በማኅበረ ቅዱሳን የሰሜን አሜሪካ ማእከል የኢንዲያና ግንኙነት ጣቢያ 5ተኛውን ሐዊረ ሕይወት አካሄደ::
የግንኙነት ጣቢያው ጽ/ቤት እንደገለጸው መነሻውን ከኢንዲያና ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በማድረግ ቺካጎ ወደሚገኘው የደብረ ጽዮን መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ቅዳሜ ጥቅምት 16 ቀን 2017 ዓ. ም በኢንዲያና ዙሪያ የሚገኙ ከ185 በላይ ምእመናንን ያሳተፈ መንፈሳዊ ጉዞ አካሂዷል።
በዕለቱ ምክረ አበውና በርካታ መርሐ ግብራት መከናወናቸው የተገለጸ ሲሆን በተጨማሪም ክርስቲያናዊ ቤተሰብ ምን መምሰል እንዳለበት የሕይወት ልምድና ትምህርት ተሰጥቷል ተብሏል፡፡
በመርሐ ግብሩ የአሜሪካ ማእከል ሥራ አስፈጻሚ አባልና አቅም ማጎልበቻና የሰው ሀብት ዋና ክፍል ኀላፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ፍስሐ እሸቱ፣ የኢንዲያና ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መልአከ ሰላም ቀሲስ ንጉሤ ገብሬ፣ ሰባኬ ወንጌል ብርሃኑ አድማስ፣ የማኅበረ ቅዱሳን ኢንዲያና ግንኙነት ጣቢያ አባላት እንዲሁም ምእመናን ተገኝተዋል፡፡
የግንኙነት ጣቢያው ጽ/ቤት እንደገለጸው መነሻውን ከኢንዲያና ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በማድረግ ቺካጎ ወደሚገኘው የደብረ ጽዮን መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ቅዳሜ ጥቅምት 16 ቀን 2017 ዓ. ም በኢንዲያና ዙሪያ የሚገኙ ከ185 በላይ ምእመናንን ያሳተፈ መንፈሳዊ ጉዞ አካሂዷል።
በዕለቱ ምክረ አበውና በርካታ መርሐ ግብራት መከናወናቸው የተገለጸ ሲሆን በተጨማሪም ክርስቲያናዊ ቤተሰብ ምን መምሰል እንዳለበት የሕይወት ልምድና ትምህርት ተሰጥቷል ተብሏል፡፡
በመርሐ ግብሩ የአሜሪካ ማእከል ሥራ አስፈጻሚ አባልና አቅም ማጎልበቻና የሰው ሀብት ዋና ክፍል ኀላፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ፍስሐ እሸቱ፣ የኢንዲያና ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መልአከ ሰላም ቀሲስ ንጉሤ ገብሬ፣ ሰባኬ ወንጌል ብርሃኑ አድማስ፣ የማኅበረ ቅዱሳን ኢንዲያና ግንኙነት ጣቢያ አባላት እንዲሁም ምእመናን ተገኝተዋል፡፡