩት ደግሞ ጀነት ይገባሉ፡፡ እኔ የአንተ ባሪያህ ከየትኛው ወገን ይሆን የምሆነው?' ይህን ካለ በኋላ ስለ ጀሀነም የሚናገር የቁርአን አንቀፅ ሲያነብ ሰማሁት፡፡ ከዚያም ረዥም ትንፋሽ ሲያወጣ ከሰማሁት በኋላ ፀጥታ ሰፈነ። ምን እንደተፈጠረ ለማወቅ ጓጓሁ፡፡ ለራሴም:- 'ይህ ወጣት ያለበትን ቤት በሚገባ እስካላየሁት ድረስ የተፈጠረውን ነገር ሲነጋ መስማቴ አይቀርም:: አሁን ወደ ቤቴ ልግባ' በማለት ወደዚያው አመራሁ፡፡
ነግቶ ወደዚያ ስፍራ ስሄድ ከቤቱ በር ላይ የሰው አስከሬን ተመለከትኩ፡፡ ምን እንደተፈጠረ ስጠይቅም እናቱ እንዲህ አለችኝ፡-
የሞተው የእኔ ልጅ ነው፡፡ ከነብዩ ﷺ ጋር የሚያያዝ የዘር ሀረግ አለው፡፡ ጨለማው ያዝ ካደረገ ጀምሮ እስኪነጋ ድረስ ሲሰግድና ሲያለቅስ ያነጋል፡፡ ያለውን ነገር ደግሞ ቀኑን ሙሉ ለድሆች ሲመፀውት ይውላል፡፡ ስለ ጀሀነም የሚናገር የቁርዓን አንቀፅ ከሰማ ፈፅሞ መቋቋም ስለማይችል ያለቅሳል፡፡ በዚህ ዓይነት ሲያለቅስ ሌሊት ላይ ወድቆ ሞተ፡፡አለችኝ
.... እኔም እንዲህ አልኳ ት፡-
እንቺ የተከበርሽ ሴት ሆይ! ልጅሽ በቀጥታ ያመራው ወደ ጀነት ነው ምክንያቱም አላህን ፈርቶ ይህን ያክል የሚያነባ ሰው ጀሀነብ ሊገባ አይችልም: በዚህ ዓይነት ሁኔታ ነፍሱን ስቶ የሞተ ሰው እንዴት ጀሀነም ይገባል? አላህን አመስግኚው።'አልኳት
አሏህ ጀሀነምን ፈርተዉ ከሚያለቅሱ ..ጀነትን ከሚለምኑ አቢድ ዛሂድ ያረገን ዘንድ አላህን እንማፀነዋለን....
join👇👇👇
t.me/IslamisUniverstiy_public_group
t.me/IslamisUniverstiy_public_group
✍ አሚር ሰይድ
መንሱር ኢብን አማር እንዲህ በማለት ተናግሯል፦ “አንድ ሌሊት የነጋ መስሎኝ ከቤቴ ወጥቼ ስሄድ ንጋቱ አለመቀረቡን ተገነዘብኩ፡፡ ከዚያም በአንድ ሰው ቤት አጠገብ ሳልፍ አንድ ወጣት ምርር ብሎ እያለቀሰ ጌታውን እንዲህ በማለት ሲማፀን ሰማሁት፡-
ጌታዬ ሆይ! እኔ ብዙ ሀጢያቶችን ፈፅሜያለሁ፡፡ በዚህም ድርጊቴ ራሴን መቀመቅ አውርጃለሁ። ዓላማዬ ያንተን ትዕዛዝ መጣስ አልነበረም። ሆኖም ግን ነፍሴ አሸነፈችኝ፡፡ ምንም እንኳን እኔ እራሴን ብበድልና መጥፎ ድርጊቶችን ብፈፅምም አንተ ግን ለዚህ ድርጊቱ የወሰድክብኝ ብቀላ የለም፡፡ በዚህ ቻይነትህና ይቅር ባይነትህም ተዘናግቼ ተወሰድኩ። ሀጢያቶቼንም የሠራኋቸው ባለማወቅ ነው፡፡ አሁን ግን መሳሳቴን ተገነዘብኩ። የምትቀጣኝ ከሆነ ምን ይውጠኛል? ወዮልኝ ለራሴ! ጌታዬ ሆይ! ባሮችህን ሁሉ በሲራጥ ድልድይ ላይ እንዲያልፉ በምታደርግበት ቀን የተወሰኑት ወድቀው ጀሀነም ሲገቡ የቀሩት ደግሞ ጀነት ይገባሉ፡፡ እኔ የአንተ ባሪያህ ከየትኛው ወገን ይሆን የምሆነው?' ይህን ካለ በኋላ ስለ ጀሀነም የሚናገር የቁርአን አንቀፅ ሲያነብ ሰማሁት፡፡ ከዚያም ረዥም ትንፋሽ ሲያወጣ ከሰማሁት በኋላ ፀጥታ ሰፈነ። ምን እንደተፈጠረ ለማወቅ ጓጓሁ፡፡ ለራሴም:- 'ይህ ወጣት ያለበትን ቤት በሚገባ እስካላየሁት ድረስ የተፈጠረውን ነገር ሲነጋ መስማቴ አይቀርም:: አሁን ወደ ቤቴ ልግባ' በማለት ወደዚያው አመራሁ፡፡
ነግቶ ወደዚያ ስፍራ ስሄድ ከቤቱ በር ላይ የሰው አስከሬን ተመለከትኩ፡፡ ምን እንደተፈጠረ ስጠይቅም እናቱ እንዲህ አለችኝ፡-
የሞተው የእኔ ልጅ ነው፡፡ ከነብዩ ﷺ ጋር የሚያያዝ የዘር ሀረግ አለው፡፡ ጨለማው ያዝ ካደረገ ጀምሮ እስኪነጋ ድረስ ሲሰግድና ሲያለቅስ ያነጋል፡፡ ያለውን ነገር ደግሞ ቀኑን ሙሉ ለድሆች ሲመፀውት ይውላል፡፡ ስለ ጀሀነም የሚናገር የቁርዓን አንቀፅ ከሰማ ፈፅሞ መቋቋም ስለማይችል ያለቅሳል፡፡ በዚህ ዓይነት ሲያለቅስ ሌሊት ላይ ወድቆ ሞተ፡፡አለችኝ
.... እኔም እንዲህ አልኳ ት፡-
እንቺ የተከበርሽ ሴት ሆይ! ልጅሽ በቀጥታ ያመራው ወደ ጀነት ነው ምክንያቱም አላህን ፈርቶ ይህን ያክል የሚያነባ ሰው ጀሀነብ ሊገባ አይችልም: በዚህ ዓይነት ሁኔታ ነፍሱን ስቶ የሞተ ሰው እንዴት ጀሀነም ይገባል? አላህን አመስግኚው።'አልኳት
አሏህ ጀሀነምን ፈርተዉ ከሚያለቅሱ ..ጀነትን ከሚለምኑ አቢድ ዛሂድ ያረገን ዘንድ አላህን እንማፀነዋለን....
join👇👇👇
t.me/IslamisUniverstiy_public_group
t.me/IslamisUniverstiy_public_group