Addis Maleda - አዲስ ማለዳ


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


ዜና ከምንጩ

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций




በሌሎች ክልሎች ልዩ ኃይልና ታጣቂዎች ሲበተኑ ለትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የተሰጠው መብት ለአሁኑ ቀውስ መነሻ ነው- ኢዜማ

ሐሙስ ሚያዝያ 10 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) ባለፉት ጥቂት ቀናት በአላማጣ እና አከባቢው የሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ታጣቂዎች "የኃይል እርምጃ እየወሰዱ" መሆኑን ተከትሎ መንግሥት “ጦርነት የሚጎስመውን የሕወሓት ስብስብ በፕሪቶሪያው ሥምምነት መሠረት ትጥቅ እንዲፈታ” በማድረግ ሕግ እና ሥርዓት እንዲያስከብር ሲል የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ፓርቲ አሳሰበ።

አዲስ ማለዳ ከፓርቲው መግለጫ እንደተመለከተችው፤ ቡድኑን [ህወሓት] ትጥቅ የማስፈታት ጉዳይ ዛሬም ቢሆን ከአጎራባች ክልሎች አልፎ ለአገር ሉዓላዊነት ጠንቅ ሊሆን እንደሚችል መታሰብ ይኖርበታል ብሏል።

መንግስት ቡድኑ በፈረመው ሥምምነት መሠረት በሰላሳ ቀናት ውስጥ መሣሪያ አስረክቦ ወደ ሰላም አስተሳሰብ እንዲመጣ ሊደረግ ሲገባ ይበልጥ እራሱን አደራጅቶ ዛሬም ንፁሀን ዜጎችን ለመከራ ለእንግልት እና ከቀያቸው ተፈናቅለው ሜዳ ላይ እንዲወድቁ እያደረገ ይገኛል ሲል ኢዜማ ህወሓትን ተችቷል።

ኢ-ሕገ መንግስታዊ አደረጃጀት የነበረው የክልል ልዩ ኃየል ትጥቅ በማስፈታት መዋቅሩ እንዲፈርስ ሲደረግ፤ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ህጋዊ እውቅና የሌለው "ፓርቲ" ከመሆኑ ባሻገር “መሣሪያ የታጠቁ የራሱ ኃይሎች ያሉት ብቸኛ ስብስብ” ነው ሲል ኢዜማ መግለጹን አዲስ ማለዳ ከመግለጫው ተመልክታለች።

በተለይ በሌሎች ክልሎች ያሉ ልዩ ኃይሎች እና ታጣቂዎች ሁሉ ፈርሰው ወጥ በሆነ የጸጥታ አመራር ሥር ሆነው እንዲንቀሳቀሱ ቢደረግም “ለጊዜያዊ አስተዳደሩ ልዩ መብት በማጎናፀፍ በሌሎች ክልሎች በሌለ እና ፈጽሞ በማይታሰብ መልኩ ታጣቂ ኃይል የማሠማራት መብት በመሰጠቱ” አሁን በአማራ ክልል ያለው ቀውስ እንዲቀጣጠል መነሻ መሆኑን ጠቁሟል።

ሕወሓት አንዴ "ትጥቅ ፈትተናል” ሌላ ጊዜ ደግሞ "የምንፈልገውን ለማድረግ በቂ ኃይል አለን” በማለት ከፕሪቶሪያው ሥምምነት ባፈነገጠ መልኩ "ሲያምታቱ"፤ የፈደራል መንግሥቱ እያሳየ ያለው ኃላፊነቱን በአግባቡ ያለመወጣት፣ ደካማ መረጃ አሰጣጥ፣ ቸልተኝነት እና መሰል ግዴለሽነት የተሞላ ተግባር በእጅጉ የሚያሳዝነን፣ በፅኑ የምናወግዘውም ነው” ብሏል።

አሁን የተከሰተውን አለመረጋጋት እና ችግር ለመፍታት የፌደራል መንግስት “የአንበሳውን ድርሻ” እንደሚወስድ የገለጸው ኢዜማ፤ መንግሥት የፕሪቶሪያውም ሥምምነት ተከብሮ በአስቸኳይ ትጥቅ እንዲፈታ እና “ጦርነት የሚጎስመውን ስብስብም ሥርዓት እንዲያሲዝ” በማለት ፓርቲው አሳስቧል።

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ እንድገለጸው ይኽ መሆን ካልቻለ “ህወሓት ሰሞኑን የጀመረው ዳግም ወረራ በዜጎች ሕይወት፣ አካል እና ንብረት ላይ ለሚደርሰው ውድመት እና ምስቅልቅል መንግሥት ሙሉ ኃላፊነቱን የሚወስድ ይሆናል”።

የአማራ እና ትግራይ ክልሎች ከሚወዛገቡባቸው የራያ አካባቢዎች አንዱ በሆነው ራያ አላማጣ ወረዳ በትጥቅ የተደገፈ ግጭት መጀመሩን አዲስ ማለዳ ከተለያዩ ወገኖች የሚሰጡ መረጃዎችን እያቀረበች መዘገቧ አይዘነጋም።

"የህወሓት ኃይሎች ጀምረውታል" ከተባለው ጥቃት ተከትሎ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር በዚህ ጉዳይ ላይ “ህወሓት እጁ የለበትም” ያለ ሲሆን በአንጻሩ የአማራ ክልል መንግስት “ህወሓት አራተኛ ዙር ወረራ ፈጽሞብናል” በማለት የሚቃረን መግለጫ ማውጣታቸው አይዘነጋም።
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram
| Facebook | YouTube | X | www.addismaleda.com | 0961414141




የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተ ክርስቲያን እድሳት በገንዘብ እጥረት ሳቢያ እየተጓተተ ሲሆን ለማጠናቀቅ 85 ሚልየን ብር ያስፈልጋል

ሐሙስ ሚያዝያ 10 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) በኢትዮጵያ የፓትሪያርክ ሹመት የሚፈጸምበቱ በቸኛ ስፍራ የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተ ክርስቲያን የህንፃ እድሳት እንዲጠናቀቅ 85 ሚሊየን ብር እንደሚያስፈልግ ተገለጸ።

የቤተ ክርስቲያኗ አስተዳደር ሰበካ ጉባዔ ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ የህንፃ እድሳቱ እስካሁን 75 በመቶ የተጠናቀቀ ሲሆን 90 ሚሊዮን ብር ገደማ እንደፈጀ ተጠቁሟል።

የቤተ ክርስቲያኗ የእድሳት ሂደት ለ16 ወራት ያህል ጥናት ሲደረግበት ቆይቶ "በቅርስ እድሳት ልምድ ካለው" ቫርኔሮ ከተባለ ድርጅት ጋር በ172 ሚሊዮን ብር የሥራ ውል መጀመሩን አዲስ ማለዳ ከመግለጫው ተረድታለች።

በዚህ የእድሳት ሂደት ከውጪ ለሚገቡ እቃዎች የውጭ ምንዛሪ እጥረት እንዲሁም ቤተ ክርስቲያኗ ከፍተኛ ገቢ ታገኛለች በሚል ግምት ህብረተሰቡ ለመርዳት ፍቃደኝነት አለማሳየታቸው እንደ ተግዳሮት ተጠቅሰዋል። ድጋፍ የሚሰበሰብባቸው መንገዶችም እንደቀጠሉ ነው።

እድሳቱ ከተጀመረ አንድ ዓመት ከግማሽ ገደማ ያስቆጠረ ሲሆን መጋቢት 30 ቀን 2016 እንደሚጠናቀቅ ታቅዶ የነበረ ቢሆንም በገንዘብ እጥረት ሳቢያ ለሦስት ወራት እንዲራዘም መደረጉን አዲስ ማለዳ ከታደመችበት መግለጫ ሰምታለች።

የቤተ ክስርስቲያኗ አስተዳዳሪ ሊቀ ስልጣን ቆሞስ አባ ሲራክ አድማሱ እንደገለጹት እድሳቱ ከኢትዮጵያ ቅርስና ጥበቃ ህጋዊ ፈቃድ አግኝቶ የሚታደስ መሆኑን ጠቁመው በግንባታ ሂደት ያጋጠመ ችግር የለም ብለዋል።

የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተ ክርስቲያን በ1924 ከተመሰረተ ጀምሮ ከ90 ዓመታት በላይ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram
| Facebook | YouTube | X | www.addismaleda.com | 0961414141




የሠራተኞች ጥያቄ የሚቀርብበት ዓመታዊው የሠራተኞች ቀን (ሜይዴይ) በአደባባይ እንደማይከበር ተገለጸ

ሐሙስ ሚያዝያ 10 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) በየዓመቱ ሚያዚያ 23 ቀን ሠራተኞች ጥያቄዎቻቸውን እና ብሶታቸውን በአደባባይ የሚያሰሙበትና የሚያከብሩት ዓለም አቀፍ የሠራተኞች ቀን (ሜይዴይ) ለሁለተኛ ጊዜ በአደባባይ እንደማይከበር የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) አስታወቀ።

የዘንድሮ አከባበርን በተመለከተ ኢሠማኮ ከኢንዱስትሪ ፌዴሬሽን አመራሮች ጋር ውይይት ማድረጋቸውምን አዲስ ማለዳ ከኮንፌደሬሽኑ ያገኘችው መረጃ ያመላክታል።

በዚህም በኢትዮጵያ ለ49ኛ ጊዜ በዓለም ደረጃ ደግሞ ለ135ኛ ጊዜ የፊታችን ሚያዝያ 23 ቀን 2016 የሚከበረው በዓል "የአገሪቱን አጠቃላይ ሁኔታ በማገናዘብ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ስር ያሉ ከባቢዎችንም ከግምት በመክተት እንደ ባሕር ዳር፣ ኮምቦልቻና ፊንፊኔ ዙሪያ ካሉት ውጪ" በአዳራሽ ውስጥ ለማክበር ተወስኗል ተብሏል።

ባለፈው ዓመትይ 48ኛው የሠራተኞች ቀን በዓልን ኢሠማኮ በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ እንዲሁም በክልሎች በሰላማዊ ሰልፍ ለማክበር ቢያቅድም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጸጥታ ቢሮ መከልከሉ አይዘነጋም።

ዘንድሮ በአዳራሽ ይከበራል በተባለው ዝግጅት በሠራተኛው በኩል ምላሽ ለሚነሱ ጥያቄዎች የመንግሥት ተወካዮች ምላሽ እንደሚሰጡ ኮንፌዴሬሽኑ ገልጿል።

እንዲሁም የኢሠማኮ ፕሬዝዳንት ካሳሁን ፎሎ የኢሰማኮ ጠቅላይ ምክር ቤት ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ለመገናኘት የሚጠይቅ ደብዳቤ መጻፉንና ምላሽ እየተጠበቀ መሆኑ ተጠቁመዋል።

በአንጻሩ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን አመራሮች ነሐሴ 24 ቀን 2015 ለመጀመሪያ ጊዜ ከጠቅላይ ሚኒስቴር ዐቢይ አሕመድ ጋር ባደረጉት ውይይት ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል፣ የደመወዝ ግብር ቅነሳ እንዲሁም ለዓመታት የተቋረጠው የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አማካሪ ቦርድ ሥራ እንዲጀምር ተጠይቀው ነበር።
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram
| Facebook | YouTube | X | www.addismaleda.com | 0961414141






በ15 ሰዓታት ውስጥ ከ1 ነጥብ 6 ሚልየን ብር በላይ አስመልሻለሁ ሲል የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታወቀ

ረቡዕ ሚያዝያ 9 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ15 ሰዓታት ውስጥ 1 ሚሊየን 600 ሺህ 479 ብር ያላግባብ ከተወሰደበት ገንዘብ ላይ ማስመለሱን ገለጸ።

ባንኩ ካወጣው መረጃ አዲስ ማለዳ እንደተመለከተችው እስከ ትላንት ድረስ 95 በመቶ ማለትም ብር 762 ሚልየን 941 ሺህ 341 አስመልሶ ነበር። ዛሬ ዘጠኝ ሰዓት ገደማ ላይ እንዳስታወቀው ደግሞ 95 ነጥብ 4 በመቶ ወይም ብር 764 ሚልየን 567 ሺህ 820 የሚሆነውን አስመልሷል።

ባንኩ ከሲስተም ማሻሻያ ሥራ ጋር በተገናኘ መጋቢት 7 ቀን 2016 በተፈጠረ ችግር ምክንያት ብር 801 ሚሊየን 417 ሺህ 747 ከ81 ሳንቲም ያለአግባብ ተወስዶብኛል ማለቱ ይታወሳል።

በዚህም በተደጋጋሚ ካደረጋቸው ጥሪዎች እና ማስጠንቀቂያዎች በኋላ በአሁን ሰዓት 95 ነጥብ 4 በመቶውን እንዳስመለሰ አስታውቋል።

ቀሪውን 36 ሚሊየን 848 ሺህ 584 ብር ለማስመለስ እየተሰራ ነውም ተብሏል።
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram
| Facebook | YouTube | X | www.addismaleda.com | 0961414141


#ተጨማሪ #updates
ህወሓት በአማራ ክልል ላይ “በሙሉ አቅሙ” ወረራ መፈጸም ጀምሯል- የአማራ ክልላዊ መንግስት

ረቡዕ ሚያዝያ 09 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ከስህተቱ መማር “የተሳነው” ሕዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህ.ወ.ሓ.ት) “የፕሪቶሪያውን ስምምነት ሙሉ በሙሉ በመጣስ ለአራተኛ ዙር ሕዝባችን ላይ ወረራ ፈፅሟል” በማለት አስታወቀ።

አዲስ ማለዳ የተመለከተችው የክልሉ መንግስት መግለጫ መጋቢት 16 ቀን 2016 “በርካሽ ፖለቲካዊ ብያኔና ፍረጃ በጊዜያዊ አሥተዳደሩ ካቢኔ አማካኝነት የአማራ ክልል ተማሪዎችን መማሪያ መጽሐፍ እንደ ሰበብ ተጠቅሞ በይፋ ጦርነት” አውጇል፤ “በሙሉ አቅሙ ወደ ጦርነት ገብቷል”... https://addismaleda.com/archives/36472
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram
| Facebook | YouTube | X | www.addismaleda.com | 0961414141


#updates #ተጨማሪ
"የአማራ ታጣቂዎች" ያቋቋሟቸውን አስተዳደሮች ለማፍረስ ከፌደራል መንግስት ጋር ተስማምተናል ሲል የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አስታወቀ

ማክሰኞ ሚያዝያ 08 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) በምዕራብ ትግራይ በፀለምቲ አካባቢ እና በደቡብ ትግራይ አንዳንድ አካባቢዎች በአማራ ታጣቂዎች የተቋቋሙትን አስተዳደሮች ለማፍረስ የፌዴራል መንግስት እና የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ከስምምነት ላይ ደርሰዋል ሲሉ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ምክትል ኃላፊ ታደሰ ወረደ ገለጹ።

አዲስ ማለዳ ዛሬ ከሰጡት መግለጫ እንደሰማችው “የመጀመሪያው እርምጃ በየአካባቢው የታጠቁ ቡድኖችን ማፍረስ እና የተቋቋሙትን ህገ-መንግስታዊ ያልሆኑ አስተዳደሮችን ማፍረስ ነው” ያሉት ጀነራል ታደሰ ወረደ፤
"የፍትህ ስርዓቱን ወደነበረበት መመለስ" በተከታይነት ይሰራል ብለዋል።

ጄኔራሉ የታጠቁ ሃይሎች ከፌዴራል ሃይሎች ጋር መጠነኛ ግጭት በመፍጠር ሂደቱን እያስተጓጎሉ መሆናቸውንም አብራርተው የፕሪቶሪያ ስምምነት ግጭት እንዳያገረሽ በሚከላከል መልኩ ተግባራዊ ይደረጋል ሲሉ ገልጸዋል።

የጊዜያዊ አስተዳደሩ ምክትል ኃላፊ እንደገለጹት የፕሪቶሪያ ስምምነት የግዛትን ጨምሮ ሁሉም አለመግባባቶች በህገ መንግስቱ መሰረት መፈታት እንዳለባቸው መደንገጉን አስታውሰዋል።

በራያ አላማጣ አካባቢ የህወሓት ታጣቂዎች ወረራ መፈጸማቸው እየተዘገበ መሆኑን ተከትሎ ነው ይኽ መግለጫ በዛሬው ዕለት መሰጠቱን አዲስ ማለዳ ከክልሉ ቴሌቭዥን ያገኘችው መረጃ ያመለክታል።
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram
| Facebook | YouTube | X | www.addismaleda.com | 0961414141


የህወሓት ታጣቂዎች ወረራ ፈጽመዋል ቢባልም የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ህወሓት የለበትም ብሏል

👉🏿 አብን አጋጣሚውን "ይህ በራያ ብቻ የማይቆም ይልቁንም የሁሉ ነገር መፍረሻና ማፍረሻ" ነው ብሎታል


ማክሰኞ ሚያዝያ 8 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር በራያ አላማጣ አካባቢዎች "የህወሓት ታጣቂዎች" በፈጸሙት ጥቃት የተኩስ ልውውጥ መጀመሩ ቢዘገብም ችግሩ “በአማራና ትግራይ ክልል አስተዳደር መካከል አይደለም” ብሏል።

የፕሪቶሪያው ስምምነት እንዲተገበር ለመጠየቅ በራያ አካባቢዎች ቅዳሜና እሁድ የተካሄደውን ሰልፍ ተከትሎ የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ኃይሎች ከፈቱት በተባለው ጥቃት የተኩስ ልውውጥ መጀምሩን ነዋሪዎች እና የአካባቢውን ባለስልጣናት ዋቢ ያደረጉ ዘገባዎችን አዲስ ማለዳ ተመልክታለች።

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) በበኩሉ ህወሓት “አራተኛ ዙር በሕዝባችን ላይ ወረራ ፈፅሟል” ሲል ትናንት ማምሻውን ባወጣው መግለጫ ከሷል።

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው "በደቡብ ትግራይ እና በሌሎች የትግራይ ግዛቶች የተፈጠረው ግጭት በፌደራል መንግስትና በጊዜያዊ አስተዳደሩ ወይም በህወሓት፤ አሊያም በአማራ እና በትግራይ ክልል አስተዳደሮች መካከል የተፈጠረ አይደለም" በማለት ማጋራታቸውን አዲስ ማለዳ ተመልክታለች።

የአማራ ህዝብ “የቡድኑ ወረራ ቀጥተኛ ሰለባ እና ገፈት ቀማሽ ነው” ያለው አብን፤ የፌዴራልና የአማራ ክልል መንግስታትም በሕዝብ ላይ “የተቃጣውን የጥፋት ወረራ” በአስቸኳይ እንዲያስቆሙ ጥሪውን አቅርቧል።

ጌታቸው ረዳ አክለውም የፕሪቶሪያውን ስምምነት የሚገጥሙትን ተግዳሮቶች ለመፍታት በአዲስ አበባ ስብሰባ ላይ መሆናቸውን ጠቁመው፤ "ስምምነቱን ተግባራዊ ለማድረግ የሚሰሩ ስራዎችን ለማደናቀፍ የሚፈልጉ አካላት የፈጸሙት ነው" ብለዋል።

እንዲሁም ይኽ ክስተት ስምምነቱ ላይ ተጽዕኖ እንደሚኖረው አያጠያይቅም ያሉት ጌታቸው፤ ሰላምና ንግግር ብቸኛው መንገድ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

የአማራ ሕዝባዊ ንቅናቄ እንደገለጸው መንግስት እየተፈጸመ የሚገኘውን ጥቃት በዝምታ የሚመለከት ከሆነና "ሕህዝባችን ስርአቱን አምኖ ችግሮች ሁሉ በሕግ አግባብ ይፈታሉ የሚል ቀናኢነቱ ማታለያ ሆኖ ከዋለ፤ "ይህ በራያ ብቻ የማይቆም ይልቁንም የሁሉ ነገር መፍረሻና ማፍረሻ እንዲሆን መንግስት የፈቀደ መሆኑን ታሪክ የሚመዘግበው ሀቅ ነው”።

የአማራና ትግራይ ክልሎች ጥያቄ በሚነሳባቸው አካባቢዎች ውጥረት ሲነግስ ይኽ የመጀመሪያው አይደለም። በራያ አካባቢ የይገባኛል ጥያቄ የሚነሳባቸው አካባቢዎች ወፍላ ወረዳ፣ ዛታ ወረዳ፣ ኮረም ከተማ፣ አላማጣ ከተማ፣ አላማጣ ወረዳ እና ራያ ባላ ወረዳ ናቸው።

የፌደራል መንግስቱ ጉዳዩ በሕዝበ ውሳኔ እንደሚፈታ መግለጹን ተከትሎ የሕዝብ አሰፋፈር እና የተፈናቃዮች "ትክክለኛነት" ጉዳይ እያወዘገበ የሚገኝ ሲሆን ለሕዝበ ውሳኔ የማይመች ሁኔታ ለመፍጠር በሚደረግ ጥረት ከአማራ እና ትግራይ ክልሎች ውንጀላዎች ይደመጣሉ።
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram
| Facebook | YouTube | X | www.addismaleda.com | 0961414141




የበቴ ኡርጌሳ ሞት ፖለቲካዊ ግድያ ነው ሲል ኦነግ አስታወቀ

ማክሰኞ ሚያዚያ 07 ቀን 2016(አዲስ ማለዳ)የኦሮሚያ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ዛሬ ባወጣው መግለጫ አመራሩ በቴ ኡርጌሳ በፖለቲካዊ ግድያ ነው የሞቱት ብለን እናምናለን ብሏል።

በቴ ኡርጌሳ በኦሮሞ ነፃነት ትግል በህዝቦቹ ዘንድ የተወደደ እና የተከበረ መሆኑን የሚገልጸው የኦነግ መግለጫ ‘ነገር ግን በቴ በጠላቶች እና በኢትዮጵያ መንግስት ዘንድ ፈሪ ነው ልክ እንደ ሌሎቹ ታጋዮች የተገረፈው ለዚህ ነው" ሲል አመላክቷል፡፡

በተጨማሪም መንግስት የኦነግ አመራሮች ኦሮሞን ለመበጣበጥ የድርጅቱን ትግል ለማደናቀፍ ወደ ኦሮሚያ እየመጡ አቅመ ደካሞችን ለማዳከም ከአመራሮች እስከ አባል በማሰር፣ በመግደል፤ ሁሉንም የኦሮሚያ ታጋዮችን በመግደል ሀገሪቷን እየመራ ያለውን መንግስት የፖለቲካ ግድያ እያመላከቱ ነው ብሏል።

አክሎም የበቴ ኡርጌሳ ፍትህ እንደባለፈው ግድያ በኦሮሚያ እንዳይቀር እንደ አርቲስት ዳዲ ገላን፣ ሃጫሉ ሁንዴሳ፣ አባ ገዳ ካራዩ ተድበስብቦ እንዳይቀር ነፃ ምርመራ በውጭ አካላት እንዲደረግ ጠይቋል።

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ የነበሩት በቴ ኡርጌሳ በመቂ ከተማ ካረፉበት ሆቴል እኩለ ሌሊት ላይ “በጸጥታ አካላት” ከተወሰዱ በኋላ ተገድለው መገኘታቸውን አዲስ ማለዳ መዘገቧ ይታወሳል።
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram | Facebook | YouTube | X | www.addismaleda.com | 0961414141






የሹዋሊድ በዓል በዓለም ቅርስነት ከተመዘገበ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከነገ ጀምሮ ይከበራል

ሰኞ ሚያዝያ 07 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) የሐረሪ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ነስሪ ዘከሪያ በክልሉ ከነገ ጀምሮ የሚከበረው የሹዋሊድ በዓል ያለ አንዳች የጸጥታ ቸግር እንዲከበር አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል አሉ።

በዓሉን ተከትሎ የጸጥታ ችግር እንዲከበር ከሌሎች የጸጥታ አካላት ጋር በጋራ በመቀናጀት የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መከናወናቸውም ተገልጿል።

እንደ ኮሚሽነሩ ገለጻ በዓሉ በሚከበርባቸው አካባቢዎች በቂ የጸጥታ ኃይሎችን በማሰማራት የቅድመ ዝግጅት ስራ ተሰርቷል። በዓሉ እስከሚጠናቀቅ ድረስ አስፈላጊው የጸጥታ ስራ ይቀጥላል ተብሏል።

በተጨማሪም በበዓሉ ዋዜማና በዕለቱ የሚፈጠረውን የትራፊክ መጨናነቅ ለመቀነስ እንዲቻል የተወሰኑ መንገዶች ለትራፊክ ዝግ እንደሚሆኑ ኮሚሽነር ነስሪ ገልፆል፡፡

ኢትዮጵያ በ2016 ዓመት የሹዋልኢድ ክብረ በዓል፣ የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ እና የጌዴኦ ባህላዊ መልክዓምድርን በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) የዓለም ቅርስነት ማስመዝገቧ ይታወሳል።
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram
| Facebook | YouTube | X | www.addismaleda.com | 0961414141


በፖለቲከኛው በቴ ኡርጌሳ ግድያ ዙሪያ የዓይን እማኞች የደረሱበት አልታወቀም፤ “አሳፋሪ” ምርመራ እየተደረገ ነው- ኦነግ

ሰኞ ሚያዝያ 07 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) አጠቃላይ የሚታየው ሁኔታና የመንግስት የጸጥታ አካላት ባህሪ “በደርግ ጊዜ እና ቀይ ሽብር” ወቅትን ይመስላሉ ሲል ኦነግ ገልጿል።

ድርጊቱን የተመለከቱ አንድ የጥበቃ ሰራተኛ እንዲሁም አስክሬኑን ከአውሬ ሲጠብቁ የነበሩ ሰዎች የገቡበት አልታወቀም አልያም ተገድለዋል ተብሏል።

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር የአባሉን ግድያ በተመለከተ በማስረጃ አረጋግጫለሁ ያላቸውን ጉዳዮች ይፋ ያደረገ ሲሆን የግድያውን ሂደት እንዲሁም በዓይን እማኖች ላይ የደረሱ ክስተቶችን https://addismaleda.com/archives/36458
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram
| Facebook | YouTube | X | www.addismaleda.com | 0961414141


የአዲስ ማለዳ የሳምንቱ አንኳር ዜናዎች

እሁድ ሚያዝያ 06 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ)

1. የአዲስ አበባ ፖሊስ በከተማዋ ልዩ ቦታው ቦሌ ሚሊኒየም አዳራሽ አካባቢ “የጽንፈኛው የፋኖ አመራር” ካላቸው አካላት ጋር በዚህ ሳምንት በተደረገ የተኩስ ልውውጥ ሁለት "የፋኖ" አባላት ሲገደሉ፤ ሁለት የፖሊስ አባላት ቆስለዋል።

2. የመላው ኢትዮጵያ እንድነት ድርጅት (መ.ኢ.አ.ድ)፣ አማራ ግዮናዊ ንቅናቄ፣ እናት ፓርቲ እና የኢትዮጵያ ሕዝብ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢ.ሕ.አ.ፓ) በሰላማዊ መንገድ የሚታገሉ ፖለቲከኞች "ተጠያቂነት በሌለው አኳኋን ወደማይታወቅ ቦታ" በመንግስት እየተወሰዱ ነው ብለዋል። ሙሉ ዘገባው https://t.me/addismaleda/18972 ይመልከቱ

3. በሳዑዲ ዓረቢያ ሽሜሲ ማቆያ ማዕከል በአስቸጋሪ ሁኔታ የሚገኙ ዜጎችን መመለስ ተጀምሯል። 70 ሺህ ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ ዓረቢያ ወደአገራቸው በሚቀጥሉት አራት ወራት ይመለሳሉ ተብሎ ይጠበቃል።

4. በአዲስ አበባ ከተማ በሁሉም ክፍለ ከተሞች ውስጥ 221 ለእሳት አደጋ፣ 218 ለጎርፍ አደጋ፣ 27 ለትራፊክ አደጋ እንዲሁም 17 ለመሬት መንሸራተት አደጋ ተጋላጭ የሆኑ ቦታዎች መለየታቸውን እና የቅድመ መከላከል ሥራ እየተሠራ እንደሆነ የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ገልጿል፡፡

5. አምነስቲ ኢንተርናሽናል በኢትዮጵያ የጅምላ ግድያ መበራከት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል አለ። “የኢትዮጵያ መንግስት ተአማኒነት ያለው ጥረት እያደረገ አይደለም" ተብሏል፤ ዝርዝሩን https://t.me/addismaleda/18999

6. በጋምቤላ ክልል በጆርና በኢታንግ ልዩ ወረዳ ተከስቶ በነበረው የፀጥታ መደፍረስ ምክንያት እጃቸው አለባቸው የተባሉ 14 አመራሮችና አንድ ግለሰብ በህግ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።

7. በተለያዩ አካባቢዎች እምነትን መሰረት አድርገው የሚፈጸሙ ጥቃቶችን በተመለከተ መንግስት ንጹሃን ዜጎችን ከጥቃት የመጠበቅ ሕጋዊና መንግስታዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ የበላይ ጠባቂ አባቶች ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤትም በአማራ ክልል ሙስሊሞች ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶች እየተባባሱ በመሆኑ የክልሉ መንግስት ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጠይቋል።

8. መንግስት በአሸባሪነት የፈረጀውና ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት (ኦነሠ) ብሎ የሚጠራው ቡድን የኦነግ አመራሩ በቴ ኡርጌሳ በመቂ ከተማ ካረፉበት ሆቴል እኩለ ሌሊት ላይ “በጸጥታ አካላት” ከተወሰዱ በኋላ ተገድለዋል ሲል ገልጿል። የክልሉ መንግስት ከተሟላ ምርመራ በፊት ምንም ማለት አይቻልም ብሎ ለጊዜው ባልታወቁ ሰዎች ሲል ገልጾታል። የዚህ ዝርዝር https://addismaleda.com/archives/36451

9. ለሁለት ዓመታት በትግራይ ክልል በተቀሰቀሰው ጦርነት ምክንያት ለ17 ወራት ሳይከፈል የቆየው የጡረታ አበል እየተከፈለ እንደሆነ አዲስ ማለዳ ከአረጋውያን ማህበሩ አረጋግጣለች። ዝርዝሩን https://t.me/addismaleda/18961 ያንብቡ

10. በኦሮሚያ ክልል ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን አመያ ወረዳ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ ንጹሀን እየተገደልን ነው ሲሉ ቅሬታ አቅርበዋል። ልዩ ስሙ ቆታ በተባለ ከተማ ታጣቂዎች "ከ40 በላይ ሰዎችን በመግደል ባንኮችን መዝረፋቸው" ለአዲስ ማለዳ ጥቆማ ደርሷል; ሙሉ ዘገባው https://t.me/addismaleda/18964

11. በ15 ቀናት ውስጥ ከ700 በላይ እግረኞች በመንገድ ትራንስፖርት ትራፊክ መቆጣጠሪያ ደንብ ቁጥር 395/2009 መሰረት መቀጣታቸውን አዲስ ማለዳ ከባለስልጣኑ ሰምታለች።
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram
| Facebook | YouTube | X | www.addismaleda.com | 0961414141



Показано 20 последних публикаций.