ታላቁ ደራሲ / ስብሐት ገ/እግዚአብሔር፦
ጋሼ ስብሐት ብለው ይጠሩታል ብዙዎቹ፣ ለሕይወት ቁብ የሌለው፣ በመፃፍና በድርሰት የታጠረ፣ ኢንተርቪው ሲደረግ በቀልድ አዋዝቶ የሚመልሳቸው መልሶች፣ ሕይወትንና የኑሮ ውጥንቅጥን አቅሎ የሚያይ፣ በሕይወት የሚያጋጥሙትን ክስተቶች ለመቀበል ቸል የማይል ሠው ነበር ጋሽ ስብሐት።
የፃፋቸውን ድርሰቶችና፣ በጋዜጦችና መፅሔቶች ያስተላለፋቸው ፅሑፎች ሲታዩ ይዘታቸው ገራሚ ነው፣ ቅርፃቸውም የሚያምርና የተሽሞነሞነ። ከጋሽ ስብሐት ድርሰቶች ልብን የሚሠቅሉና በተለዬ መልክ የተፃፉ ትኩሳትና ሌቱም አይነጋልኝ ናቸው፣ ለትውስታ በትካሳት ላይ ከዚህ በፊት ያስተላለፍኩት ፅሑፍ ተለጥፏል። በሌቱም አይነጋልኝ ድርሰቱ ያስተላለፋቸው መልእክቶች ገራሚ ናቸው። በተለይ በአማርኛ ሥነ ፅሑፍ ያልተለመዱ ቃላትን እንደወረዱ ፈሰስ ለማድረግና ታቡን ለመጣስ የመጀመሪያው ሠው ጋሽ ስብሐት ይመሥላል። ለምሳሌ ከዚሁ ድረሰቱ ተቀንጭባ የተለጠፈች ፅሑፍ አለች፣ ስብሐት ለምንም ታቡ ደንታ እንደሌለው የምትገልፅ። በዚያች ፅሑፍ ታቡን አጥባቂዎች ብቻ ሳይሆኑ የማያጠብቁም ሠዎች "የማይጋሩት" ክስተት እናያለን አንዲት ሴትን ለብዙ መጋራት። በድርሰቱ ሙሉ ተብላ የምትጠራ ከማሚት ጋር የምትኖር ሴተኛ አዳሪ አለች፣ እርሷን አንዱ ለአዳር ይዟት ሄደ ከአምሥት ጓደኞቹም ጋር ተጋሯት፣ ግንኙነትን የፈፀሙ ስድስት ናቸው፣ አንድ ለስድስት ብንል ያስኬደን ይሆን ? በብዙዎች አስተያዬት ይህ ሰብአዊ ባኅሪይ ሳይሆን እንደ እንሰሳዊ ባኅሪይነት የሚታሰብ ነው /የፈረደበት እንስሳ ብዙ ሥም ይሰጠዋል/። በውነት ነውን ? የሚል ጥያቄ ብናነሳ መልሱ አይደለም ነው። ስብሐት ያነሳው የሠው ልጅ ከሚኖርበት ሕይወት በመነሳት ነው፣ የሠው ልጅ ጨለማን ወይም አለመጋለጥን ተገን አድርጎ የሚፈፅመው ተግባር። ክስተቱን ፈፃሚዎች እንስሳትም ሠዎችም ናቸው፣ ልዩነቱ እንስሳት በግልፅ የሠው ልጅ በሥውር ማድረጋቸው ብቻ ነው። እንግዲህ ጋሽ ስብሐት የሠው ልጅ በሥውር የሚከውነውን ነው አደባባይ ያወጣውና፣ ጥፋተኝነቱ እምኑ ላይ ነው።
ጋሽ ስብሐት ነባራዊ እውነታን ለምን እንሸፋፍነዋለን ባይ ነው፣ የሚወደደውም በዚህ ፀባዩ ነው። ለምሳሌ ለማንኛውም የሠውነት ክፍል ስም እንዳለው ሁሉ ለመራቢያ አካላትም ሥም አለ። መራቢያ አካላትን በሥማቸው መጥራቱ፣ ሥማቸውን አደባባይ ማውጣቱ ክፋቱ ምንድርነው በማለት ራሡን ከጠየቀና ከራሡ ጋር ከተስማማ በኋላ ነው አደባባይ ያወጣው። በዚህ ቅንጣት እንደማያፍርና ተፈጥሯዊ በሆነ ነገር አፋችንን መሸበብ እንደሌለብን ነው የገለፀልን። ለምሳሌ እንደነ ሮዛ ቁጥር አንድና ቁጥር ሁለትን የመሣሠሉ ድርሰቶች ታቡን መጣስ የተማሩት ከጋሽ ስብሐት እንደሆነ ይታሠባል።
ይህን ከብልግና ጋር የምናያይዘው ከሆነ ነው ትልቁ ስሕተት፣ ተፈጥሮን በተሠጠው ሥም በአደባባይ መጥራት በምንም መልኩ ብልግና ሊሆን አይችልም፣ ይህን እውነታ የማንም ልብ ሊዘነጋው አይገባም ከነባራዊ እውነታ ልንርቅ ስለማንችል።
በተለጠፈው ትኩሳት ድርሰቱ አስተያዬት ላይ ብዙ ሀሳቦች ተሰንዝረዋል የጋሽ ስብሐት፣ በዚያ ድርሰቱ ብዙ ነገር እንዳስተማረን፣ ወጣትነትን፣ እርጅናን፣ ሪቮሊሲዮንን፣ ፍቅርን፣ የመለየት ምሬትን፣ የጓደኝነት ሚስጥራትን፣ ሌሎችንም ክስተቶች። የተለጠፈውን አስተያዬት አንብባችሁ ተረዱ፣ ሀሳብም ሰንዝሩ። አስተያዬቱን እነሆኝ፦
ትኩሳት የስብሐት ገብረ እግዚአብሔር ወጣትነት ትውስታ ድርሰት፦
ስብሐት በወጣትነቱ፣ ስብሐት በስርጅናው ስዕሎቹ እታች ይታያሉ፣ ስብሐት ወጣትነትን እንደሚያደንቅ ሁሉ እርጅናን ይፈራ ነበር፣ እርጅና ቃሉ ያሸማቅቀዋል። በፈረንሣይ ሀገር የ፪ኛ ዲግሪ ትምህርቱን በሚከታተልበት ወቅት በየቦታው የፈረንሣይ ሴትና ወንድ አዛውንቶች ያጋጥሙታል፣ የእርጅናንም አስፈሪነት ያስገነዝቡታል፤ ስብሐት ይህንን በትኩሳት መፅሐፉ እንዲህ ይገልፀዋል፦
" በጣም ይቀፋሉ የፈረንጅ ሽማግለዎችና አሮጊቶች። ጨምዳዳ ቆዳቸው የተሰነጣጠቀ ደረቅ ሠም ይመስላል። ቀጥቃጣዎች። ዝምተኞች። አገጫቸው ተገንጥሎ ወደ ታች የወደቀ፣ ከንፈራቸው የተንጠለጠለ፣ ጥርሳቸው የፈራረሰ ሽማግሌዎች። ጥርሳቸው አልቆ አፋቸው ወደ ውስጥ የጎደጎደ ፅማም አሮጊቶች። የመኖር ግዜያቸው አልፎ የሞት ግዜያቸውን ዘመናዊ ህክምና ከልክሏቸው ፣ ታችኛ ከንፈራቸውን እንደ ጡጦ እየጠቡ ሞትን ሲጠብቁ የሚውሉ የሕይወት ኦናዎች። ለዓይን ብቻ ሳይሆን ለአፍንጫም ይቀፋሉ ። የልዩ ልዩ መድኃኒት ፣ የእርጅና፣ የሞት ሽታ፣ ሳይቀበር መግማት የጀመረ ሥጋ።"
ለስብሐት አስፈሪው እርጅና እንደዚያ ነበር የሚታየው፣ አበስኩ ገበርኩ የሚያሰኝ፣ ተላላፊ በሽታን የመሠለ። ወጣትነትስ? እንዲህ ይገልፀዋል፦
" ጥሩ ነው ወጣት መሆን ገንዘብ ባይኖርህም ጤና ይኖርሀል፣ መልክ ባይኖርህም አንጎል ይኖርሀል፣ ዕውቀት ባይኖርህም ጉራ ይኖርሀል፣ ፍቅር ባይኖርህም ተስፋ ይኖርሀል፣ ደስታ ባይኖርህም ንዴት ይኖርሀል፣ መጨቆን ቢኖርብህ ሪቮሉሽን ታነሳለህ-------መኖር ቢያስጠላህ ወይም ቢያቅትህ ራስህን ትገድላለህ፣ ሠው ባያውቀም ቅሉ ታሪክ ይኖርሀል ወጣት ነህና።"
ወይ ጋሽ ስብሐት የሚገርም ነው። እስቲ የንዴት መኖር፣ የጉራ መኖርና ራስን መግደል እንዴት እንደ መፍትሔ ሀሳብ ይቆጠራል። ምናልባት የወጣትነት ድፍረትና ቆራጥነት እነዚህንም እንደ መፍትሔ ሀሳብ ያስቆጥር ይሆን።
ጋሽ ስብሐት በትኩሣት መፅሐፉ ብዙ ነገር ይላል፣ በብዙ ነገር ይፈላሰፋል፣ በፈረንሳይ ተማሪ በነበረበት ግዜ ማነሁለል ይችልበት ነበር፣ ከቆነጃጅት የፈረንሳይ እንስት ወጣቶች ጋር ዓለሙን ቀጭቷል፣ በቋንቋው ያነሆልላል፣ ዐዕምሮው ለዕውቀት ክፍት ነበር፣ በጥቂት ግዜ የፈረንሳይኛ ቋንቋን በቁጥጥሩ ስር አድርጎት ነበር፣ ችሎታው በዛዚ ርዕስ የንኮሎን መፅሐፍ በአማርኛ እንዲተረጉም አብቅቶታል፣ ጨዋነቱ፣መልከ መልካምነቱና ከፍተኛ የቀለም ቀበኛነቱ ተወዳጅነትን አትርፎለት ነበር።
የምትወደውንና መልከመልካሟን ፈረንሣይት ወጣት እንዲህ ይገልፃታል፦
" ሲልቢ በጣም ቆንጆ ናት፣ እጥር ምጥን ያለች ፈረንሳዊት ሆና ቡናማ ጉልህ አይኖችዋ ውስጥና ውብ አፍዋ ዙሪያ እንደ ነበልባል የሚውለበለበው ፈገግታዋ ልብ ያሞቃል። ወደ ኋላ የተለቀቀው ንፁህ ጥቁር ፀጉሯ ያብለጨልጫል ------ከታች ደግሞ አበጥ ያለው ዳሌዋ እንደ ፀጉሯ ይወዛወዛል። እግርዋ በብዙ ጥንቃቄ የተቀረፀ ውብ ፍጥረት ነው። ፍቅርም ምቾትም የምትቀሠቅስ ወጣት ትመስላለች።"
ስብሐት ቀላል ሠው አልነበረም። በሲልቢ እጅግ በጣም የሚወደድና የሚፈቀር ወጣት ነበር። በመፅሐፉ እንደተገለፀው የስብሐት ጨዋነትና በራስ ላይ የነበረው ዕምነት፣ ደንታ ቢስነት ብዙም ለሴትም ሆነ ለሌላ አለመጨናነቅ በሲልቢ ተወዳጅ አድርጎታል። ባይታወቅበትምና በድብቅ ቢይዘውም ቅብጥብጥ ወጣቷን ማፈቀሩና እንደምታስቀናውም በመፅሐፉ ገልጿል።
ባጠቃላይ ትኩሳት መፅሐፉ ትኩስ ጉልበት ስላለው የወጣቶች ከስብሐት ስራዎች ቀዳሚ ምርጫ መሆኑን ብዙ ወጣቶች ያወሳሉ።
በዚህ መፅሐፉ ስብሐት ስለ ፍቅርና ቅናት ተቃርኖና ጥምርታዊ ግንኙነት፣ ገፅታን ስለማንበብ፣ ስለ ሪቮሊሲዮን፣ የወጣትነትና አዛውንትነት የሕይወት ሂደት፣ የሴት ልጅ ውበትና መስህብነት፣ የፍቅር ሳይኮሎጂ፣ የቋንቋ ክህሎት ጠቀሜታ፣ ሠውን ከእንስሳት የሚለዩ ሠብአዊ ባኅሪያት፣ የወጣትነት ትርጉምና መገለጫዎቹ፣ ግዜን ስለ መመንዘርና መጠቀም፣ ምሳሌያዊ አገላለፆች፣ ስለ ጭቡና ጭቆናንም አካቶ በሚያስደምም ሁኔታ ከሽኖ አቅርቧል።
ጋሼ ስብሐት ብለው ይጠሩታል ብዙዎቹ፣ ለሕይወት ቁብ የሌለው፣ በመፃፍና በድርሰት የታጠረ፣ ኢንተርቪው ሲደረግ በቀልድ አዋዝቶ የሚመልሳቸው መልሶች፣ ሕይወትንና የኑሮ ውጥንቅጥን አቅሎ የሚያይ፣ በሕይወት የሚያጋጥሙትን ክስተቶች ለመቀበል ቸል የማይል ሠው ነበር ጋሽ ስብሐት።
የፃፋቸውን ድርሰቶችና፣ በጋዜጦችና መፅሔቶች ያስተላለፋቸው ፅሑፎች ሲታዩ ይዘታቸው ገራሚ ነው፣ ቅርፃቸውም የሚያምርና የተሽሞነሞነ። ከጋሽ ስብሐት ድርሰቶች ልብን የሚሠቅሉና በተለዬ መልክ የተፃፉ ትኩሳትና ሌቱም አይነጋልኝ ናቸው፣ ለትውስታ በትካሳት ላይ ከዚህ በፊት ያስተላለፍኩት ፅሑፍ ተለጥፏል። በሌቱም አይነጋልኝ ድርሰቱ ያስተላለፋቸው መልእክቶች ገራሚ ናቸው። በተለይ በአማርኛ ሥነ ፅሑፍ ያልተለመዱ ቃላትን እንደወረዱ ፈሰስ ለማድረግና ታቡን ለመጣስ የመጀመሪያው ሠው ጋሽ ስብሐት ይመሥላል። ለምሳሌ ከዚሁ ድረሰቱ ተቀንጭባ የተለጠፈች ፅሑፍ አለች፣ ስብሐት ለምንም ታቡ ደንታ እንደሌለው የምትገልፅ። በዚያች ፅሑፍ ታቡን አጥባቂዎች ብቻ ሳይሆኑ የማያጠብቁም ሠዎች "የማይጋሩት" ክስተት እናያለን አንዲት ሴትን ለብዙ መጋራት። በድርሰቱ ሙሉ ተብላ የምትጠራ ከማሚት ጋር የምትኖር ሴተኛ አዳሪ አለች፣ እርሷን አንዱ ለአዳር ይዟት ሄደ ከአምሥት ጓደኞቹም ጋር ተጋሯት፣ ግንኙነትን የፈፀሙ ስድስት ናቸው፣ አንድ ለስድስት ብንል ያስኬደን ይሆን ? በብዙዎች አስተያዬት ይህ ሰብአዊ ባኅሪይ ሳይሆን እንደ እንሰሳዊ ባኅሪይነት የሚታሰብ ነው /የፈረደበት እንስሳ ብዙ ሥም ይሰጠዋል/። በውነት ነውን ? የሚል ጥያቄ ብናነሳ መልሱ አይደለም ነው። ስብሐት ያነሳው የሠው ልጅ ከሚኖርበት ሕይወት በመነሳት ነው፣ የሠው ልጅ ጨለማን ወይም አለመጋለጥን ተገን አድርጎ የሚፈፅመው ተግባር። ክስተቱን ፈፃሚዎች እንስሳትም ሠዎችም ናቸው፣ ልዩነቱ እንስሳት በግልፅ የሠው ልጅ በሥውር ማድረጋቸው ብቻ ነው። እንግዲህ ጋሽ ስብሐት የሠው ልጅ በሥውር የሚከውነውን ነው አደባባይ ያወጣውና፣ ጥፋተኝነቱ እምኑ ላይ ነው።
ጋሽ ስብሐት ነባራዊ እውነታን ለምን እንሸፋፍነዋለን ባይ ነው፣ የሚወደደውም በዚህ ፀባዩ ነው። ለምሳሌ ለማንኛውም የሠውነት ክፍል ስም እንዳለው ሁሉ ለመራቢያ አካላትም ሥም አለ። መራቢያ አካላትን በሥማቸው መጥራቱ፣ ሥማቸውን አደባባይ ማውጣቱ ክፋቱ ምንድርነው በማለት ራሡን ከጠየቀና ከራሡ ጋር ከተስማማ በኋላ ነው አደባባይ ያወጣው። በዚህ ቅንጣት እንደማያፍርና ተፈጥሯዊ በሆነ ነገር አፋችንን መሸበብ እንደሌለብን ነው የገለፀልን። ለምሳሌ እንደነ ሮዛ ቁጥር አንድና ቁጥር ሁለትን የመሣሠሉ ድርሰቶች ታቡን መጣስ የተማሩት ከጋሽ ስብሐት እንደሆነ ይታሠባል።
ይህን ከብልግና ጋር የምናያይዘው ከሆነ ነው ትልቁ ስሕተት፣ ተፈጥሮን በተሠጠው ሥም በአደባባይ መጥራት በምንም መልኩ ብልግና ሊሆን አይችልም፣ ይህን እውነታ የማንም ልብ ሊዘነጋው አይገባም ከነባራዊ እውነታ ልንርቅ ስለማንችል።
በተለጠፈው ትኩሳት ድርሰቱ አስተያዬት ላይ ብዙ ሀሳቦች ተሰንዝረዋል የጋሽ ስብሐት፣ በዚያ ድርሰቱ ብዙ ነገር እንዳስተማረን፣ ወጣትነትን፣ እርጅናን፣ ሪቮሊሲዮንን፣ ፍቅርን፣ የመለየት ምሬትን፣ የጓደኝነት ሚስጥራትን፣ ሌሎችንም ክስተቶች። የተለጠፈውን አስተያዬት አንብባችሁ ተረዱ፣ ሀሳብም ሰንዝሩ። አስተያዬቱን እነሆኝ፦
ትኩሳት የስብሐት ገብረ እግዚአብሔር ወጣትነት ትውስታ ድርሰት፦
ስብሐት በወጣትነቱ፣ ስብሐት በስርጅናው ስዕሎቹ እታች ይታያሉ፣ ስብሐት ወጣትነትን እንደሚያደንቅ ሁሉ እርጅናን ይፈራ ነበር፣ እርጅና ቃሉ ያሸማቅቀዋል። በፈረንሣይ ሀገር የ፪ኛ ዲግሪ ትምህርቱን በሚከታተልበት ወቅት በየቦታው የፈረንሣይ ሴትና ወንድ አዛውንቶች ያጋጥሙታል፣ የእርጅናንም አስፈሪነት ያስገነዝቡታል፤ ስብሐት ይህንን በትኩሳት መፅሐፉ እንዲህ ይገልፀዋል፦
" በጣም ይቀፋሉ የፈረንጅ ሽማግለዎችና አሮጊቶች። ጨምዳዳ ቆዳቸው የተሰነጣጠቀ ደረቅ ሠም ይመስላል። ቀጥቃጣዎች። ዝምተኞች። አገጫቸው ተገንጥሎ ወደ ታች የወደቀ፣ ከንፈራቸው የተንጠለጠለ፣ ጥርሳቸው የፈራረሰ ሽማግሌዎች። ጥርሳቸው አልቆ አፋቸው ወደ ውስጥ የጎደጎደ ፅማም አሮጊቶች። የመኖር ግዜያቸው አልፎ የሞት ግዜያቸውን ዘመናዊ ህክምና ከልክሏቸው ፣ ታችኛ ከንፈራቸውን እንደ ጡጦ እየጠቡ ሞትን ሲጠብቁ የሚውሉ የሕይወት ኦናዎች። ለዓይን ብቻ ሳይሆን ለአፍንጫም ይቀፋሉ ። የልዩ ልዩ መድኃኒት ፣ የእርጅና፣ የሞት ሽታ፣ ሳይቀበር መግማት የጀመረ ሥጋ።"
ለስብሐት አስፈሪው እርጅና እንደዚያ ነበር የሚታየው፣ አበስኩ ገበርኩ የሚያሰኝ፣ ተላላፊ በሽታን የመሠለ። ወጣትነትስ? እንዲህ ይገልፀዋል፦
" ጥሩ ነው ወጣት መሆን ገንዘብ ባይኖርህም ጤና ይኖርሀል፣ መልክ ባይኖርህም አንጎል ይኖርሀል፣ ዕውቀት ባይኖርህም ጉራ ይኖርሀል፣ ፍቅር ባይኖርህም ተስፋ ይኖርሀል፣ ደስታ ባይኖርህም ንዴት ይኖርሀል፣ መጨቆን ቢኖርብህ ሪቮሉሽን ታነሳለህ-------መኖር ቢያስጠላህ ወይም ቢያቅትህ ራስህን ትገድላለህ፣ ሠው ባያውቀም ቅሉ ታሪክ ይኖርሀል ወጣት ነህና።"
ወይ ጋሽ ስብሐት የሚገርም ነው። እስቲ የንዴት መኖር፣ የጉራ መኖርና ራስን መግደል እንዴት እንደ መፍትሔ ሀሳብ ይቆጠራል። ምናልባት የወጣትነት ድፍረትና ቆራጥነት እነዚህንም እንደ መፍትሔ ሀሳብ ያስቆጥር ይሆን።
ጋሽ ስብሐት በትኩሣት መፅሐፉ ብዙ ነገር ይላል፣ በብዙ ነገር ይፈላሰፋል፣ በፈረንሳይ ተማሪ በነበረበት ግዜ ማነሁለል ይችልበት ነበር፣ ከቆነጃጅት የፈረንሳይ እንስት ወጣቶች ጋር ዓለሙን ቀጭቷል፣ በቋንቋው ያነሆልላል፣ ዐዕምሮው ለዕውቀት ክፍት ነበር፣ በጥቂት ግዜ የፈረንሳይኛ ቋንቋን በቁጥጥሩ ስር አድርጎት ነበር፣ ችሎታው በዛዚ ርዕስ የንኮሎን መፅሐፍ በአማርኛ እንዲተረጉም አብቅቶታል፣ ጨዋነቱ፣መልከ መልካምነቱና ከፍተኛ የቀለም ቀበኛነቱ ተወዳጅነትን አትርፎለት ነበር።
የምትወደውንና መልከመልካሟን ፈረንሣይት ወጣት እንዲህ ይገልፃታል፦
" ሲልቢ በጣም ቆንጆ ናት፣ እጥር ምጥን ያለች ፈረንሳዊት ሆና ቡናማ ጉልህ አይኖችዋ ውስጥና ውብ አፍዋ ዙሪያ እንደ ነበልባል የሚውለበለበው ፈገግታዋ ልብ ያሞቃል። ወደ ኋላ የተለቀቀው ንፁህ ጥቁር ፀጉሯ ያብለጨልጫል ------ከታች ደግሞ አበጥ ያለው ዳሌዋ እንደ ፀጉሯ ይወዛወዛል። እግርዋ በብዙ ጥንቃቄ የተቀረፀ ውብ ፍጥረት ነው። ፍቅርም ምቾትም የምትቀሠቅስ ወጣት ትመስላለች።"
ስብሐት ቀላል ሠው አልነበረም። በሲልቢ እጅግ በጣም የሚወደድና የሚፈቀር ወጣት ነበር። በመፅሐፉ እንደተገለፀው የስብሐት ጨዋነትና በራስ ላይ የነበረው ዕምነት፣ ደንታ ቢስነት ብዙም ለሴትም ሆነ ለሌላ አለመጨናነቅ በሲልቢ ተወዳጅ አድርጎታል። ባይታወቅበትምና በድብቅ ቢይዘውም ቅብጥብጥ ወጣቷን ማፈቀሩና እንደምታስቀናውም በመፅሐፉ ገልጿል።
ባጠቃላይ ትኩሳት መፅሐፉ ትኩስ ጉልበት ስላለው የወጣቶች ከስብሐት ስራዎች ቀዳሚ ምርጫ መሆኑን ብዙ ወጣቶች ያወሳሉ።
በዚህ መፅሐፉ ስብሐት ስለ ፍቅርና ቅናት ተቃርኖና ጥምርታዊ ግንኙነት፣ ገፅታን ስለማንበብ፣ ስለ ሪቮሊሲዮን፣ የወጣትነትና አዛውንትነት የሕይወት ሂደት፣ የሴት ልጅ ውበትና መስህብነት፣ የፍቅር ሳይኮሎጂ፣ የቋንቋ ክህሎት ጠቀሜታ፣ ሠውን ከእንስሳት የሚለዩ ሠብአዊ ባኅሪያት፣ የወጣትነት ትርጉምና መገለጫዎቹ፣ ግዜን ስለ መመንዘርና መጠቀም፣ ምሳሌያዊ አገላለፆች፣ ስለ ጭቡና ጭቆናንም አካቶ በሚያስደምም ሁኔታ ከሽኖ አቅርቧል።