TGStat
TGStat
Введите текст для поиска
Расширенный поиск каналов
Russian
Язык сайта
Russian
English
Uzbek
Вход на сайт
Каталог
Каталог каналов и чатов
Поиск каналов
Добавить канал/чат
Рейтинги
Рейтинг каналов
Рейтинг чатов
Рейтинг публикаций
Рейтинги брендов и персон
Аналитика
Поиск по публикациям
Мониторинг Telegram
©Legal details center© :የህግ ማብራሪያ ማዕከል©
5 Jan, 13:24
Открыть в Telegram
Поделиться
Пожаловаться
ባልና ሚስት በየስማቸው የተመዘገቡ መኖሪያ ቤቶች የግል ንብረታቸው እንዲሆኑ በጋብቻ ውል ተስማምተዋል። ሁለቱም ቤቶች የሚገኙት አማራ ክልል ነው። ጋብቻ ውስጥ እያሉ አዲስ አበባ ላይ ቤት መግዛት ፈለጉና አንድ ዘዴ ዘየዱ። ይኸውም በባል ስም የተመዘገበውና የባል የግሉ የሆነው መኖሪያ ቤት ተሸጦ አዲስ አበባ ላይ ለኮንዶሚኒየም መግዣ እንዲውል: በተጨማሪም ይኸው የተገዛው ቤት እና በሚስት ስም ተመዝግቦ ያለው የሚስት የግል ንብረት ሁለቱም የጋራ ንብረቶቻቸው እንዲሆኑ ተስማሙ።
በዚህ መሰረት የባል ቤት ተሸጠና አዲስ አበባ ላይ ቤት ተገዛበት። በመቀጠል ባልና ሚስት ስምምነታቸውን በፍርድ ቤት ለማፀደቅ በዝግጅት ላይ እንዳሉ ሚስት ቀድማ "ትዳር በቃኝ" አለችና ፍቺ ጠየቀች። ፍቺ በፍርድ ቤት ተወሰነ።
ቀጥሎ የንብረት ክፍፍል ጥያቄ ቀረበ። ንብረቱ እንዴት ነው መካፈል ያለበት?
ያው አዲስ አበባ ያለው ቤት የግል ንብረት ተሸጦ በግብይት የተገኘ ስለሆነና በባል በኩል የግል ይባልልኝ አቤቱታ ቀርቦ በፍርድ ቤት ስላልፀደቀ የጋራ ንብረት ነው።
በሚስት ስም የተመዘገበው ንብረት ደግሞ አስቀድሞ በጋብቻ ውል የሚስት ስለሆነ የግል ንብረቷ ነው።
እርግጥ ነው በመካከላቸው ስምምነት ነበር። ግን በፍርድ ቤት ቀርቦ አልፀደቀም።
ግልፅ ሆኖ አንደኛው ወገን በህጉ ክፍተት በልፅጓል።
ግን ደሞ በሌላ መልኩ ፍትሐዊ ውሳኔ መስጠት የሚቻልበት መንገድ አለ?
792
0
2
1
×