አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) በጎፋ ዞን በደረሰው አደጋ ለተጎዱ ወገኖች የ1 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ!
አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ ለተጎዱ ወገኖች የአንድ ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርጓል፡፡
አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን በጎፋ ዞን በገዜ ጎፋ ወረዳ በኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው ድንገተኛ የመሬት መንሸራተት አደጋ ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ድጋፉን በማድረግ በአደጋው ህይወታቸውን ላጡ ወገኖች መጽናናትን ተመኝቷል፡፡
በጎፋ ዞን፣ ገዜ ጎፋ ወረዳ፣ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ ጉዳት የደረሰባቸውን ዜጎች ለማገዝ የተለያዩ አካላት ድጋፋቸውን እያደረጉ ሲሆን፤ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችም አደጋው በደረሰበት ስፍራ በመገኘት ተጎጂዎችን እያፅናኑ ይገኛል።
ከዚህ ጋር ተያይዞ በኢትዮጵያ ከነገ ጀምሮ ለሦስት ቀናት የሚቆይ ብሔራዊ ሐዘን ማወጁን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያስታወቀ ሲሆን፤ ብሔራዊ ሐዘኑ የታወጀው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰውን የመሬት መንሸራተት አደጋ የዜጎች ሕይወት በማለፉ መሆኑ ተገልጿል፡፡
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ ለተጎዱ ወገኖች የአንድ ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርጓል፡፡
አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን በጎፋ ዞን በገዜ ጎፋ ወረዳ በኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው ድንገተኛ የመሬት መንሸራተት አደጋ ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ድጋፉን በማድረግ በአደጋው ህይወታቸውን ላጡ ወገኖች መጽናናትን ተመኝቷል፡፡
በጎፋ ዞን፣ ገዜ ጎፋ ወረዳ፣ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ ጉዳት የደረሰባቸውን ዜጎች ለማገዝ የተለያዩ አካላት ድጋፋቸውን እያደረጉ ሲሆን፤ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችም አደጋው በደረሰበት ስፍራ በመገኘት ተጎጂዎችን እያፅናኑ ይገኛል።
ከዚህ ጋር ተያይዞ በኢትዮጵያ ከነገ ጀምሮ ለሦስት ቀናት የሚቆይ ብሔራዊ ሐዘን ማወጁን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያስታወቀ ሲሆን፤ ብሔራዊ ሐዘኑ የታወጀው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰውን የመሬት መንሸራተት አደጋ የዜጎች ሕይወት በማለፉ መሆኑ ተገልጿል፡፡
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ