Ethio Menzuma


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Религия


Welcome to Ethio Menzuma! We preserve the traditional spiritual music and prayers of Ethiopia. Join us to experience the beauty and power of this spiritual music. Stay connected for daily updates, unique content, and a chance to celebrate and honor our cu

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Религия
Статистика
Фильтр публикаций


የሀሰን ታጁ መልእክት ነው የኡማ






🤣🤣🤣😂😂ቤት ውስጥ ትንሽ ት/ት ቤት

#Ethiopia | ሳውዲ አረብያዊው የ50 ዓመት ሰው ከአንድ ት/ት ቤት ከየአይነቱ ማለትም ተማሪ ፣መምህር ፣ የት/ት ቤቱን መሪዎች ማግባታቸውን አል አረብያ ዘግቧል::🤣🤣🤣😂😂😂🤣




ሰበር ዜና! ቅዳሜ 1
የስነ ፈለክ ተመራማሪ እና ባለራዕይ ሊቅ አብዱላህ አልኩዳይሪ እንዲህ ይላሉ፡- በሥነ ፈለክ ጥናት የተባረከው የረመዳን ወር የመጀመሪያው ቀን ቅዳሜ መጋቢት 1 ቀን 2025 ብለው ገምተዋል ። 🌙🤲😍




መልኳም ኳሚስ ይሁንላችሁ


Репост из: HASSEN TAJU
Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
እንኳን ለወርሀ ረመዷን በሠላም አደረሰን።




የደራሲ ኸድር ታጁ መፅሃፎች በመመረቅ ላይ ናቸው
......................................
ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጅ ዑመር እንድሪስን ጨምሮ ታላላቅ የሃገራችን ዑለማዎች ማዲሆች እና ሙሁራን በተገኙበት በቢላሉል ሃበሺ ማእከል በኢንጅነር ኸድር ራህመቶ የመሰብሰቢያ አዳራሽ በመመረቅ ላይ ናቸው ።
በምረቃውም ከዳናዎች ቅፅ ሁለት በተጨማሪ የደራሲው ቀደምት ስራዎች በመመረቅ ላይ ናቸው።


ዉሸታሞች ሲበዙ የሚዋሹበት ነገር ራሱ ይደበላለቃል

የአቅል ፍርድ - ነገረ ተንታ
✍️
በትናንትናው ዕለት በደቡብ ወሎ ዞን ተንታ ወረዳ የመውሊድ ምግብ ተመርዞ አራት ሰዎች መሞታቸውን እና ቁጥሩ ከፍ ያለ የመውሊዱ ተሳታፊ ደግሞ መመረዛቸውን በሶሻል ሚዲያ ላይ መንሸራሸሩ እንዲሁም የወንጀል ተጠርጣሪዎቹ በአካባቢው የመውሊድ ስነስርዓቱን ሲቃወሙ የነበሩ ግለሰቦች ናቸው መባሉን ተከትሎ የተለያዩ ግለሰቦች ተቃውሞ ሲያሰሙ ውለዋል ።

✍️
የመጀመሪያው በጉዳዩ ላይ አስተያየት የሰጡት ግለሰብ "Mohammed Seid" የተባሉ ከተንታ ወረዳ አስተዳደር ሲሆኑ በአካባቢው ማህበረሰብ መዋጮ የተዘጋጀ የመውሊድ ፕሮግራም መሆኑን ገልፀው የችግሩ ምክንያት ደግሞ የታረደው በሬ ህመምተኛ መሆኑ አስረድተዋል ።

❶ ምክንያቱ የታመመ በሬ ነው ተብሎ ከተረጋገጠ ግለሰቦችን ማሰሩ ለምን አስፈለገ ?

❷ ከአካባቢው በስልክ ደውለን ባገኘነው መረጃ መሰረት የተቀቀለውን የበሬ ስጋ ብቻ የተመገቡ ተሳታፊዎች ምንም አይነት የመመርዝ ጉዳት ያላጋጠማቸው ሲሆን በአንፃሩ ተጠርጣሪ ግለሰቧ ባመጣችው ዘይት የተሰራውን ወጥ የተመገቡ ግለሰቦች መመረዛቸውን ነግረውናል ። ስለዚህ ጉዳዩ ከበሬው ስጋ ሳይሆን ከዘይቱ ነው ወደሚል ድምዳሜ ያደርሰናል ።

✍️
ሁለተኛው በጉዳዩ ላይ አስተያየት የሰጠው አቶ ሙሐመድ አባተ ሲሆን የመውሊድ ፕሮግራም እንዳልሆነ እና የመመረዙ ምክንያት ከተለያዬ ቦታ የተሰበሰበ ምግብ መሆኑን የወረዳው ጤና ጽ/ቤት አረጋግጧል ሲል ፅፏል።

❶ መሐመድ አባተ ከወረዳው ጤና ጽ/ቤት አገኘሁ ያለው መረጃ ከወረዳው አስተዳደር መረጃ ጋር እንዴት ሊጣርስ ቻለ ?

❷ በመሐመድ አባተ መረጃ መሰረት የምግብ መመረዙ ምክንያት ከተለያዬ ቦታ የተሰበሰበ ምግብ ሲሆን የወረዳው አስተዳደር ደግሞ የታረደው በሬ የታመመ በመሆኑ ነው ብሏል ። እንዴት ?

❸ ሙሐመድ አባተ ሶስት ሰዎች መሞታቸውን ገልፆ የሞቱት ግን የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው በአራተኛው ቀን ነው ያለ ሲሆን በአንፃሩ የወረዳው መስተዳድር ሁለቱ ግለሰቦች የሞቱት የህክምና ቡድኑ በአካባቢው ሳይደርስ ነው በማለት ገልጿል። ለመሆኑ ሙሐመድ አባተ አምባሳደር ሐሰን ታጁን ለመወንጀል በዚህ ልክ መዋሸት ለምን አስፈለገው ?

❹ መሐመድ አባተ ጉዳዩን ሁለት ሳምንት ያለፈው ነው በማለት ለማጣጣል ሞክሯል ። በዕርግጥ ከአሁን በፊት ሻሸመኔ ላይ በዕድሜ የገፉ የመጅሊስ አመራሮች በአፍላ ወጣቶች በቡጢ እና በካልቾ ሲነረቱ የሚያሳይ ቪዲዮ ሶሻል ሚዲያ ላይ በተለቀቀ ወቅት ካሚል ሸምሱ "ጉዳዩ ወር ያለፈው ነው ፤ የመቷቸው አህባሽ መስለዋቸው ነው " ማለቱን አንዘነጋውም ። እንግዲህ የህግ ምሩቅ የሆነው ካሚል ሸምሱ ይህንን ካለ ጓደኛው ሙሐመድ አባተ ከዚህ የከፋ ቢናገር ገርሞ አይገርምም ።

✍️
ሶስተኛው በጉዳዩ አስተያየት የሰጠው ፕሮፌሰር ቃልኪዳን [Kha Abate] ሲሆን የችግሩ ምክንያት "በአረም መርዝ ዕቃ ዘይት ቀንሰው ወጥ ተሰራ" በማለት ፅፏል።

✍️
እንደ አጠቃላይ ከላይ የተጠቀሱት ግለሰቦች የምግብ ምረዛው ምክንያት በማለት የተለያዩ ሶስት ምክንያቶችን አስፍረዋል ። ይህም በጉዳዩ ላይ የተጠረጠሩ ግለሰቦችን ከህግ ተጠያቂነት ለማስመለጥ የታሰበ ነገር ሊኖር ይችላል የሚል እሳቤን ያጭራል ። በመሆኑም የተጎጂ ቤተሰቦች እንዲሁም የአካባቢው ማህበረሰብ በጉዳዩ ላይ ያለ ምንም ጫና ለሚዲያዎች ማብራሪያ ቢሰጡ እንዲሁም የወሃብያው ወገን በህግ አፈፃፀም ላይ ጣልቃ እንዳይገባ ተደርጎ ተገቢውን የህግ ማስከበር ሒደት እንዲከናወን ስንል በትህትና እንጠይቃለን ‼️


#ለክቡር_አምባሳደር_ሀሰን_ታጁ
ረጅም ሀያት
#ቻሌንጅ@ethio_Menzuma




My Hero




ፕሬዚዳንት ኤርዶጋን የመጀመሪያውን ረመዷን በሶሪያ ያፈጥራሉ የመጀመሪያውንም ተራዊህ በደማስቆ ኡመውይ መስጅድ ይሰግዳሉ!

ፕሬዚዳንቱ ከዛሬ 13 አመት በፊት " ወላህ ያ አሳድ በአላህ ፈቃድ ሶሪያን ነፃ እናወጣታለን በኡመያ መስጅድም ጀመአ እንሰግድበታለን" ብለው መናገራቸው ይታወቃል።

በቱርክ እገዛ የሶሪያ ነፃ አውጪዎች የአሳድን ሰቅጣጭ አገዛዝ ካስወገዱና ሶሪያን ነፃ ካወጡ በሗላ አላህን ለማመስገን የዘንድሮው የመጀመሪያ የረመዷን ቀንን ኤርዶጋን በሶሪያ እንደሚያሳልፉ የቱርክ መገናኛ ብዙሀን ዘግበዋል።

አላህ የሶሪያ ወንድሞቻችንን ነፃ እንዳወጣቼው የፍልስጤም ወንድሞቻችንንም የነፃነታቸውን ቀን ቅርብ አድርጎላቸው ያስደስተን!




ኢንና ሊላህ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን
ተንታ አካባቢ ለመውሊድ የሚዘጋጀ ምግብ እንዲመረዝ በማድረግ አንድ ሸይኽ ከሶስት ደረሶቻቸው ጋር ወዲያውኑ እንደሞቱ በርካቶች በመርዙ ጉዳት እንደደረሰባቸው ሰማን። አላህ የሞቱትን በጀነት ያኑርልን የተጎዱትን ቶሎ ያሽርልን።
ሐስቡነላህ ወኒዕመል ወኪል
ነገሮች ወዴት እየሄዱ እንደሆኑ ትልቅ ማሳያ ነው። የሚመለከታችሁ የፀጥታና የህግ አካላት ይህን ፀያፍና ዘግናኝ ተግባር የፈፀሙትን በማጋለጥና በነዚህ ጨካኞች ላይ ተገቢውን እርምጃ በመውሰድ የመውሊድ ወዳጆችን ታሪካዊ ጠላት ህዝብ እንዲያውቀው የማድረግን ስራ ትሰሩ ዘንድ እንጠይቃለን። እንዲህ አይነት ጭካኔ የተሞላበትን የጅምላ ግድያ የሚፈፅሙ አካላት ወይም ቡድኖች ህዝበ ሙስሊሙን የማይወክሉ አውሬዎች መሆናቸውንም አውቃችሁ ከስር ያሉ መዋቅሮቻችሁ እነሱን ማገዝ አቁመው ፍትህን በማስፈን ከሙስሊሞች ጫንቃ ላይ አሸቀንጥራችሁ እንድትጥሉ እንጠይቃለን ።



Показано 20 последних публикаций.