“ኢትዮጵያ አሁን ባለችበት ተከታታይ የፖለቲካ ቀውስ ውስጥ ሆና ምንም አይነት ሀገራዊ ምክክር ማድረግ አትችልም”- ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ
ጥር 14 ቀን 2017(አዲስ ማለዳ)ብሔራዊ መግባባት በሚል ርዕስ ዛሬ በተካሄደው 2ኛው የፓርላማ የዜጎች ፎርም ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን በውይይቱ በርካታ ሀሳብ እና አስተያየት ተስተናግደዋል፡፡
ሀሳባቸውን የሰጡት ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ በበኩላቸው ኢትዮጵያ አሁን ባለችበት ተከታታይ የፖለቲካ ቀውስ እና አለመግባባት እንዲሁም ጦርነት ውስጥ ምን አይነት ሀገራዊ ምክክር ሊደረግ ይችላል ሲሉ ጠይቀዋል፡፡
እንዲሁም የሰላም እና የጸጥታ ጉዳይ ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ ቢሆንም የውይይቱ ዋነኛ መወያያ ርዕስ አለመሆኑ ሊታሰብበት እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡
በተጨማሪም “በትክክል አሁን ባለው የኢትዮጵያ ሁኔታ ውጤታማ የሆነ ሀገራዊ መግባባት አካሂደን የሀገራችንን የወደፊት ተስፋ መቅረጽ በምንችልበት ቁመና ላይ ነው ያለነው” በማለት ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ጠይቀዋል፡፡
ይህን ተከትሎ በአባላቱ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት ፕ/ር መስፍን አርአያ የተነሱት ጥጣቄዎች አግባብነት ያላቸው መሆናቸውን ገልጸው ሀገራዊ ምክክር የሚደረገው በሶስት መንገድ ነው አንደኛውም በግጭት ውስጥም ተሆኖ ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡
አንጻራዊ ሰላም እንደሚያስፈል እና ከመንግስትም ሆነ ከተቋዋሚ አካላት ከሁሉም ህዝቦች ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለውይይት የሚሆን አስቻይ ሁኔታዎችን ፍጠሩልን ሲሉ አሳስበዋል፡፡
ጥር 14 ቀን 2017(አዲስ ማለዳ)ብሔራዊ መግባባት በሚል ርዕስ ዛሬ በተካሄደው 2ኛው የፓርላማ የዜጎች ፎርም ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን በውይይቱ በርካታ ሀሳብ እና አስተያየት ተስተናግደዋል፡፡
ሀሳባቸውን የሰጡት ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ በበኩላቸው ኢትዮጵያ አሁን ባለችበት ተከታታይ የፖለቲካ ቀውስ እና አለመግባባት እንዲሁም ጦርነት ውስጥ ምን አይነት ሀገራዊ ምክክር ሊደረግ ይችላል ሲሉ ጠይቀዋል፡፡
እንዲሁም የሰላም እና የጸጥታ ጉዳይ ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ ቢሆንም የውይይቱ ዋነኛ መወያያ ርዕስ አለመሆኑ ሊታሰብበት እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡
በተጨማሪም “በትክክል አሁን ባለው የኢትዮጵያ ሁኔታ ውጤታማ የሆነ ሀገራዊ መግባባት አካሂደን የሀገራችንን የወደፊት ተስፋ መቅረጽ በምንችልበት ቁመና ላይ ነው ያለነው” በማለት ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ጠይቀዋል፡፡
ይህን ተከትሎ በአባላቱ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት ፕ/ር መስፍን አርአያ የተነሱት ጥጣቄዎች አግባብነት ያላቸው መሆናቸውን ገልጸው ሀገራዊ ምክክር የሚደረገው በሶስት መንገድ ነው አንደኛውም በግጭት ውስጥም ተሆኖ ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡
አንጻራዊ ሰላም እንደሚያስፈል እና ከመንግስትም ሆነ ከተቋዋሚ አካላት ከሁሉም ህዝቦች ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለውይይት የሚሆን አስቻይ ሁኔታዎችን ፍጠሩልን ሲሉ አሳስበዋል፡፡