ታጋይ አምሓራ


Гео и язык канала: Эфиопия, Английский
Категория: Новости и СМИ


ነፃነት በትግል እንጂ በልመና አይገኝም !
መረጃ፣ ጥቆማ፣ ሀሳብና አስተያየት ለማድረስ @TheGreatHQ ን ይጠቀሙ።

Связанные каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Английский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


ከፋተኛ ትኩረት!!💥💥

በአማራ ፋኖ ትግል ውስጥ በየደረጃው ያሉ አመራሮች በተለይም በሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ሚናቸውን ይወጡ ዘንድ ኃላፊነት ያለባቸው ሁሉ ፤የድል ውሎ ዘገባ፡የሕዝብ ግንኙነትና የፕሮፓጋንዳ ሥራዎች ላይ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል።የትጥቅ ትግል ሕይወት እየተከፈለ በሚደረግ ብሎም በጎንሽ ጉዳት ሕዝባችን ከፍተኛ ችግር እየተጋፈጠ ያለበት ነው።

የሠራዊቱን ጠንካራ ጎን እስከ ትጥቅ አይነትና መጠን በፎቶ ብሎም በየአደረጃጀቱ ማሳየቱ ጥቅሙ ምንድነው? በቅርቡ እንዲህ እናደረጋለን እንዲህም ተዘጋጀተናል አይነት እቅዶችን ማሳወቁስ ይጠቅማል? ሠራዊቱ የተሠማራበት ወይም ስልጠና የሚወስድበት ቀጠና እና ቦታ ላይ ቲክቶክ መሥራት እና መሰል መረጃ ሰጪ አካሄዶች በጥብቅ ሊታዩ ይገባል።

የመረጃ እና ደህንነት መዋቅሩ አጠቃላይ የፖለቲካ እና የሕዝብ ግንኙነት ሥራው ከትግሉ ውጤታማነት አንፃር እንዴት እየተሠራ ነው? የሚለውን መገምገምና ልዩ ልዩ ፕሮቶኮሎችን አውጥቶ ማስተገብር ይኖርበታል።የአባላት ጓዳዊ ግንኙነቶች በስልክም ሆነ በሌላ መንገድ ሲደረጉ የተቋሙን ምስጢር ለሶስተኛ ወገን አሳልፎ በሚሰጥ መልኩ እንዳይደረጉ ከፍተኛ ክትትልና ጥበቃ ያስፈልጋል። ለዚህም መመሪያ ያስፈልገዋል።

በራስ ተነሳሽነትና በጀብደኝነት አልያም በደስታ የውሎ ጉዳዮችና ሌሎችንም ኩቶች በማሕበራዊ ሚዲያ ሲፅፉ፤ ከመረጃ አንፃር እና ከጥቅል ትግሉ አብርክቶ መመዘን እጅግ ጠቃሚ ይሆናል። በትግል ሂደት የሚፈጠሩ አለመግባባቶች ሲኖሩ በንዴትና በስሜት ወደ ማሕበራዊ ሚዲያ ይዞ መውጣትም መረጃ ሰጪነት ይሆናል። ከዚያ ይልቅ በመርሕ እና አሠራር ተቋማዊ በሆነ መልኩ እየፈቱ መጓዝ ለጋራ ደህንነትም ለተቋም ግንባታና ድል ያበቃል።

ድል ያለመሰዋዕትነት የማይመጣ ቢሆንም በተቻለ መጠን በአነሰ መሳዋእትነት የበዛ ድል መቀዳጀትን ታሳቢ ያደረገ ትግል ማድረግ ይጠበቃል። ይሄ የሚሆነው ደግሞ ሁሉም ለጋራ ደህንነት እየተጨነቀ ፤ጠላት ላይ ቀድሞ እያቀደ ሁለንተናዊ ብልጫ ወስዶ መታገልን ምርጫው ሲያደርግ ነው።

አንድ አማራ💪💪
አንድ ፋኖ💪💪

@Shamal Dawit

 ታጋይ አምሓራ
ነፃነት በትግል እንጂ በልመና አይገኝም!


ለ፪ኛ ግዜ ከድሮን አረር ተረፍኩ!

በፈጣሪ ፈቃድ ከሕዝባዊ በትንሳኤው ጋር አብረን እንምንነሳ አምናለሁ።

በዓሉን ላከበራችሁ በሙሉ እንኳን አደረሳችሁ!

[የምታዩት ፍርስራሽ ንፁሃን አማሮች አጠገባችን በድሮን የተገደሉበት ቤት ነው]

✍አርበኛ ጥጋቡ መኮነን

ይቺ ምስል ያዙልኝማ አርበኛ ጥጋቡ መኮነን በተዓምር የተረፈበትን የድሮን ጥቃት ነው እንግዲ 120 ንፁሃንን ብቻ ተጨፈጨፏ ብሎ ጥቃቱ ከመፈፀሙ አንድ ሰዓት ሳይሞላ በመግለጫ የተነፋነው። ወዳጄ እውነት እውነቱን አውርተን ለቀጣይ እንዳይደገም ብናወጋ ይሻላል። መቃብሩን አንደብቀው!!

@ አንድ አምሐራ ዕዝ ሚዲያ


የአገዛዙ አሽከሮች በዓላት በመጣ ቁጥር የክፍለጦራችን ም/ሰብሳቢ አርበኛ አስማማዉ ሞላ  ቤተሰቦች እያሰረ ማሰቃየት የዘወትር ተግባሩ አድርጎታል። የማይዝገዉ ብረት አስሜ ግን ይሄን ብሏል👇
◈◈◈◈

ሁልጊዜ በእኔ ምክንያት በበዓላት ቀን በእስር ቤት ትሰቃያላችሁ ስቃያችሁ ያመኛል ግን የወጣሁለት ዓላማ ለእናንተ አይደለም የወጣሁለት ዓላማ እንዲጠፋ በአዋጅ ለታወጀበት የአማራ ህዝብ ነው ከዚህ ህዝብ መካከል እናንተ ትገኛላችሁ እና የአማራ ህዝብ ነፃ ሲወጣ ነፃነታችሁን ታረጋግጣላችሁ።

በእስር ቤትም ብትሆኑ መልካም የትንሳኤ በዓል🥰

12/8/2017 ዓ.ም
አስማማው ሞላ አጥናፉ የቀኝ ጌታ ዮፍታሔ 6ኛ ክ/ጦር  ም/ ሰብሳቢ


የአደረጃጀት መረጃ በዕለተ ፋሲካ!

ድርጅታችን ካሉት ግዙፍ ክፍለጦሮች አንዱ የሆነው 4ኛ ክፍለ ጦር የነበሩበትን ውስጣዊ ችግሮች የአማራ ፋኖ በጎጃም ከፍተኛ አመራር የሆኑት ዶ/ር ጋሹ ክንዱ እና አርበኛ ምናልባት ይታየው በተገኙበት ጥልቅ ግምገማ ካደረገ በኋላ በዛሬው ዕለት የአመራር ሪፎርም በማደረግ አጠናቋል።
በዚህ መሰረት፦
1. ሰብሳቢ..........................ፋኖ ግርማው አየለ
2. ምክትል ሰብሳቢ...............ፋኖ አመሃ አይሸሽም
3. የጽህፈት ቤት ሀላፊ...........ፋኖ አደራጀው አድማስ
4. ህዝብ ግንኙነት.................ፋኖ ያዕቆብ ጌታሁን
5. ፓለቲካ ዘርፍ ሀላፊ.............ፋኖ አጃናው ስሜነህ
6. አደረጃጀት ዘርፍ ሀላፊ.........ፋኖ ዳዊት አይችሌ
7. ፋይናንስ ሀላፊ....................ፋኖ ሸጋው አለም
8. ወታደራዊ አዛዥ................ፋኖ 50 አለቃ ተገኜ ደጀኔ
9. ምክትል ወታደራዊ አዛዥ........ፋኖ ሻለቃ ጌጡ አለሙ
10. ዘመቻ መምሪያ ሀላፊ........... ፋኖ ቻሌ መንግስቴ
11. ም/ዘመቻ መምሪያ...............ፋኖ ሳሙኤል አታላይ
12. ሎጅስቲክ መምሪያ ሀላፊ...........ፋኖ ወርቁ አድባሩ
13. ስልጠና መምሪያ ሀላፊ.......ፋኖ ቻሌ አበበ
14. ኦርዲናንስ.........ፋኖ 10 አለቃ ሀብታሙ ይበልጣል
15. ጤና መምሪያ ሀላፊ.........ፋኖ ዶ/ር ይታየው ገበየሁ
16. ወታደራዊ አስተዳደር..........ፋኖ ጌትነት አበባው
17. የሰው ሃይል.......................ፋኖ ሻለቃ አዳነ በቀለ
18. ቀጠና ትስስር....................ፋኖ አወቀ ሞላ
19. መረጃና ደህንነት................xxxxxxx

በመሆን ተመድበዋል።

አዲስ ትውልድ፣አዲስ አስተሳሰብ፣አዲስ ተስፋ

[አማራ ፋኖ በጎጃም]
ሚያዝያ 12/2017 ዓ.ም

የአማራ ህዝብ የነፃነት ሻማዎች ፤ የኢትዮጵያ ህዝብ የሰላም ተስፋዎች በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ


ከአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር
     የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት

     ለመላው የክርስትና ዕምነት ተከታዮችና ለመላው የፋኖ ሰራዊታችን እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው አደረሳችሁ።

  በተለያዩ ፈታኝ ሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ ተግዳሮቶችን ተቋቁሞ አመርቂ ድል እያስመዘገብን ባለበት በዚህ ጊዜ በአንድነትና በመተሳሰብ፣በመቻቻልና በማስተዋል፣በመደጋገፍና በትህትና፣የዕንከን ቋጠሮዎችን ፈተን አጠቃላይ ማህበረሰባዊ የመጥፋት አደጋ በመታደግ የሚቀጥለውን ዓመት ትንሳኤ ስናከብር ምድራዊ መከራውን ቀልብሰን እንዲሆን ከምኞት የዘለለ ገቢራዊ ርምጃ በመራመድ ጭምር ይሆናል።

   የውስጥ ጉዳያችን የመፍቻ ቁልፍ "አንድነታችን" ነውና ለሁሉም የፋኖ ሰራዊት የአንድነት ጥሪ እናስተላልፋለን።

     መልካም የትንሳኤ በዓል!
    የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር
               አፋአጎ


⛪️✝️ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ፣ ለሁሉም የአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች ፣ ለመላው የአማራ ፋኖ አባላትና አመራሮች ፣ ለብርጌዳችን አባላትና አመራሮች እንዲሁም ለመላው የአማራ ህዝብ እንኳን ለጌታችንና ለመድሃኒታችን ለኢሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ(ፋሲካ) በዓል አደረሳቹህ አደረሰን!!

ትንሳኤ ማለት ድል ነዉ፣ ትንሳኤ ማለት ስኬት ነዉ፣ ይህን ድልና ስኬት ለመየት ከትንሳኤ በፊት ስቃይ አለ ፣ ከትንሳኤ በፊት ግርፋት ስቅላት አለ፣ ከትንሳኤ በፊት መረረዋን ፅዋ መጎንጨት አለ ፣ ከትንሳኤ በፊት እርዛት አለ ፣ ከትንሳኤ በፊት በእሾህ አክሊል መሰቃየት አለ፣ከትንሳኤ በፊት ለሐቅና እዉነት መቆም አለ ፣ከትንሳኤ በፊት ስጋዊ አምሮትን ስጋዊ ስሜትንና  ስጋዊ ፍላጎትን መግታት (መተው)  አለ፣ መወገርና መሰደብ አለ።ስኬት ያለ ስቃይ ፣ ድል ያለ መከራ ፣ ጀግንነት ያለ ፈተና እንደማይታሰብ  ሁሉ ይህ የትንሳኤ በአል ምስክራችን ነው። የአማራ ህዝብ የደረሰበትን መከራ፣ ስቃይ ፣ ግርፋት፣ መሳደድና መገደል በማስቆም የአማራን ትንሳኤ  ለማብሰር የግድ ከትንሳኤ በፊት ያሉትን የመከራና ስቃይ ጊዜያት ማለፍ አለብን።

ስለሆነም በጭቆና ቀንበር ውስጥ ያለኸው ህዝባችን ሆይ በኛ መራር አይተኬ የህይወት መስዋትነት ይህን ስርዓት ለአንዴና ለመጨረሻ ግዜ በተባበረ ክንዳችን አስወግደን የአማራን ህዝብ ብሎም የኢትዮጵያን ህዝብ ትንሳኤ እስከምናበስር ከጐናችን ትሆን ዘንድ ጥራያችንን እናቀርባለን።

የአማራ ህዝብ ሰቆቃ አንገብግቧቹህ በዱር በገደሉ ለአማራ ህዝብ የመነናችሁ የአማራ ፋኖ የትግል ጎዶቻችን እና ታላቁ የአማራ ህዝብ ሆይ በድጋሚ እንኳን ለትንሳኤ በዓል አደረሳቹህ።

አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ! አዲስ ተስፋ!!!
ድላችን በተባበረ ክንዳችን!!!
ድል ለአማራ ፋኖ!!!

የአፋጎ ቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴ ፮ኛ ክፍለ ጦር ንጉስ ተከለሃይማኖት ብርጌድ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ
ፋኖ ባዬ ሽፈራው ( ቀኜ)


የትንሳኤ መልእክት ከሻለቃ ዝናቡ ልንገረው
▢▢▢▢▢▢▢▢▢▢▢▢▢▢▢▢▢▢▢

ዛሬም ትንሳኤ የሌላት ሀገር 'የአምላኳን ትንሳኤ' ደጋግማ እያከበረች ነው። "ሕዝባችን የሕማማቱ ዘመን አልፎለትና ተሽሮ፣ ሀገራችንም የራሷን ትንሳኤ እንደ አምላኳ ትንሳኤ ታከብር ዘንድ" የአማራ ፋኖ ሰራዊት አስፈላጊውን ውድ ዋጋ ሁሉ እየከፈለ ነው። በዚህም ለጠላት ሰሞንኛ እቅድ መገታት መላው ሰራዊታችንና ህዝባችን ለምታደርጉት አኩሪ ገድል ምስጋናችንን እናቀርባለን።

✝️
ክርስቶስ አላዛርን ከሙታን መቃብር ውስጥ ሲያስነሳ ‹‹ድንጋይ ማንከባለሉ›› የሰወች ስራ ነበር፡፡ ዳዊት ሊጠጣ የፈለገውን ውሐ ለማምጣት ሲሉ የተጋደሉለት ወታደሮች "መስዋዕትነታቸው ፅድቅ ሁኖ እንደተቆጠረላቸው የተነገረን" ክርስቶስን በሚያመልኩ የክርስትያኖች መፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ ነው። እግዚአብሔርም "ሳኦልን የጣለው በዳዊት ጠጠር" ነው። በደልንና ግፍን እያዬ ዝም ማለትም በአምላክ ፊት እንደሚያስቀጣ ሲነግረን "ፈሪ አይፀድቅም" ብሎ የገሰፀንም ይህ ቅዱስ መፅሐፍ ነው። እግዚአብሔርን 'ና ዉረድ' በማለት ብቻ የሚመጣ ለውጥም የለም። ይልቁንስ አንድም ሁለትም ሁነን ተሰልፈን በጀመርነው ተጋድሎ ውስጥ "እግዚአብሔርን ሃይልህ በእኛ ላይ ይደር" እንበለው። በስግደት ብቻ የምናገኘው ለውጥ ቢኖር ኑሮ በሰዓታት ልዩነት "ኪርያላይሶ" እያልን ለአምላክ ክብር እየሰገድን በቤቱ ብንኖር ደስ ባለን ነበር። "በተማፅኖ ብቻ እንደማንድን፣ በትግልም ብቻ እንደማንጥል" ተነግሮናል።

✝️
ትግሉ የመኖር ዋስትና አጥቶ፣ የሕልውና አጣብቂኝ ውስጥ የወደቀ የግፉኣን ህዘብ ነዉ። የምትታገልለት ዓላማን "ቅዱስነት መረዳትና ማወቅም" በፅናት ለመቆም ይበጃል። ከዛሬ 500ዓመት በፊት አባ ባሕሪይ "..ሀገሬ ጠፋች" በሚለው ድርሰታቸው እንደነገሩን በቅርቡም ጀኔራል አሳምነው ፅጌ "..ከዛሬ 500ዓመት በፊት ከነበረው የከፋ እልቂት ህዝባችን ላይ ተደግሷል" ብሎ እንዳሳሰበን እየሆነ ያለው ሁሉም ቀድመው የነቁት የነገሩንን ነው። ክርስቶስ በክርስትና ውስጥ ያሳዬንን ትልቁ ትምህርትም "ቤዛነት - ለሚወዱት ራስን አሳልፎ መስጠትን" ነው። ለሀብት፣ ለልጅ፣ ጤናም ሆነ ተያያዥ ምክንያቶች በመስገብገብ፤ ይሄንን ህዝብ ለውርደት በሚዳርግ ሂደት ውስጥ በጠላትነትም ሆነ ዝምታ ውስጥ መቆም 'ቤዛ' የሆኑትን ደም እንደማርከስና የህዝባችንን የትንሳኤ ቀን እንደማዘግየት እንቆጥረዋለን። ስለሆነም በየትኛውም የከፍታም ሆነ ዝቅታ ውስጥ የሚገኝ ሁሉም የአማራ ህዝብ ለሕልውና ትግሉ የራሱን አበርክቶ እንዲያደርግ ጥሪ እናቀርባለን።

✝️
ለአማራ ህዝብ የማይተመን ውድ ዋጋ ሁሉ በመክፈል 'ቤዛነትን ያሳያችሁን ፋኖዎች' ትግላችሁን ለትንሳኤ እንደምናደርሰው ቃል እየገባን መላው የፋኖ ሰራዊታችን በዓልን በወትሮ ዝግጁነትና ራሳችሁን ለአየር ላይ ጥቃት በማያጋልጥ መልኩ እንድታሳልፉ አሳስባለሁ።

የትንሳኤ በዓሉን ለምታከብሩ ሁሉ እንኳን አደረሳችሁ!

      ሻለቃ ዝናቡ ልንገረው ደለለ
የአፋጎ ም/ሰብሳቢና ወታደራዊ መምሪያ አዛዥ


በአማራ ፋኖ በጎጃም ጎጃም አገዉ ምድር ፫ኛ ክ/ጦር ፲/አ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ የተላለፈ የእንኳን አደረሰን መልዕክት!!

በመከራ ዉስጥ የነበረዉን የሰዉ ልጅ ለማዳን ቃል ከሰማያት ወርዶ ከድንግል ማሪያም ማህፀን አድሮ ከስጋዋ ስጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ሰው ሆኖ ተወለደ።  በምድርም ቀስበቀስ እንደ ሰው አደገ እየተመላለሰም ፍቅርን ሰበከ፣ ሰላምን አወጀ፣ አስተማረ፣ ፅድቅን ሁሉም ሰራልን። ነገር ግን ቅድመ ጠላቱ ለአዳም የሆነዉ ዳቢሎስ በጻፈው የዕዳ ደብዳቤ በፈሪሳዊያን  አድሮ ነገርን ሁሉ እያጣመመ ቀጥ ያለዉን ኢየሱስን በተጣመመ መዝገብ ከሰሰዉ። ኢየሱስም ሁሉንም ነገር ስለ ሰዉ ልጅ መዳን ሲል ሁሉንም ለመቀበል ፈቅዶ ኖሮ በትግስት ተቀበለዉ። ዲያብሎስም የአስቆሮጦሱ ይሁዳን ተጠቅሞ እየሱስን በሠላሳ ዲናር ለሄሮድስ እንዲሸጠዉ በማድረግ  በሮም ወታደሮች  እንዲያዝ አደረገ። ኢየሱስም ምንም ጥፋት ሳይኖርበት መከራን ተቀበለ በመስቀልም ላይ ተሰቀለ  ሞተ ተቀበረም። በዕለቱ  ታላላቅ ታምራት ተከሰቱ፤ ፀሐይ ብርሃኗን ከለከለች፣ ጨረቃም ደም ለበሰች፣ ከዋክብት ረገፉ የቤተ መቅደስ መጋረጃ ከሁለት ተከፈለ። በሦስተኛዉም ቀን ግን ኢየሱስ ሞትን ድል አድርጎ ተነሳ።

ነገረ ፋኖ፦
አማራ በሀሰት ትርክት የተከሰሰበትን የእዳ  ደብዳቤ ለመቅደድ  አዲሱ ትዉልድ በአዲስ አስተሳሰብ አዲስ ተስፋ ይዞ ከአማራ መከራ መከራዉን  ከሞቱም ሞትን ወስዶ ከግፍ ፋኖ ሁኖ ተወለደ።

ትላንት ከትላንት በፊት የአማራን ራስ ቅል በሠላሳ ብር ለፋሽስት ጣሊያን የሸጡት ቅድመ ጠላቱ ለአማራ የሆኑ ኢትዮጵያዊ ይሁዲዎች  ለብዙ አስርት አመታት አስፍተዉ የቆፈሩትን  የአማራነት መደምሰሻ  የመቃብር አፍ ለመዝጋትም ትግሌ እስከ ቀራኒዮ ድረስ ነዉ ሲል ቆርጦ ተነሳ።
ይህ ከአዲሱ ትዉልድ ተመዞ፣ በአዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ ሰንቆ የተነሳዉ ፋኖም ሁለት ዓመት ባልሞላ የትግል ዕድሜዉ የጠላትን ተስፋ አጨልሟል።

በዚህ የተደናገጡ እና ተስፋ የቆረጡ መነሻቸዉ ክፋት፣ ጥላቻ እና ፀረ አማራነት የሆኑ የዘመናችን ፈሪሳውያንም ነገር እያጣመሙ  ፋኖን ባልዋለበት ዋለ፣ ያልሰራዉንም ሰራ፣ በሚል እየከሰሱት ይገኛሉ።  ቢሆንም ዓላማችን ግልፅ ነዉ። ሁሉንም ፈተና ስለ አማራ ሲባል ተቀብለን በሞታችን አማራ የግፍ መቃብሩን  ፈንቅሎ እንዲነሳ አድርገናኣ፤ እኛ አልፈን ነገ በትውልድ የአማራን ትንሳኤ እናመጣለን። 

በድጋሜ እንኳን ለጌታችን ለመድኅኒታችን ለእየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል አደረሰን/አደረሳችሁ!!!

አዲስ ትዉልድ፣
አዲስ አስተሳሰብ፣
አዲስ ተስፋ!!!

የአማራ ፋኖ በጎጃም ጎጃም አገዉ ምድር ፫ኛ ክ/ጦር ፲/አ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ

ሚያዝያ 12/2017 ዓ/ም


ሰሞነኛ የአገዛዙ ሰራዊት እንቅስቃሴ!!💥

ደቡብ ጎንደር የተወሰኑ ቀጠናዎችን በአድማ ብተና ለመሸፋን ምስራቅ እዝ ኮርን ወደ  አዴት እና መራዊ ለመሳብ  ታስቦ ነበር አንድ እርምጃ ሳይራመዱ ነገር ተበላሽቶባቸዋል።

አዊ ዞን ያለው ምስራቅ ዕዝ ኮር ሰሜናዊ አዊ ወረዳወች፣ሰከላ፣ ቡሬ እና ሽንዲን እንዲይዝ ፋኖተሰላም ላለው 6ኛ ዕዝ ኮሮች ድጋፍ እንዲሰጥ እቅዱ አሁንም እንደቀጠለ አንድ አምሐራ ዕዝ ከአፈንፋኝ የመረጃ ምንጮች መረጃ ተቀብላለች።

ምስራቅ ጎጃም የተሰማሩት ምዕራብ ዕዝ  403ኛ ኮር አባይ በርሃ ዙሪያውን እንዲሰማራ ሚሊሻ እና አድማ ብተና መሃሉን እንዲቆጣጠር፣ ማርቆስ  ያለው ድብልቅ ሃይል የ32 ኛ ክፍለጦር ጨምሮ የ6ኛ ኮር ወደ ስናን ይዞ፣ ቁይ እስከ ዋብር ሊሸፍን ፣ የአማኑኤሉ ወደ ደንበጫ ድጋፍ  እንዲሰጥ፣ ስምሪት ሰጠው እንቅስቃሴ ጀምረዋል።

ይሄም ውጊያውን ለመሰብሰብ የታቀደ ነው።

እኛም እንደአመጣጣቸው እንቀበላቸው አለን እንዳካሄዳቸው እንሄዳለን💪💪

  @አንድ አምሐራ ዕዝ ሚዲያ


ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን
~በዐቢይ ኀይል ወሥልጣን
• አሰሮ ለሰይጣን
~አግአዞ ለአዳም
• ሰላም
~እምይእዜሰ
• ኮነ
~ፍስሐ ወሰላም


ታጋይ አምሓራ
ነፃነት በትግል እንጂ በልመና አይገኝም!


Репост из: አንድ አምሐራ ዕዝ💪
እኛ 24 ሰዓት በየአካባቢው የት አካባቢ የድሮን ቅኝት አለ የጥላት እንቅስቃሴ ምን ይመስላል እያልን የጥንቃቄ መረጃዎችን ለወገን ለማድርስ ደፋ ቀና እያልን መከራችንን እንበላለን እናንተ ፎቶ እየተነሳህ እዚህ ነን እያልክ ትላላጣለህ።

እሺ ትግል ነው እና እንተወው በነገው የጌታችን መድሀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል ወቅት ጤና ተቋማት፣ ትምህር ቤት፣ ቀበሌ አስተዳደር፣ ካንፕ ላይ...በአጋላጭ ሁኔታ በህብረት በመሰብሰብ ከዛም አልፎ ተሽሞንሙነህ ያለህበትን ቦታ ሳቀይር ከጀርባህ የት እንዳለህ የሚያሳብቅ ፎቶ immediately የምትለቅ ቡድን በራሳህ እና በወንድምህ ሞት እንደፈረድክ ቁጠረው።

በደረሰን ታማኝ የመረጃ ምንጮች በነገው ዕለት ብቻ በተመረጡ ሶስት ቦታዎች የድሮን ጥቃት ይፈፀማል። መረጃውን በውስጥ ለሚመለከተው አካል አድረሰናል።

እነ ሲሳይ ሳተናው፣ ስዩም ይዘንጋው ድንቁ፣ Girma .... ይህ መልዕክት በደንብ ይመለከትሃል።የገና በዓል ላይ የተፈጠረው ስህተት እንዳይደገም።

እንደ ምሬ፣እንደ ዘሜ፣እንደ ሐብቴ፣እንደ ደሱ ተወዳጅ ሌሊት ይሁንላቹ🙏🙏🥰🥰

....አንድ አምሐራ ዕዝ ሚዲያ
11/17


እስቲ ተጠንቀቁአቸው👇👇👇

እነዚህ የfb አካውንቶች በአማራ ፋኖ ስም የተከፈቱ የብልፅግና ዲዲታል የሚዲያ ናቸው። የፋኖ አደረጃት አንድ አለመሆኑን እንደ እድል ተጠቅመው አንዱን የፋኖ አደረጃጀት በመደገፋ በሌላኛው ላይ የሚዘምቱ በመገርሰስ ፍፃሜ ላይ የሚገኘውን ብልፅግናን ለማዳን የዘመቱ የሚዲያ ሚሊሻዎች ናቸው።

በአማራ ስም የተከፈቱ የብልፅግና ዲዲታል ሚዲያዎች  በፋኖ ስምና በኢትዮጵያ ስም የሚነግዱ አማራ ጠል የብልፅግና ዲዲታሎች  ለጊዜው 45ቱን  የባንዳወች ስም ዝርዝር እነሆ፦
1.  Yotor amhara
2. ገብርዬ ገብርዬ, 
3.  Ethiopiam renaissance
4. አማራው የማይሰበረው
5. የፍቅር መንገድ
6. Alazar zeleke
7. Natan amhara
8.  ፍታውራሪ ገበየሁ
9. ቤዛ ብሩክ/ብሩክ ቤዛ
10. kelemu taddele
11. ሰውመሆን የእኔሰው
12. Lula kebede
13. ጥንቅሽ
14. ክብረ አማራ
15. ግዜ ተሻለ
16. Firewu teshale
17. One ethiopia
18. ዮቶር አማራ
19. ዝምተኛው ንጉስ መደመር
20. ለሁሉም አለው ጌዜ
21. አማኑኤል አወቀ
22. ሰላም ለሃገሬ                                                            23. Tibebe solomon dawit
24. አማራ ጠቅላይ ግዛት ፋኖ
25. ቡርቧክስ በጌምድር
26. መልከ ሓራ
27. Gebre mariam
28. Tana press
29. ተዋበች ጎንደር
30. ነገረ አማራ
31. ሀበሻዊት ነኝ የአባይ
32. Gasha medina
33. Indo Amhara እና
34. Blen Getachew
35. Gucher man
36. Nardos page
37. ሰላም በፍቅር
38. Ethiopian Tim
39. ቴዲ ጤና ይሰጥልኝ
40. አቦል መረጃ
41. Ethio peace
42. ስሜነህ ደስታ
43. sela markose
44. Werku Abay
45. ከሰው post ናቸው፡፡

ቀሪወችን ጨምሩበት.....

ታጋይ አምሓራ
ነፃነት በትግል እንጂ በልመና አይገኝም!


እንኳን ለጌታችን ለመዳኒታችን ለእየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤እያልሁ በዓሉን ስናከብር የጠላትን እንቅስቃሴ እየተከታተልንና ከድሮን ተጋላጭ ባልሆነ ቦታ ሁነን ብዓሉን እናሳልፍ።ጥንቃቄ ከሁላችንም አይለየን።

ከአማራ ፋኖ በጎጃም የጎጃም አገዉ ምድር ክ/ጦር ቢትወደድ አያሌዉ መኮነን ብርጌድ ህ/ግንኙነት ሃላፊ ፋኖ Abebe amlakie(ማንከቻዉ)

ታጋይ አምሓራ
ነፃነት በትግል እንጂ በልመና አይገኝም!


የትንሳዔውን በዓል የትግላችን የድል ዋዜማ የህዝባችን ትንሳዔ መዳረሻ ላይ ሆነን እናከብረዋለን‼️

   የተከበርከው የአማራ ህዝብ ሆይ ብዙ መከራ፣ ብዙ ጭንቅ ብዙ ሰቆቃዎችን እያሳለፍክ እንደሆነ በትግል ሜዳ ያለነው ለህልውናህ መፅናት የወጣነው ልጆችህ በግልፅ እንረዳዋለን።

ባለፉት ዘመናት መንግስታት ተፈራርቀው የተጫነብህ እዳና በገፍ የተፈፀመብህ ግፍም ለነፍጥ ትግል አስወጥቶን የጀመርነው ተጋድሎ ፍሬው እያማረና እየጎመራ የድል ዋዜማ ላይ እንገኛለን።

ጌታችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከረጅም መከራና ህማም በኋላ ድል ላደረገበት የትንሳዔው በዓል መላውን ህዝባችንን እንኳን አደረሳችሁ ስንላችሁም  አሁን ካለንበት ህዝባዊ መሳደድ፣ የመገደልና እልቂት የተሻገረ ህዝባዊ  ፈውስን በታላቁ የአማራ ህዝብ ሁለንተናዊ ድጋፍና በኛ በልጆቻችሁ የፀና ትግል እንደምናበስራችሁ በመተማመን ነው።

ለህዝባችን ድልና ስኬት የሚከፈለውን ዋጋ ሁሉ ከፍለን  ትውልዳዊ አደራችንን እንወጣለን፤ ታሪካችንንም በክንዳችን እንፅፋለን።

መልካም የትንሳዔ በዓል ይሁንላችሁ

ዋርካው ምሬ ወዳጆ
©የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ)
ዋና ሰብሳቢ


#ከጎጃም_አገዉ_ምድር_ክፍለ_ጦር
ተወርዋሪ ኮማንዶዎች እና ልዩ ግዳጅ ፈፃሚወች።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
         #የተላለፈ_መልዕክት

ለመላዉ የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለጌታችን መዳኒታችን ለእየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ (ፋሲካ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
📌የተከበራችሁ በየጫካውና በእየገደሉ እየተዋደቃችሁ የምትገኙ የፋኖ አባላት ሆይ ኢየሱስ አዳምን ለማዳን መሞቱ መቁሰሉ ግድ ነበር  ፋኖም የአማራን ህዝብ ለማዳን መሞት መቁስል ግድ ነው።

📌ትንሳኤውን ለማየት ስቅለትን ማለፍ ግድ ነበር፤    የአማራን ትንሳኤ ለማዬት ስቅለቱን፣ሞቱን መከራውን ማለፍ ግድ ይለናል።

📌ይሁዳ ፈጣሪውን ካደ ያለንስሀ ሞተ፤ የሞት ሞትንሞ ሞተ፤ ጴጥሮስ ፈጣሪውን ካደ ተጸጸተ ንስሀም ገባ ከሞት ወደ ህይወት ተሸጋገር አማራን ክዳችሁ የአማራን ህዝብ ለባርነት በገንዘብ፣በስልጣን  የሸጣችሁ ባንዳ ሚኒሻ፣ፖሊስ፣አድማ በተኝ እና የብልጽግና አመራሮች እንደ ጴጥሮስ ወደ ልባችሁ ተመልሳችሁ ተጸጽታችሁ ከህዝባችሁ ጎን እንድትቆሙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

           #ኮማንዶ ፲/አ አቢ አስፈራዉ

የግዙፉ የጎጃም አገዉ ምድር ክ/ጦር ተወርዋሪ ኮማንዶዎች የልዩ ዘመቻ ጠርናፊ


ከአማራ ፋኖ በሸዋ የፋሲካ በዓልን አስመልክቶ የተሰጠ የእንኳን አደረሳችሁ መግለጫ
ፋሲካ የክርስትና እምነት መሠረት የሆነ ጌታችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጎ ትንሳኤዉን ለአለም ያበሰረበት እጅግ ድንቅ በዓል ነው።

ብርሃን በጨለማ ላይ፣ ሕይወት ደግሞ በሞት ላይ ድልን የተጎናጸፈበት እለት ነው። ከፋሲካ በፊት ነቢዩ ኢሳይያስ በመንፈስ ሀይል አስቀድሞ እንደተናገረዉ በእውነት ደዉያችንን ተቀበለ፡፡ ሕመማችንንም ተሸከመ… ስለ መተላለፋችን ቆሰለ… በማስጨነቅና በፍርድ ተወሰደ… ብሎ ሊፈጸም ያለዉን ግፍና ሰቆቃ ተናገረ (ኢሳይያስ 53፥5-7)። ይህ ነቢያዊ ትንቢት በክርስቶስ ትንሣኤ መቋጨቱን ሲያስረዳ ደግሞ… ነፍሱን ስለ-ሀጢያት መስዋእት ካደረገ በኋላ ዘሩን ያያል፡፡ … ከነፍሱ ድካምም ብርሀንን ያያል፡፡ ደስም ይለዋል፡፡ ብሎ ፍሰሀና ሀሴትን ሰበከ፡፡ 

በመሆኑም ካለንበት ዱር ገደል እንኳን ለፋሲካ በአል አደረሳችሁ እንላለን! እረግጥ ነዉ ፋሲካ ወተንስአ እሙታን የሚል ብስራት የታወጀበት እለት ነዉ፡፡ እለቱ ታሪካዊ ክስተት ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጅ የዘላለም ተስፋ ነው፡፡ ኃጢአትም፣ መከራም፣ ሞትም መጨረሻ እንዳልሆኑ የተረጋገጠበት በምትኩ በጸሎት፣ በትእግስትና በጽናት አርነት እንደምንወጣ እለት እለት የሚመራን የተግባር መመሪያ ነው፡፡

የክርስቶስ ትንሳኤ ለአለም አዲስ ክስተትና ተአምር ነዉ፡፡ የተቀበለው መከራ፣ የተፈረደበት የኃጥያተኛ ሞት እና ሞትን ድል አድርጎ መነሳቱ የሰዉ ልጅ የሀጥያት ይቅርታና ምህረት ብሎም የዘላለም ህይወት ቃል ኪዳን የተረጋገጠበት አስገረራሚ ትእይንት ነው፡፡ ይህንን ሲያስረግጥ ሐዋርያዉ ጳዉሎስ አሁን ግን ክርስቶስ ላንቀላፉት በኩራት ሆኖ ከሙት ተነስቷል አለ (1 ቆሮንቶስ 15፥20)።

ይህ አስደናቂ ክስተት ለእያንዳንዱ ግፍና መከራ ለሚደርስበትና ፍትህ ለተጠማ ሰው ሁሉ እውነት ተቀብራ እንደማትቀርና ሳትዘገይም እንደምታሸንፍ ማሳያ ነው፡፡ ፋሲካ ለእኛ በመከራ ውስጥም እምነት፤ ጽናትና ተስፋ አብሮን እንዲቆይ የሚያስተምረን ነው። ጆሮ ያለዉ ይስማ እንደተባለዉ ልብ ያለዉ ልብ ይበል!
ቅዱስ ዳዊት (መዝሙር 41፥9) "የታመንኩበት እንጀራዬን የበላ በእኔ ላይ ተረከዙን አነሣ" እንዳለዉ በብዙ ዉጣ ዉረድና መስዋእትነት ለስልጣን ያበቃዉና በኃላም ለመንበሩ ጽናት ዋጋ የከፈለለትን የአማራ ህዝብ ለመርገጥ ሳይሆን ወደ አፈር ለመቀላቀል ሲንቀሳቀስ አቢይ አህመድ ብዙም አልፈጀበትም፡፡

 
በክርስቶስ ላይ ክህደት በመፈጸም በ30 ብር አሳልፎ ሊሰጠዉ የተስማማዉ ይሁዳ ከርቀት የመጣ አልበረም፡፡ ከክርስቶ ጋር አብሮ ሲኖር፣ ሲበላና ሲጠጣ ብሎም ዝቅ ብሎ እግሩ እስኪታጠብለት ድረስ የፍቅርን ጥግ የተቀበለ በክርስቶስ ቤት እንደ አንድ ታማኝ ይቆጠር የነበረ ኃዋርያ እንጂ፡፡ የአማራን ህዝብ በመካድ፣ የዉለታ እጁን አመድ አሳፍሶ አመድ ሊያደርገዉ የተነሳዉ አቢይ አህመድም ከሩቅ የመጣ ሳይሆን ቤተኛ ነኝና አዉሉኝ አሳድሩኝ ብሎ የተጠጋ፣ በእምነትም መደብ ሳይሆን አልጋ የተለቀቀለት፣ አቻነት ሳይሆን የበላይነትን የተመጸወተ፤ የክፉ ቀን አለኝታ ከሆነ ህዝብ ብዙ የተደረገለት ግን ደግሞ ለእኩይ ጥማቱና ለፖለቲካ ሴራዉ ሲል አማራን የካደ ዳግማዊ ይሁዳ ነዉ፡፡

ክርስቶስን ወደ ፍርድ ሲያቀርቡትም ሆነ መከራና ስቃይ ሲያደርሱበት ሴረኞች ሀሰትን በማቀነባበር መሟገቻ ምክንያት ያቀርቡ ነበር፡፡ የመጨረሻዉን የሞት ጽዋ እስኪጎነጭ ድረስም ሽንጣቸዉን ገትረዉ በህግ ፊት ይሟገቱ ነበር፡፡ የታመመ መፈወሱን፣ የተራበ መመገቡን እና ስለ ፍቅር፣ እዉነትና ደህንነት የሰበከዉን በሙሉ የዉንጀላ መረጃ በማድረግ እንዲገደል አድርገዋል፡፡ ዛሬም የአማራ ህዝብ ኢትዮጵያን አንድ ለማድረግ ብሎም ሉአላዊነቷ እንዳይደፈር ያበረከተዉን የደም ግብርና የጀግንነት ገድል ጭምር በማርከስና በማንቋሸሽ በልብ ወለድና በሴራ ፖለቲካ ጥንስስ አማራን መጨፍጨፍ፤ ማሰር፣ ማቃጠል፣ ማፈናቀልና ማሳደድ የተለመደ ተግባር ሆነ፡፡ ፈሪሳዉያን ክርስቶስን ሲወነጅሉ ህግ በማጣቀስ ህዝቡን ለማደናገር ይጥሩ እንደነበረ ሁሉ ዛሬ አብይና ጀሌዎችም የሀሰት ትርክቶችን በመጠቀም የደም ጉንጨታ ድርጊታቸዉን ለማለባበስ ይጥራሉ፡፡


አለም እንደሚያዉቀዉ በጥቅሉ የዘር ማጥፋት ሂደት እየተከናወነብን ይገኛል፡፡ በዚህም ስንቶች አድራሻቸዉ ጠፋ…. ስንቶችስ ተቀሰፉ… የግፉን አይነትና መጠን እንዲሁም የደረሰዉን ዉድመት ሰማይና ምድር ይቁጠረዉ…፡፡  ቢሆንም… ቢሆንም… ፋሲካ የሚያረጋግጠዉ ክርስቶስን እናጠፋለን ብለዉ የተነሱ ሰዎች በተገላቢጦሽ በክብር ላይ ክብር እንዳጎናጸፉት ነዉ፡፡ እኛም ከግፉና ከመከራዉ በኃላ ህዝባችን እንደ ሰዉ ክብር የሚያገኝበት ዘመን እንደሚመጣ ከክርስቶስ ትንሳኤ  ስለምናዉቅ ደግሞም ስለተረዳን የማይቀረዉን የአርነት ተስፋችንን እየናፈቅን በጽናት መስዋእትነታችንን እንቀበላለን፡፡

መላዉ የአማራ ህዝብ ሆይ ይህንን የጀመርነዉን መራር ትግል በድል እስከምንቋጭ ድረስ ትግላችን ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡ ለመኖር ሌላ አማራጭም የለንም፡፡ በመሆኑም ህዝባችን በተለያየ መንገድ የሚያደርገዉን ድጋፍ አጠናክሮ መቀጠል አለበት፡፡ እንደምታዉቁት ወደን የገባንበት አይደለም፡፡ ስልጣንም ፈልገን አይደለም፡፡ መኖር ተከልክለን፣ ዘራችን እየተጨፈጨፈ ከምድረ ገጽ ለማጥፋት የሚደረገዉን ጥረት ለማክሸፍ ነዉ፡፡ ሰዉ ነንና የመኖር መብት አለን ነዉ፡፡ ወደ ኃላ መለስ ብለን እናስብ… ወደ ትግል ከመግባታችን በፊት ለብዙ አስርተ አመታት ጭምር የፖለቲካ አቋም ሆኖ አማራ ሲሳደድ፣ ሲገደልና ሲታፈን ቆይቷል፡፡ በመሆኑም ትግላችን ይህ ይብቃ ነዉና በትግላችን እንቀጥላለን … በአጭር ጊዜ ድል አድርገን የደማችንን መመጠጥ እናስቆማለን፡፡


በድጋሚ ለመላዉ የክርስትና እምነት በሙሉ መልካም የፋሲካ በአል እንላለን  ! 
       ክብር ለተሰውት!
       "ድላችን በተባበረ በክንዳችን"
        ሚያዝያ 11/2017 ዓ/ም
        ሸዋ አማራ ኢትዮጵያ
        የአማራ ፋኖ በሸዋ የህዝብ ግንኙነት ክፍል




የጥንቃቄ መረጃ!!💥

"...በዘመቻ አንድነት በመሀል ሳይንት ግንባር አምሐራ ሳይንት መቅደላ ክፋለ ጦር ክንፋ የሆነው አትሮንስ ብርጌድ ቀኝ አዝማች ይታገሱ አራጋው ሻለቃ ትናንት ማለትም 10/08/2017 ዓ.ም የመሀል ሳይንት አስተዳደር የሆነው ባንዳው ጌታው መንበሩን አጅቦ ከደሴ ወደ መሀል ሳይንት ደንሳ ወረዳ ሲከንፋ የመጣውን የጁላ ሰራዊት ቀይዋሻ( ጓሳ) በሚባል ቀጠና ልዩ ደፈጣ በመያዝ የአገዛዙን ሰራዊት ሙት እና ቁስለኛ አድረገውታል።

በዚህ ልዩ ደፈጣ የሰማዕቱ ልጆች የአለ አንዳች መስዋዕትነት ድል የቀናቸው ሲሆን በተቃራኒው የአገዛዙ ሰራዊት 24 ሙት ፣ 6ት ምርኮኛ፣ 10 ቁስለኛ አሁን ከመሸ በደረሰን ታማኝ የምንጮች መረጃ 4ቱ ቻው ሲሉ 6ቱ ሪፈር ተብለው ወደ አቀስታ ጠቃላላ ሆስፒታል ተልከዋል።

በዚህ አውደ ውጊያም 1ብሬን፣ 3ስናይፐር፣2ጥቁር ክላሽ መማረክ ተችሏል።

በዚህ ድንገተኛ ጥቃት የተበሳጨው በሻለቃ ሰንደቁ የሚመራው የጁላ ሰራዊት አሁን ከመሸ 12፡30 አካባቢ 4ንፁሃንን የፋኖ ቤተሰብ ናቹ መረጃ ትሰጣላቹ በማለት በአደባባይ እንደረሸናቸው ከታማኝ የአይን እማኝ ምንጮች አንድ አምሐራ ዕዝ ሚዲያ አረጋግጣለች።

ስለሆነም ህዝባችን አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያረግ እና ከአሁን በሁአላ ለምናረገው ማንኛውም ኦፕሬሽን ልዩ ጥንቃቄ እንዲያረግ ለማሳሰብን እንወዳለን ሲል የብርጌዱ ዋና አዛዠ ጎሹ ሳይንቴው ከአንድ አምሐራ ዕዝ ሚዲያ ጋ በነበረው ቆይታ ገልፆል።

በነገራችን ላይ መሀል ሳይንት ደንሳ ወረዳ ካሉት 17 ቀበሌዎች መካከል 15ቱን ሙሉ ለሙሉ በአትሮንስ ብርጌድ እየተዳደሩ እንዳለ የቀሩት ሁለት ቀበሌዎችን ደሞ በከፊል በፋኖ የፀጥታ መዋቅር እየተመሩ እንዳሉ ጎሹ ሳይንቴው ለአንድ አምሐራ ዕዝ ሚዲያ አረጋግጧል።


ታጋይ አምሓራ
ነፃነት በትግል እንጂ በልመና አይገኝም!


በአማራ የህልውና ትግል ላይ ግንባር ቀደም መረጃዎችን የሚያደርሱ ሚዲያዎች እንጠቁማቹህ።
https://t.me/addlist/nmnYZC22bwBlMjNk


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
የትናንትናው እና የዛሬው የመሀል ሳይንቱ ድል ዝም ብሎ በድል ስም የሚመዘገብ አይደለም፤ የድል ድል የሚባል ነው ብለውኛል የመረጃ ምንጮች።

"ሳይንት አትውረዱ በርበሬ ብላችሁ!
ይሻላል መሰንበት አልጫ በልታችሁ!"

ብለን ተናግረን ነበር ግን ሲክለፈለፉ መጡ ሀቃቸው ተሰጣቸው።

የቀኝ አዝማች ይታገሱ አረጋው ሻለቃ መሪ ፋኖ በለጠ አከለ💪💪

ቻለው ቀጠናዉ ቤርሙዳ ነው።

 
ታጋይ አምሓራ
ነፃነት በትግል እንጂ በልመና አይገኝም!

Показано 20 последних публикаций.