በልዩ ልዩ መንፈሳዊ መዝሙር ቤተ ክርስቲያንን በማገልገል የሚታወቀውና ከተወሰኑ ዓመታት በፊት በስህተት መንገድ ከቤተ ክርስቲያን ኮብልሎ የነበረው ዲ/ን ዘማሪ ዕዝራ ኃ/ሚካኤል ወደ እናት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን መመለሱን አስታወቀ፡፡
ዘጋቢ፡- መምህር ማቆርስ ተበቃ
(#EOTCTV ሚያዝያ ፲፰ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም አዲስ አበባ)
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++
ዘማሪው ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የብዙኃን መገናኛ ድርጅት (EOTC TV) ጋር ባረገው ቆይታ ለቅዱስ ፓትርያኩ የይቅርታ ደብዳቤ መጻፉን ገልጾ ቤተክርስቲንም ይቅርታውን መቀበሏን ገልጿል፡፡
በቅጽል ስሙ ሕፃን ዕዝራ በመባል ይጠራ የነበረውና በጣዕመ ዝማሬው ቤተ ክርስቲያንን ሲያገለግል የምናውቀው ዲ/ን ዘማሪ ዕዝራ ኃ/ሚካኤል ከ2009 ዓ.ም ጅምሮ በስህተት መንገድ በመጓዝ ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ተለይቶ ቆይቷል፡፡
ሆኖም ግን አገልጋዩ ከሄደበት ጊዜ አንስቶ በመንፈሳዊና በሥጋዊ ሀብት ያሳደገችውን እናት ቤተ ክርስቲያንን ከልቦናውና ከህሊናው ሊያወጣት ባለመቻሉ ለበርካታ ሥነ ልቦናዊ ጉዳት መዳረጉን ጠቁሞ ወደ አሳደግችው እናት ቤተ ክርስቲያን ለመመለስ የይቅርታ ደብዳቤ ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ጽፎ አቅርቧል፡፡
ቅዱስነታቸውም ጉዳዩን ወደ ቋሚ ቅዱስ ሲኖዶስ በማስተላለፍ ውይይት የተደረገበት ሲሆን፤ በተደረገው ውይይትም ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ዓላማዋ ያሉትን በትምሕርት ማጽናት፣ የጠፉትን መክራና ዘክራ በይቅርታና በምሕረት መመለስ ነውና የዲ/ን ዕዝራ ኃ/ሚካኤልን የይቅርታ ደብዳቤ በቋሚ ቅዱስ ሲኖዶስ ተቀባይነት አግኝቷል፡፡
በዚህም መሠረት ዲ/ን ዕዝራ ኃ/ሚካኤል ወደ ቤተ ክርስቲያን እና ወደ ጥንት አግልግሎቱ እንዲመለስ የተወሰነ ሲሆን፣ አገልጋዩ በአንደበቱም ቤተ ክርስቲያንን እና ምእመናንን ይቅርታ ጠይቋል፡፡
ዲ/ን ዕዝራ ኃ/ሚካኤል ይቅርታ የጠየቀበትን ቪዲዩ ከሥር በተመለከተው ሊንክ ማግኘት ይቻላል።
https://youtu.be/MbQNPfXGA_k?si=p4_UGsQqZ_EmEwv0#EOTC TV
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++
https://youtu.be/Wqgq1KebrOo 🇪🇹 "የቤተክርስቲያን የሆነውን ብቻ" 🇪🇹
📡 የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት 🎥
📱 የዲጂታል ሚዲያ ገጾች💻
ለመረጃ 📞 +251985585858
➽ የዩቲዮብ ገጻችን
http://www.youtube.com/c/eotctv➽ የፌስ ቡክ ገጻችንን
https://www.facebook.com/eotctvchannel➽የቴሌግራም ገጻችን
https://t.me/eotctvchannel➽ የቲክ ቶክ ገጻችን
https://vm.tiktok.com/ZMFSxXdUf/➽ የዩቲዮብ ገጻችን Eotc tv 2
https://youtu.be/Wqgq1KebrOo➽የትዊተር ገጻችን
https://twitter.com/EotcT/➽የኢንስታግራም ገጻችን
https://www.instagram.com/p/CknRF0MtB77/?igshid=MDJmNzVkMjY