#ሚካኤል ማለት መሓሪ ወመስተሣህል ዕፁብ ማለት ነው። ገብርኤል ማለት አምላክ ወሰብእ ገብር ወአግዓዚ ማለት ነው። ማርያም ማለት መርሕ ለመንግሥተ ሰማያት ማለት ነው ። ዳዊት ማለት ፍቁር ልበ አምላክ ማለት ነው። #ሰሎሞን ማለት መስተሣልም ማለት ነው። #ሳሙኤል ማለት ሰምአኒ እግዚአብሔር ማለት ነው። ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ የጌታን መታጠቂያ ከታጠቀ በኋላ ፍትወት እንስሳዊት ከባሕርይው ጠፍታለች። የሙሴ የቀድሞ ስሙ ምልክአም ነው ። ምልክአም ማለት መልአከ እግዚአብሔር ማለት ነው። #አሮን ማለት ደብር ማለት ነው። #ዘካርያስ ማለት ዝክረ እግዚአብሔር ማለት ነው። ቅዱስ ገብርኤል መጋቤ ሐዲስ ነው ። ቅዱስ ሚካኤል መጋቤ ብሉይ ነው። የእግዚአብሔር መዓቱም ምሕረቱም በእውነት ይደረጋል። በአፀደ ቤተክርስቲያን በመዓልት 600፣ በሌሊት 600 መላእክት ይኖራሉ። ቤተክርስቲያንን ይጠብቃሉ። የእግዚአብሔር ባሕርዩ በዚህ ጊዜ ተገኘ አይባልም። በባሕርይው አስገኝ ምክንያት የለውም። ክርስቶስ ራሱን በመስቀል ሠውቶ አስታርቆናልና ሊቀ ካህናት ይባላል። የእግዚአብሔር ሥልጣኑ የባሕርዩ ነው። ጌታ በተወለደ ጊዜ መላእክትና ኖሎት በአንድ ላይ አመስግነዋል። ቄሱ ከሕዝቡ ኃጢአት ንጹሕ ነኝ ሲል እጁን ይታጠባል።
(መምህር በትረ ማርያም አበባው)
#ኦርቶዶክሳዊ_አእምሮ
(መምህር በትረ ማርያም አበባው)
#ኦርቶዶክሳዊ_አእምሮ