ከወላጅ የመለየት ፍራቻ!
ከወላጅ የመለየት ፍራቻ ሁሉም ልጆች ላይ በሚባል ደረጃ የሚፈጠር እጅግ የተለመደ የእድገት ሂደት ነዉ። ከተወለዱ ከ6 - 8 ወራት ጊዜ ዉስጥ ይጀምራል፤ ከ10 - 18 ወር ላይ ከፍተኛ ደረጃ ይደርሳል፤ 4 ወይም 5 ዓመት አካባቢ ልጆች በራስ የመተማመን አቅማቸው ስለሚጨምር የመለያየት ፍርሀቱ በሂደት ይከስማል።
ልጆች ምን አይነት ባህርይ ሊያሳዩ ይችላሉ?
- ማልቀስ፣ ከመጠን በላይ መጣበቅ፣ ወይም ወላጆቻቸው ጋር ሲለያዩ ከመጠን ያለፈ ብስጭት።
- ሌሎች ሰዎች ሲያባብሏቸዉ አለመቀበል።
- ለአጭር ጊዜም ቢሆን ለብቻ መሆንን መፍራት
- የመለያያ ሰዐት ሲደርስ የህመም ስሜት (ሆድ ቁርጠት፣ ራስ ምታት) እየተሰማቸዉ እንደሆነ መናገር።
- የወላጅ እቅፍ ዉስጥ ወይም አጠገብ ካልሆኑ ለመተኛት መቸገር ናቸዉ።
ወላጆች ምን ማረግ አለባቸዉ?
- በአጭር ደቂቃ መለያየትን በመጀመር ቆይቸታዉን ቀስ በቀስ በማያስታዉቅ መልኩ መጨመር
- ወላጆች ተደብቆ መሄድን ማቆም። መለያያ ሰዐት ሲደርስ ለጥቂት ደቂቃ አዋርቶ እንደሚመለሱ ነግረዉ መሰናበትን ባህል ማድረግ።
- የወላጅን ፍርሀት ልጆች በቀላሉ ማወቅ ስለሚችሉ የፍርሀት ስሜትን ከፊት ላይ ማስወገድ እና በሙሉ የራስ መተማመን እና መረጋጋት መቅረብ
- የመለያያ ሰአት ላይ የልጆችን ምቾት ለመጨመር የሚወዱትን መጫወቻ ማቅረብ።
- የልጆችን የፍርሀት ስሜት በደንብ መረዳትና በሚያረጋጉ ቃላት መልስ መስጠት።
- ወላጆች በተቻለ መጠን እንመጣለን ባሉት ሰዐት ለመመለስ መሞከር እና የመዉጫ መግቢያ ሰአትን ቋሚ ማድረግ።
- በዚ ሁሉ ሂደት ዉስጥ ልጆች የሚያሳዩትን ለዉጥ እና ጥንካሬ በትንንሽ ሽልማቶች ማበረታታት።
ነገር ግን ምልክቶቻቸዉ ለተራዘመ ጊዜ ከቆዩና በእለት ተእለት እንቅስቃሴ ላይ እክል መፍጠር ከጀመሩ የባለሙያ እገዛ ሊያስፈልግ ይችላል!
ዶ/ር ሚካኤል ከፍያለዉ
(Sitota Mental Health Care & Rehabilitation Center)
@melkam_enaseb
ከወላጅ የመለየት ፍራቻ ሁሉም ልጆች ላይ በሚባል ደረጃ የሚፈጠር እጅግ የተለመደ የእድገት ሂደት ነዉ። ከተወለዱ ከ6 - 8 ወራት ጊዜ ዉስጥ ይጀምራል፤ ከ10 - 18 ወር ላይ ከፍተኛ ደረጃ ይደርሳል፤ 4 ወይም 5 ዓመት አካባቢ ልጆች በራስ የመተማመን አቅማቸው ስለሚጨምር የመለያየት ፍርሀቱ በሂደት ይከስማል።
ልጆች ምን አይነት ባህርይ ሊያሳዩ ይችላሉ?
- ማልቀስ፣ ከመጠን በላይ መጣበቅ፣ ወይም ወላጆቻቸው ጋር ሲለያዩ ከመጠን ያለፈ ብስጭት።
- ሌሎች ሰዎች ሲያባብሏቸዉ አለመቀበል።
- ለአጭር ጊዜም ቢሆን ለብቻ መሆንን መፍራት
- የመለያያ ሰዐት ሲደርስ የህመም ስሜት (ሆድ ቁርጠት፣ ራስ ምታት) እየተሰማቸዉ እንደሆነ መናገር።
- የወላጅ እቅፍ ዉስጥ ወይም አጠገብ ካልሆኑ ለመተኛት መቸገር ናቸዉ።
ወላጆች ምን ማረግ አለባቸዉ?
- በአጭር ደቂቃ መለያየትን በመጀመር ቆይቸታዉን ቀስ በቀስ በማያስታዉቅ መልኩ መጨመር
- ወላጆች ተደብቆ መሄድን ማቆም። መለያያ ሰዐት ሲደርስ ለጥቂት ደቂቃ አዋርቶ እንደሚመለሱ ነግረዉ መሰናበትን ባህል ማድረግ።
- የወላጅን ፍርሀት ልጆች በቀላሉ ማወቅ ስለሚችሉ የፍርሀት ስሜትን ከፊት ላይ ማስወገድ እና በሙሉ የራስ መተማመን እና መረጋጋት መቅረብ
- የመለያያ ሰአት ላይ የልጆችን ምቾት ለመጨመር የሚወዱትን መጫወቻ ማቅረብ።
- የልጆችን የፍርሀት ስሜት በደንብ መረዳትና በሚያረጋጉ ቃላት መልስ መስጠት።
- ወላጆች በተቻለ መጠን እንመጣለን ባሉት ሰዐት ለመመለስ መሞከር እና የመዉጫ መግቢያ ሰአትን ቋሚ ማድረግ።
- በዚ ሁሉ ሂደት ዉስጥ ልጆች የሚያሳዩትን ለዉጥ እና ጥንካሬ በትንንሽ ሽልማቶች ማበረታታት።
ነገር ግን ምልክቶቻቸዉ ለተራዘመ ጊዜ ከቆዩና በእለት ተእለት እንቅስቃሴ ላይ እክል መፍጠር ከጀመሩ የባለሙያ እገዛ ሊያስፈልግ ይችላል!
ዶ/ር ሚካኤል ከፍያለዉ
(Sitota Mental Health Care & Rehabilitation Center)
@melkam_enaseb