📌የአሊ ረዐ ለነብዩ ﷺ የነበራቸዉ ፍቅር 📌
✍አሚር ሰይድ
የአላህ መልዕክተኛ ﷺ የተወለዱባትንና የሚወዷትን መካን ለቅቀው ለመሰደድ በተዘጋጁበት ሌሊት ዓሊን (ረ.ዐ) ጠርተው ወደ መዲና እንዲሰደዱ መለኮታዊ መመሪያ የወረደላቸው መሆኑን ገለፁላቸው፡፡ ከዚያም በመቀጠል እርሳቸው ወደ ኋላ እንዲቀሩና መካውያን ከእርሳቸው ዘንድ በአደራ ያስቀመጧቸውን ገንዘብና ንብረት ለየባለቤቶቻቸው ከመለሱላቸው በኋላ እንዲከተሏቸው አሳሰቧቸው፡፡ ምክንያቱም መካ ውስጥ ውድና ዋጋ የሚያወጣ ሀብት ኖሮት ከአላህ
መልዕክተኛ ﷺ ዘንድ ያላስቀመጠ ብዙ አይገኝም ነበርና፡፡ ጠላቶቻቸው እንደዚያ ግድያና ታላቅ አደጋ ሊያደርሱባቸው እየፈለጉ ውድ ንብረቶቻቸውን ከእርሳቸው ዘንድ ማስቀመጣቸው እውነተኛና ታማኝ በመሆናቸው እንጂ በሌላ አልነበረም ሀቢቡና ሙሀመድ ﷺ
የከሀድያኑን እቅድ አስመልክተው የአላህ
መልዕክተኛ ﷺዓሊን (ረ.ዐ) ሲያስጠነቅቋቸው እንዲህ አሉ፡- “ዓሊ ሆይ! ሌሊቱን በመኝታዬ ጋደም በል፡፡ በዚህ መጎናፀፊያዬም ራስህን ሽፍን፡፡ የማትወደው ነገር ይደርስብኛል ብለህ ምንም ፍርሀት እንዳይዝህ፡፡''
ታላቅ በሆነ የእምነት ወኔ የደነደኑት ዓሊ (ረ.ዐ) በአካላቸው ላይ ሊሸቀሸቁ በተዘጋጁ ብዙ ጦሮችና ጐራዴዎች ጥላ ታጅበው እነሆ በነብዩ ﷺ መኝታ ላይ ተኝተዋል፡፡
.....አስፈሪ በሆነ ቁጣና እልህ እየተደናፉ የመጡት አጋሪዎች የአላህን መልዕክተኛ ﷺ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ገድለው ለመገላገል ወስነው ይጠባበቃሉ። ሌሊቱ ሊገባደድ አቅራቢያ በሩን በኃይል በርግደው ወደ ውስጥ ሲዘልቁ የነብዩን ﷺ መጎናፀፊያ ለብሰው የተኙት ዓሊ (ረ.ዐ) መሆናቸውን ተመለከቱ፡፡ በንዴት እሳት ለብሰውም እንዲህ በማለት ጮሁ
"ዓሊ ሆይ! የአጎትህ ልጅ የት ነው ያለው?"
"እኔ አላውቅም፡፡ ይህን ጉዳይ በተመለከተም ምንም መረጃ የለኝም፡፡ እኔ እርሳቸውን ስከታተል አልቆየሁም፡፡ እንደሚመስለኝ ግን ከመካ ውጣልን ያላችኋቸው በመሆኑ መካን ሳይለቁ አይቀሩም፡፡”አሉ አሊ ረዐ
....ይህን እንደሰሙ አሊን እየተራገሙና እያመናጨቁ ወስደው በመስጂደል ሀረም ውስጥ አሰሯቸው፡ ሆኖም ብዙም ሳይቆዩ ፈታቷቸው፡፡
አሊ ረዐ ዉዴታቸዉ በነብዩ ﷺ መተኛ ላይ ሁነዉ በነብዩ ﷺ ላይ የመጣዉ ሞትን ለመቀበል ተዘጋጅተዉ ነበር ሀቢቡና ሙሀመድ ﷺ አሊ ረዐ ከሚወዷቸዉ ዉዴታ ይቼ የዱቄት ያህል ትንሿ ነች ከዚህ በላይ አሊ ረዐ ሀቢቡና ሙሀመድ ﷺ ይወዷቸዉ ነበር...,
በቀንም በማታም ሶሉ አላሀቢቡና ሰይዱና
ሙሀመድ ﷺ ﷺ💚💚💚💚
join👇👇👇
t.me/IslamisUniverstiy_public_group
t.me/IslamisUniverstiy_public_group
✍አሚር ሰይድ
የአላህ መልዕክተኛ ﷺ የተወለዱባትንና የሚወዷትን መካን ለቅቀው ለመሰደድ በተዘጋጁበት ሌሊት ዓሊን (ረ.ዐ) ጠርተው ወደ መዲና እንዲሰደዱ መለኮታዊ መመሪያ የወረደላቸው መሆኑን ገለፁላቸው፡፡ ከዚያም በመቀጠል እርሳቸው ወደ ኋላ እንዲቀሩና መካውያን ከእርሳቸው ዘንድ በአደራ ያስቀመጧቸውን ገንዘብና ንብረት ለየባለቤቶቻቸው ከመለሱላቸው በኋላ እንዲከተሏቸው አሳሰቧቸው፡፡ ምክንያቱም መካ ውስጥ ውድና ዋጋ የሚያወጣ ሀብት ኖሮት ከአላህ
መልዕክተኛ ﷺ ዘንድ ያላስቀመጠ ብዙ አይገኝም ነበርና፡፡ ጠላቶቻቸው እንደዚያ ግድያና ታላቅ አደጋ ሊያደርሱባቸው እየፈለጉ ውድ ንብረቶቻቸውን ከእርሳቸው ዘንድ ማስቀመጣቸው እውነተኛና ታማኝ በመሆናቸው እንጂ በሌላ አልነበረም ሀቢቡና ሙሀመድ ﷺ
የከሀድያኑን እቅድ አስመልክተው የአላህ
መልዕክተኛ ﷺዓሊን (ረ.ዐ) ሲያስጠነቅቋቸው እንዲህ አሉ፡- “ዓሊ ሆይ! ሌሊቱን በመኝታዬ ጋደም በል፡፡ በዚህ መጎናፀፊያዬም ራስህን ሽፍን፡፡ የማትወደው ነገር ይደርስብኛል ብለህ ምንም ፍርሀት እንዳይዝህ፡፡''
ታላቅ በሆነ የእምነት ወኔ የደነደኑት ዓሊ (ረ.ዐ) በአካላቸው ላይ ሊሸቀሸቁ በተዘጋጁ ብዙ ጦሮችና ጐራዴዎች ጥላ ታጅበው እነሆ በነብዩ ﷺ መኝታ ላይ ተኝተዋል፡፡
.....አስፈሪ በሆነ ቁጣና እልህ እየተደናፉ የመጡት አጋሪዎች የአላህን መልዕክተኛ ﷺ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ገድለው ለመገላገል ወስነው ይጠባበቃሉ። ሌሊቱ ሊገባደድ አቅራቢያ በሩን በኃይል በርግደው ወደ ውስጥ ሲዘልቁ የነብዩን ﷺ መጎናፀፊያ ለብሰው የተኙት ዓሊ (ረ.ዐ) መሆናቸውን ተመለከቱ፡፡ በንዴት እሳት ለብሰውም እንዲህ በማለት ጮሁ
"ዓሊ ሆይ! የአጎትህ ልጅ የት ነው ያለው?"
"እኔ አላውቅም፡፡ ይህን ጉዳይ በተመለከተም ምንም መረጃ የለኝም፡፡ እኔ እርሳቸውን ስከታተል አልቆየሁም፡፡ እንደሚመስለኝ ግን ከመካ ውጣልን ያላችኋቸው በመሆኑ መካን ሳይለቁ አይቀሩም፡፡”አሉ አሊ ረዐ
....ይህን እንደሰሙ አሊን እየተራገሙና እያመናጨቁ ወስደው በመስጂደል ሀረም ውስጥ አሰሯቸው፡ ሆኖም ብዙም ሳይቆዩ ፈታቷቸው፡፡
አሊ ረዐ ዉዴታቸዉ በነብዩ ﷺ መተኛ ላይ ሁነዉ በነብዩ ﷺ ላይ የመጣዉ ሞትን ለመቀበል ተዘጋጅተዉ ነበር ሀቢቡና ሙሀመድ ﷺ አሊ ረዐ ከሚወዷቸዉ ዉዴታ ይቼ የዱቄት ያህል ትንሿ ነች ከዚህ በላይ አሊ ረዐ ሀቢቡና ሙሀመድ ﷺ ይወዷቸዉ ነበር...,
በቀንም በማታም ሶሉ አላሀቢቡና ሰይዱና
ሙሀመድ ﷺ ﷺ💚💚💚💚
join👇👇👇
t.me/IslamisUniverstiy_public_group
t.me/IslamisUniverstiy_public_group