ከእራስህ ተነስ!
"የመውደድ አቅም ካለህ አስቀድመህ እራስህን ውደድ።" - Charles Bukowski
ማንንም ለመውደድ ጅማሬያችን እራሳችንን መውደዳችን ነው፤ ማንንም ለማክበራችን መሰረታችን እራሳችንን ማክበራችን ነው፤ ማንንም አስደሳች ለማድረግ ቀዳሚው እራሳችንን ማስደሰት መቻላችን ነው፤ በማንም ዘንድ ተቀባይነት ለማግኘታችን ዋስትናው እራሳችንን መቀበላችን ነው። ውጪውን ለማስተካከል ከመሔድህ በፊት አንተ ጋር ምንም መስተካከል የሚገባው፣ መታነፅ ያለበትና መሻሻል የሚኖርበት ነገር እንደሌለ እርግጠኛ ሁን። አመለካከትህ፣ አረዳድህ፣ የእምነት ደረጃህ፣ እውቀትህ፣ የማስተዋል አቅምህ፣ የመረዳት ችሎታህ ሁሉ እንከን አለባ እንደሆነ እርግጠኛ ሁን። ውጪው ላይ ጣትን ከመቀሰር በተሻለ እራስን መመልከት እራስን መረዳትና ለእራስ እምነት ታምኖ መገኘት ይቀድማል። እድሎች ቢያመልጡህ ተጎጂው አንተ ነህ፤ ከእራስህ ማግኘት የምትችለውንም ከሰዎች እየፈለክ፣ እየጠበክና በየቦታው እያሳደድክ ብትቆይ የምትጎዳው እራስህ ነው።
አዎ! ጀግናዬ..! ከእራስህ ተነስ! ከእራስህ ጀምር፣ መውደዱን ከእራስህ ጀምር፣ ማክበሩን ከእራስህ ጀምር፣ ጊዜ መስጠቱን፣ ማዳመጡን፣ መንከባከቡን፣ መደገፉን፣ ማነቃቃቱን ከእራስህ ጀምር። ለእራስህ የማትሰጠውን ፍቅርና ክብር ለማንም መስጠት እንደማትችል እወቅ። በእራስህ ደስተኛ ሳትሆን ሌላውን ደስተኛ አደርጋለሁ ብለህ አታስብ፤ እራስህን ሳትመራ፣ ፍላጎቶችህን ሳትቆጣጠር፣ ስሜትህ ላይ ሳትሰለጥን ሰዎችን እመራለሁ፣ ድርጅትን አስተዳድራለሁ፣ ሀገርን እረከባለሁ፣ ትውልድንም አንፃለሁ ብለህ አታስብ። ማንም ሰው የሌለውን ነገር ሊሰጥ አይችልም። ትርጉም ሰጪው፣ አትራፊውና ውጤታማው ህይወት የሚመጣው ሌላ ከማንም ሳይሆን ከእራሱ ከባለቤቱ ነው። ክፍተትህን እንዲሞሉልህ የምትጠብቃቸው ሰዎች እራሳቸው የእራሳቸው ክፍተትና ድክመት ይኖርባቸዋል። ጫማህ ቢጠብህ እግርህን እንደማታስተካክለው ሁሉ ነገሮች እንዳሰብከው ካለሆኑ ከነገሮቹ በላይ ለነገሮቹ ያለህን አመለካከት መርምረህ አስተካክል።
አዎ! ጊዜያዊ የአመለካከት ስህተትህ የእድሜህን እኩሌታ በጥበቃና በወቀሳ እንዲጨርሰው አታድርግ። ለእራስህ መታመን እየተቸገርክ፣ የግል አቋም መገንባት ላይ እየተንገጫገጭክ፣ ወደፊት የሚመሩህን መርሆችን ወደኋላ እየጣልክ፣ እራስህን የበታች መጪዎቹን የበላይ፣ እራስህን ደካማ ገና ወደህይወትህ የሚገቡ ሰዎችን ጠንካሮች አድርገህ ማሰብ እስካላቆምክ ድረስ የምትጠብቀውን ውጤት በፍፁም ልታገኝ እንደማትችል እወቅ። እራስህን ተቀበል፣ ክፍተቶችህን ሙላ፣ ድክመትህን አርም፣ ወደህይወትህ እንዲገቡ የምትጠብቃቸው ሰዎች ሊያደርጉልህ የሚችሉትን ነገር በጥቂቱም ቢሆን ለእራስህ አድርግ። መውደድ፣ ማፍቀር፣ ማክበር፣ መንከባከብ እችላለሁ ብለህ የምታስብ ከሆነ በቅድሚያ ለእራስህ ከማድረግ ተነስ።
"የመውደድ አቅም ካለህ አስቀድመህ እራስህን ውደድ።" - Charles Bukowski
ማንንም ለመውደድ ጅማሬያችን እራሳችንን መውደዳችን ነው፤ ማንንም ለማክበራችን መሰረታችን እራሳችንን ማክበራችን ነው፤ ማንንም አስደሳች ለማድረግ ቀዳሚው እራሳችንን ማስደሰት መቻላችን ነው፤ በማንም ዘንድ ተቀባይነት ለማግኘታችን ዋስትናው እራሳችንን መቀበላችን ነው። ውጪውን ለማስተካከል ከመሔድህ በፊት አንተ ጋር ምንም መስተካከል የሚገባው፣ መታነፅ ያለበትና መሻሻል የሚኖርበት ነገር እንደሌለ እርግጠኛ ሁን። አመለካከትህ፣ አረዳድህ፣ የእምነት ደረጃህ፣ እውቀትህ፣ የማስተዋል አቅምህ፣ የመረዳት ችሎታህ ሁሉ እንከን አለባ እንደሆነ እርግጠኛ ሁን። ውጪው ላይ ጣትን ከመቀሰር በተሻለ እራስን መመልከት እራስን መረዳትና ለእራስ እምነት ታምኖ መገኘት ይቀድማል። እድሎች ቢያመልጡህ ተጎጂው አንተ ነህ፤ ከእራስህ ማግኘት የምትችለውንም ከሰዎች እየፈለክ፣ እየጠበክና በየቦታው እያሳደድክ ብትቆይ የምትጎዳው እራስህ ነው።
አዎ! ጀግናዬ..! ከእራስህ ተነስ! ከእራስህ ጀምር፣ መውደዱን ከእራስህ ጀምር፣ ማክበሩን ከእራስህ ጀምር፣ ጊዜ መስጠቱን፣ ማዳመጡን፣ መንከባከቡን፣ መደገፉን፣ ማነቃቃቱን ከእራስህ ጀምር። ለእራስህ የማትሰጠውን ፍቅርና ክብር ለማንም መስጠት እንደማትችል እወቅ። በእራስህ ደስተኛ ሳትሆን ሌላውን ደስተኛ አደርጋለሁ ብለህ አታስብ፤ እራስህን ሳትመራ፣ ፍላጎቶችህን ሳትቆጣጠር፣ ስሜትህ ላይ ሳትሰለጥን ሰዎችን እመራለሁ፣ ድርጅትን አስተዳድራለሁ፣ ሀገርን እረከባለሁ፣ ትውልድንም አንፃለሁ ብለህ አታስብ። ማንም ሰው የሌለውን ነገር ሊሰጥ አይችልም። ትርጉም ሰጪው፣ አትራፊውና ውጤታማው ህይወት የሚመጣው ሌላ ከማንም ሳይሆን ከእራሱ ከባለቤቱ ነው። ክፍተትህን እንዲሞሉልህ የምትጠብቃቸው ሰዎች እራሳቸው የእራሳቸው ክፍተትና ድክመት ይኖርባቸዋል። ጫማህ ቢጠብህ እግርህን እንደማታስተካክለው ሁሉ ነገሮች እንዳሰብከው ካለሆኑ ከነገሮቹ በላይ ለነገሮቹ ያለህን አመለካከት መርምረህ አስተካክል።
አዎ! ጊዜያዊ የአመለካከት ስህተትህ የእድሜህን እኩሌታ በጥበቃና በወቀሳ እንዲጨርሰው አታድርግ። ለእራስህ መታመን እየተቸገርክ፣ የግል አቋም መገንባት ላይ እየተንገጫገጭክ፣ ወደፊት የሚመሩህን መርሆችን ወደኋላ እየጣልክ፣ እራስህን የበታች መጪዎቹን የበላይ፣ እራስህን ደካማ ገና ወደህይወትህ የሚገቡ ሰዎችን ጠንካሮች አድርገህ ማሰብ እስካላቆምክ ድረስ የምትጠብቀውን ውጤት በፍፁም ልታገኝ እንደማትችል እወቅ። እራስህን ተቀበል፣ ክፍተቶችህን ሙላ፣ ድክመትህን አርም፣ ወደህይወትህ እንዲገቡ የምትጠብቃቸው ሰዎች ሊያደርጉልህ የሚችሉትን ነገር በጥቂቱም ቢሆን ለእራስህ አድርግ። መውደድ፣ ማፍቀር፣ ማክበር፣ መንከባከብ እችላለሁ ብለህ የምታስብ ከሆነ በቅድሚያ ለእራስህ ከማድረግ ተነስ።