ኢትዮ ቴሌኮም ስድስት ወር ውስጥ ከ60 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ አገኘሁ አለ::
ኢትዮ ቴሌኮም በግማሽ በጀት ዓመቱ 61.9 ቢሊዮን ብር ገቢ በማስገኘት የእቅዱን 90.7በመቶ ማሳካት መቻሉን አስታውቋል፡፡
ተቋሙ ይህን ያስታወቀው የ2017 በጀት ዓመት የስድስት ወር የስራ አፈጻጸም ሪፖርቱን ባቀረበበት ወቅት ነው።
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አሰፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ ከአለም አቀፍ አገልግሎት የተገኘ ገቢ 64.4 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በማስገባት የእቅዱን 63.8በመቶ ማሳካት መቻሉን ተናግረዋል ፡፡
ባለፉት ስድስት ወራትም 3.24 ሚሊዮን አዳዲስ ደንበኞች በማፍራት አጠቃላይ የቴሌኮም አገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞቻችን ብዛት 80.5 ሚሊዮን መድረሱን ገልፀው ከባለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ5.9 ሚሊዮን እድገት ማሳየቱን ገልፀዋል።
በአገልግሎት አይነት ሲታይ የሞባይል ድምፅ ደንበኞች ብዛት 77.7 ሚሊዮን፣ የሞባይል ዳታና ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች 43.5 ሚሊዮን አዲስ ማለዳ ከኢትዮ ቴሌኮም የሥራ ኃላፊዎች ሰምታለች።
ኢትዮ ቴሌኮም የሳይበር ጥቃት ሙከራዎች እና የአቅርቦት እጥረት በስድስት ወር ውስጥ ያጋጠሙኝ ተግዳሮቶች ናቸው ሲል ገልጿል።
ኢትዮ ቴሌኮም በግማሽ በጀት ዓመቱ 61.9 ቢሊዮን ብር ገቢ በማስገኘት የእቅዱን 90.7በመቶ ማሳካት መቻሉን አስታውቋል፡፡
ተቋሙ ይህን ያስታወቀው የ2017 በጀት ዓመት የስድስት ወር የስራ አፈጻጸም ሪፖርቱን ባቀረበበት ወቅት ነው።
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አሰፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ ከአለም አቀፍ አገልግሎት የተገኘ ገቢ 64.4 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በማስገባት የእቅዱን 63.8በመቶ ማሳካት መቻሉን ተናግረዋል ፡፡
ባለፉት ስድስት ወራትም 3.24 ሚሊዮን አዳዲስ ደንበኞች በማፍራት አጠቃላይ የቴሌኮም አገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞቻችን ብዛት 80.5 ሚሊዮን መድረሱን ገልፀው ከባለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ5.9 ሚሊዮን እድገት ማሳየቱን ገልፀዋል።
በአገልግሎት አይነት ሲታይ የሞባይል ድምፅ ደንበኞች ብዛት 77.7 ሚሊዮን፣ የሞባይል ዳታና ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች 43.5 ሚሊዮን አዲስ ማለዳ ከኢትዮ ቴሌኮም የሥራ ኃላፊዎች ሰምታለች።
ኢትዮ ቴሌኮም የሳይበር ጥቃት ሙከራዎች እና የአቅርቦት እጥረት በስድስት ወር ውስጥ ያጋጠሙኝ ተግዳሮቶች ናቸው ሲል ገልጿል።