ትምህርት በቤቴ®


Гео и язык канала: Эфиопия, Английский
Категория: Образование


A channel created for sharing
🔺study tips,
🔺short notes,
🔺tutorials,
🔺educational news,
🔺life tips and some motivational quotes ...

Buy ads: https://telega.io/c/temhert_bebete
📩 For comment- @Tmhert_bebete_info_bot

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Английский
Категория
Образование
Статистика
Фильтр публикаций


Репост из: In Africa Together
🚀 IAT Student Event Alert! 🚀
🎤 Hosted by In Africa Together (IAT)

✅ Licensed in 🇺🇸 Michigan, USA & 🇪🇹 Addis Ababa, Ethiopia 

✨Exclusive Offer for High School Students!✨ 
🎉 Enjoy a 10% discount just bring your High School ID!

📅 Date: Sunday, February 9
📍 Venue: Kaleb Hotel (Next to Harmony Hotel) 
⏰ Time: 2:00 AM – 8:00 AM (Local Time) 
 
🎓 No Pre-Payment Required
📜 No English Proficiency Exam
✅ 100% Admission Guarantee

🇺🇸 USA – 66% Scholarship + 34% Covered by Student Loan
🇨🇳 China – Full Scholarship + Pocket Money Allowance

🎯 Apply for: 
- Bachelor’s Degree 
- Master’s Program 
- PhD Programs 

📦 Our Packages Improve Your Visa Chances!

🔗 Secure Your Spot – Register Now!👇🏾 
https://forms.gle/aWzxNFkQJS8ozaLU7


የጤና ተመራቂዎች የሙያ ብቃት ምዘና (COC) መቼ ይሰጣል?

ከትናንት ጥር 26/2017 ዓ.ም ጀምሮ የጤና ተማሪዎችን ጨምሮ የቅድመ-ምረቃ ዕጩ ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና እየተሰጠ ይገኛል።

የሙያ ብቃት ምዘና (COC) ለመውሰድ እየጠበቁ የሚገኙ የጤና ተመራቂዎች (ምዘናውን በድጋሜ የሚወስዱትን ጨምሮ) ምዘናው መቼ እንደሚሰጥ ቲክቫህን ጠይቀዋል።

በጉዳዩ ዙሪያ ጤና ሚኒስቴርን የጠየቅን ሲሆን፤ በትምህርት ሚኒስቴር እየተሰጠ የሚገኘው የመውጫ ፈተና መጠናቀቅና ውጤት መገለፅን ተከትሎ COC የሚወስዱ አመልካቾች (ድጋሜ ተፈታኞችን ጨምሮ) ምዝገባ እንደሚደረግ ከሚኒስቴሩ አረጋግጠናል።

የCOC ምዘናውን በየካቲት ወር መጨረሻ ወይም በመጋቢት ወር የመጀመሪያ ሳምንት ለመስጠት በጊዚያዊነት መታቀዱን ከሚኒስቴሩ ሰምተናል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete


ዛሬ መሠጠት የተጀመረውን የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም ዕጩ ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና #በጥብቅ የፈተና ዲሲፕሊን እንዲሰጥ እያደረጉ መሆኑን ዩኒቨርሲቲዎች ገለፁ።

ወለጋ ዩኒቨርሲቲ ተፈታኞች ወደፈተና ማዕከላት ይዘው እንዳይገቡ የተከለከሉ ነገሮችን ፍተሻ በማድረግ መያዙን ገልጿል።

በዚህም ዩኒቨርሲቲው ኩረጃ እና ስርቆት የሚያግዙ ክልክል የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ይዘው የተገኙ ተማሪዎችን ወደ መፈተኛ ክፍሎች እንዳይገቡ አድርጓል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete


#EXITEXAM #note

ትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ተግባራዊ ማድረግ ከጀመራቸው ስራዎች አንዱ የሆነ የተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ከጥር 26 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ ይሰጣል።

⚡️በፈተና ወቅት ከተፈታኝ ተማሪዎች ምን ይጠበቃል ?


👉🏾 ተፈታኞች ወደ መፈተኛ ክፍል ሲመጡ ማንኛውም አይነት ስልክ፣ ስማርት ሰዓት ፣ ታብሌት ፣ ላፕቶፕና ... ወዘተ ተመሳሳይ ኤክትሮኒክ ቁሳቁስ መያዝ በፍፁም የተከለከለ ነው።  (ይዞ የተገኘ ፈተናው /ውጤቱ ተሰርዞበት በቀጣይ ጊዜ እንዲቀመጥ ይደርጋል)

👉🏾 ፈተና ከመጀመሩ ከ30 ደቂቃ በፊት መፈተኛ ክፍል መገኘት አለባቸው ይህም ማለት ከጥዋቱ 2፡00 በፊት ፤ ከሰዓት ደግሞ ከ8፡00 በፊት ተፈታኞች መገኘት አለባቸው።

👉🏾 ተፈታኞች ለፈተና ሲመጡ ID መያዝ ያለባቸው ሲሆን User Name እና Password lower-case and upper-case ፊደላትን ለይተው በጥንቃቄ መያዝ አለባቸው።

👉🏾 ተፈታኞች ፈተና ከተጀመረ በኃላ ከ30 ደቂቃ በፊት ከፈተናው ክፍል መውጣት የለባቸውም።

👉🏾 ተፈታኞች ፤ ፈተናውን የሚያስፈትኑ መምህራን በሚያሳዩት ቦታ ብቻ መቀመጥ አለባቸው።

👉🏾 ሁሉም ተፈታኝ እንዲቀመጥ የተመደበበት የራሱ ኮምፒውተር ላይ ብቻ ተቀምጦ መክፈትና መጠቀም አለበት።

👉🏾 በፈተና ክፍል ውስጥ መነጋገር እና ከቦታ ቦታ መዘዋወር በፍፁም የተከለከለ ነው። እንዲሁም ማንኛውም ተፈታኝ ከጎኑ ያለውን ተማሪ ኮምፒውተር በፍፁም ማየት የለበትም።

👉🏾 ምንም ዓይነት ወረቀት ወደ መፈተኛ ክፍል ይዞ መምጣት አይቻልም።

👉🏾 ተፈታኞች በምንም ሁኔታ መኮርጅም ሆነ ማስኮርጅ ተግባር ላይ ቢሳተፉ እርምጃ ይወሰድባቸዋል።

👉🏾 ሁሉም ተፈታኞሽ ለፈታኝ መምህራንና ለአስተባባሪዎች  መታዘዝ ያለባቸው ሲሆን የፈተናው ደንብ እና ስርዓት ተገዢ መሆን ይጠበቅባቸዋል።

👉🏾 በድጋሚ ተፈታኞች የፈተና መግቢያ ትኬት (Exit Exam Entry Ticket) መያዝ ይጠበቅባቸዋል።

NB.  ሁሉም ተፈታኞች ወደ መፈኛ ክፍል ተፈትሸው እንዲገቡ የሚደረግ ሲሆን ማንኛውም ተፈታኝ ከፀጥታ ኃይሉ ጋር በፍተሻ ወቅት ይሁን ሥርዓት ለማስያዝ በሚደረግ እንቅስቃሴ እንቅፋት ሆኖ ከተገኘ ከመፈተኛ አከባቢ እንዲገለል ተደርጎ በቀጣዩ የመውጫ ፈተና መስጫ ወቅት እንዲቀመጥ ይፈቀድለታል።

⚡️ከፈታኝ መምህራን የሚጠበቅ

👉🏾 የተፈታኝ ተማሪዎችን ID በአግባቡ በማረጋገጥ ወደ ክፍል እንዲገቡ ማደረግ ይጠበቅባቸዋል።

👉🏾 ተፈታኝ ተማሪዎችን በሥም ዝርዝራቸው መሠረት ማስቀመጥ ይኖርባቸዋል።

👉🏾 ፈታኝ መምራህን የተማሪዎችን አቴንዳንሰ ይወስዳሉ ፤ ተማሪዎችን ፊርማ ያስፈርማሉ።

👉🏾 በፈተና ክፍል ውስጥ ደምጽ እንዳይሰማ፣ ተማሪዎች ከቦታ ቦታ እንዳይዘዋወሩ ተገቢውን ቁጥጥር ማድረግ አለባቸው።

👉🏾 የፈተናው አጠቃለይ ሂደት በትኩረት መከታተል አለባቸው።

👉🏾 በህመም ምክንያት ተማሪዎች ከክፍል መውጣት ቢፈልጉ ከሱፐርቨዘር ጋር በመነጋገር አስፈላጊውን እርዳታ ያደርጋሉ።

👉🏾 ተማሪዎች በጎናቸው ያለውን ሌላ ኮምፒውተር እንዳይመለከቱ መቆጣጠር አለባቸው።

👉🏾 ተማሪዎች ፈተናው ከተጀመረ ከ30 ደቂቃ በፊት እንዳይወጡ መቆጣጠር ይጠበቅባቸዋል።

👉🏾 ሲኮርጂ ወይንም ሲያስኮርጅ የተገኘ ተማሪ ከመፈተኛ ክፍል እንዲወጣ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።

👉🏾 ፈተናው ከጀመረ 15 ደቂቃ በኃላ የሚመጣ ተማሪ እንዲገባ ማድረግ የላባቸውም።

👉🏾 የፈተና አፈጻጸም ሪፖርት ለሱፐርቨዘር ማቅረብ

🌺 መልካም ፈተና 🌺

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete


በ2017 ዓ.ም አጋማሽ ላይ የሚሰጠውን የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች የመውጫ ፈተና ለመውሰድ 176 ሺህ ተማሪዎች ተመዝግበዋል።

ፈተናውን በድጋሚ የሚወስዱትን ጨምሮ በጠቅላላው 176 ሺህ ተማሪዎች የመውጫ ፈተናውን እንደሚወስዱ ይጠበቃል።

ፈተናው በኢትዮጵያ በሚገኙ በሁሉም የኒቨርሲቲዎች የሚሰጥ ሲሆን፤ ተጠሪነቱ ለትምህርት ሚኒስቴር ያልሆነው የመከላከያ ዩኒቨርሲቲ ውስጥም እንደሚሰጥ በትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዬች መሪ ሥራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) ለአሐዱ ራዲዮ ተናግረዋል።

የግል ኮሌጅ ተማሪዎችም በመረጡትና በአቅራቢያቸው በሚገኝ የመንግስት ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ፈተናቸውን ይወስዳሉ ብለዋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete


Репост из: In Africa Together
🚀 IAT Student Event Alert! 🚀
🎤 Hosted by In Africa Together (IAT)

✅ Licensed in 🇺🇸 Michigan, USA & 🇪🇹 Addis Ababa, Ethiopia 

Exclusive Offer for High School Students!✨ 
🎉 Enjoy a 10% discount just bring your High School ID!

📅 Date: Sunday, February 9
📍 Venue: Kaleb Hotel (Next to Harmony Hotel) 
Time: 2:00 AM – 8:00 AM (Local Time) 
 
🎓 No Pre-Payment Required
📜 No English Proficiency Exam
✅ 100% Admission Guarantee


🇺🇸 USA – 66% Scholarship + 34% Covered by Student Loan
🇨🇳 China – Full Scholarship + Pocket Money Allowance

🎯 Apply for: 
- Bachelor’s Degree 
- Master’s Program 
- PhD Programs 

📦 Our Packages Improve Your Visa Chances!

🔗 Secure Your Spot – Register Now!👇🏾 
https://forms.gle/aWzxNFkQJS8ozaLU7




#ExitExam

176 ሺሕ ተማሪዎች የመውጫ ፈተናን ለመውሰድ መመዝገባቸው ተገለጸ

👉ፈተናው ከጥር 26 እስከ 30 ድረስ ይሰጣል

ጥር 23/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በ2017 ዓ.ም አጋማሽ ላይ የሚሰጠውን የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች የመውጫ ፈተና ለመውሰድ 176 ሺሕ ተማሪዎች መመዝገባቸውን ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።

ፈተናውን በድጋሚ የሚወስዱትን ጨምሮ በጠቅላላው 176 ሺሕ ተማሪዎች የመውጫ ፈተናውን ይወስዳሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ በትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዬች መሪ ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ኤባ ሚጀና #ለአሐዱ ገልጸዋል።

በዚህም መሰረት በኢትዮጵያ የሚገኙ በሁሉም የኒቨርሲቲዎች ፈተናው የሚሰጥ ሲሆን፤ ተጠሪነቱ ለትምህርት ሚኒስቴር ያልሆነው የመከላከያ ዩኒቨርሲቲ ጭምር በዚህ ፕሮግራም ተካታች መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

የግል ኮሌጆችን በሚመለከት አሐዱ ላቀረበላቸው ጥያቄ ትምህርት ሚኒስቴር የግል ኮሌጆች ላይ ገብቶ ለመፈተን የሚያስችል መዋቅር እንደሌለው በማንሳት፤ ነገር ግን ተማሪዎች በአቅራቢያቸው በሚገኝ የመንግስት ተቋም በኩል መፈተን እንደሚችሉ ገልፀዋል።

የፈተና ቀኑ በተለያዩ ምክንያቶች ዘግይተው ትምህርት የጀመሩትን ዩኒቨርሲቲዎች ታሳቢ ያደረገና በቂ ዝግጅት ማድረጋቸው ከተረጋገጠ በኋላ መወሰኑን ተናግረዋል።

ፈተናውን ለመስጠት ታቅዶ የነበረው ጥር 14 እና 15 የነበረ ቢሆንም፤ ሁሉም ዩኒቨርስቲዎች እኩል ትምህርት ባለመጀመራቸው ወደ ጥር 26 ቀን 2017 ዓ.ም. እንዲሸጋገር መደረጉን ገልጸዋል፡፡

በዚህ የፈተና ፕሮግራም ተንቀሻቃሽ ስልክና የወረቀት ፅሁፍ ይዞ መገኘት ፈፅሞ #የተከለከለ መሆኑን የገለጹት የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ሥራ አስፈፃሚው፤ "ተፈታኞች መታወቂያ መያዝና ከፈተና ፕሮግራሙ 30 ደቂቃ ቀድሞ ቦታው ላይ መድረስ ይጠበቅባቸዋል" ብለዋል፡፡ የወጣው ፈተናም ከተማሩት በመሆኑ ሳይጨነቁ በተረጋጋ መንፈስ መስራት እንደሚገባቸው አሳስበዋል።

የዘንድሮው የዩኒቨርስቲዎች የመውጫ ፈተና ከዚህ በፊት ይሰጥ እንደነበረው ሙሉ ለሙሉ በኦንላይን የሚካሄድ ሲሆን፤ ከጥር 26 እስከ 30 ከሰኞ እስከ አርብ ባሉት አምስት ተከታታይ ቀናት እንደሚሰጥ አስታውቀዋል።

የተማሪዎች ፈተና እንደተጠናቀቀ ቅዳሜ ማለትም የካቲት 1 ቀን የመምህራንን ስልጠና ሲወስዱ የነበሩ መምህራን ፈተና ይወስዳሉ ተብሎ ይጠበቃል።

[ዘገባው የአሃዱ ሬድዮ ጣቢያ ነው]

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete


የሐኪሞች የስራ አጥነት ቁጥር እየጨመረ ከመምጣቱ በተጨማሪ በተለያዩ በሽታዎች ተይዘው የህይወት ዋጋ እየከፈሉ ነዉ ተባለ፡፡

በህክምና የተመረቁ ስራ አጥ የህክምና ባለሙያዎች ቁጥር እየጨመረ መሆኑን የኢትዮጵያ ህክምና ማህበር አስታዉቋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ሕክምና የሚያስፈልጋቸው ሐኪሞች ተገቢውን ሕክምና በፍጥነት ባለማግኘታቸው የሕይወት ዋጋ እየከፈሉ ይገኛሉ ተብሏል፡፡

ማህበሩ ሀኪሞች ብዙ ጫናዎችን ተቋቁመው ስራ እየሰሩ ቢሆንም የሰሩበትን የትርፍ ሰዓት ክፍያ ሳይከፈላቸዉ የሚቆዩባቸዉ ክልሎች መኖራቸዉን አንስቷል፡፡

ክፍያ የሚጠይቁ ሐኪሞችም ለእስር የሚዳረጉበት ሁኔታዎች የታዩበት ዓመት ነበር ሲል ማህበሩ ገልጿል፡፡

እንደሕክምና ማህበር ከሚመለከታቸው የስራ ሃላፊዎች ጋር ምክክር ለማድረግ ቢሞከርም፤ አሁንም ከችግሩ ስፋት አንጻር ለብዙዎች ችግር ምላሽ መስጠት አልተቻለም ነዉ ያለዉ፡፡

ከዚህ ቀደም ከጣቢያችን ጋር ቆይታ ያደረጉት የኢትዮጵያ ህክምና ማህበር ፕሬዝዳንት ዶ/ር ተግባር ይግዛዉ ፤ በአገራችን ያሉ የሀኪሞች ቁጥር ወደ 17ሺህ ነዉ ያሉን ሲሆን፤ ከዚህ መሃል ወደ 40 በመቶ የሚሆነዉ ወይም 1ሶስተኛዉ ብቻ የማህበሩ አባል መሆኑን አንስተዋል፡፡

የሙያ ማህበር መቅጠር አይችልም ፤ማድረግ የሚችለዉ ጉዳዩን ማሳወቅ ነዉ ያሉት ዶ/ር ተግባር፤ከጤና ሚኒስቴርም ሆነ ከክልል ጤና ቢሮዎች ጋር በጉዳዩ ላይ መነጋገራቸዉን በወቅቱ አንስተዉ ነበር፡፡

ዘንድሮ 61ኛውን ዓመታዊ የሕክምና ጉባኤና ዓለም አቀፍ የጤና አዉደ ርእይ ከየካቲት 14 – 15/2017ዓ.ም ለማካሄድ ማቀዱንም ማህበሩ አስታዉቋል፡፡
በጉባዔዉ በሃገር ውስጥ እና በውጭ ሃገር የሚኖሩ የህክምና ባለሙያዎች ያላቸውን እውቀት፣ የምርምር ግኝቶችን እና የህክምና ልምዶችን በማቅረብ የዓመቱን መሪ ቃል መነሻ በማድረግ የፓናል ውይይቶች እንደሚካሄዱም ለማወቅ ችለናል፡፡

ማህበሩ ከተመሰረተበት 1940 ዓ.ም ጀምሮ በህክምና አገልግሎት አሰጣጥ ጥራት፣  ደህንነት እና በአጠቃላይ በህክምናው ዘርፍ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡

#EthioFM

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete


ጥንቃቄ #CBE

አደገኛ መተግበሪያ በማኅበራዊ ሚዲያ እየተዘዋወረ መሆኑን ንግድ ባንክ አስታወቀ‼️

ከጫናችሁ ያለፈቃድ ገንዘብ ይቆረጥባችኃል!

ደንበኞች በዋትስ አፕ እና በቴልግራም የሚሠራጭ Pharma+/CBE Vacancy መተግበሪያን እንዳይጭኑ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አሳስቧል።

ባንኩ ባስተላለፈው የማስጠንቀቂያ መልዕክት፤ ባደረገው ምርመራ መሠረት አደገኛ መተግበሪያ ማግኘቱን ገልጿል።

ይህ Pharma+/CBE Vacancy የተሰኘ አሳሳች መተግበሪያ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በሰፊው እየተሰራጨ እንደሆነ በመጥቀስ፤ ይህ መተግበሪያ በቴሌግራም እና ዋትስአፕ ወደ ደንበኞቹ እየደረሰ መሆኑን ጠቁሟል።

መተግበሪያው በስልክ ላይ ከተጫነ ያለ ፈቃድ ገንዘብ ማስተላለፍ እንደሚችልም አሳውቋል።

ባንኩ ከዚህ አይነት አደጋ ለመጠበቅ ከቴሌግራም ወይም ዋትስአፕ መተግበሪያዎችን አታውርዱ ብሏል። ደንበኞች መሰል ተግባራት ሲገጥሟቸው በ951 ነጻ የስልክ መስመር ደውለው እንዲያሳውቁ አሳስቧል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete


በአዲስ የመመዘኛ መስፈርት ዳግም ምዝገባ ካደረጉ 273 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ አንድም ተቋም መስፈርቱን እንዳላሟላ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ገለፀ፡፡

ባለሥልጣኑ አዲስ ባወጣው መመዘኛ 273 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዳግም ምዝገባ ያደረጉ ሲሆን፤ 84 ተቋማት ባለመቅርባቸው መሰረዛቸው ይታወሳል፡፡

ተቋማቱ መስፈርቱን እንዲያሟሉ ተጨማሪ 45 ቀናት የጊዜ ገደብ መቀመጡን በባለሥልጣኑ የፈቃድ አሰጣጥና የጥራት ኦዲት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ውብሸት ታደለ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ተናግረዋል።

በተጨማሪ የጊዜ ገደብ ተማሪዎች መመዘኛውን አሟልተው ወደሚገኙ ተቋማት ተዛውረው እንዲማሩ ማድረግን ጨምሮ የተለያዩ አማራጮችን ባለሥልጣኑ እንደሚጠቀም አመልክተዋል። #FMC
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete


#Exit_Exam

የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ከጥር 26-30/2017 ዓ.ም እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር በድጋሜ አሳውቋል፡፡

የመውጫ ፈተናው ለአዲስ እና በድጋሜ ለመፈተን ላመለከቱ በሙሉ እንደሚሰጥ ተገልጿል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete


Репост из: Daily inspiration™
Fullstop is not an end;

Because we can write a new sentence after it.

Same is the case with life -

as failure is not the real end,

it can be a real beginning of success!

More ⬇️
🍁 @daily_inspiree 🍁


" ያለ አሜሪካ ፍቃድ/ይሁንታ ቲክቶክ የለም " - ትራምፕ

👉 " 50% የቲክቶክን ድርሻ አሜሪካ መያዝ አለባት ! "

ትራምፕ ቲክቶክ አሜሪካ ውስጥ በጊዜያዊነት መስራት እንዲቀጥል ሊያደርጉ ነው።

ተመራጩ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በትሩዝ ገጻቸው ላይ ዛሬ ባወጡት ፅሁፍ ፤ ቲክቶክ በአሜሪካ ውስጥ በጊዜያዊነት መስራቱን እንዲቀጥል እንደሚያደርጉ አሳውቀዋል።

ለዚህም በስልጣን ዘመናቸው የመጀመሪያ ቀን (ነገ ማለት ነው) ቲክቶክ በጊዜያዊነት መስራት እንዲቀጥል የሚያስችል እርምጃ ይወስዳሉ / ልዩ የሆነ ትዕዛዝ ይሰጣሉ።

ትራምፕ በዚሁ ፅሁፋቸው አሜሪካ የማህበራዊ ድረ-ገፁን ግማሽ (50%) በባለቤትነት መያዝ እንዳለበት ጠቁመዋል።

ነገ ወደ ቢሮ ገብቼ ስራ ከጀምርኩ በኃላ " ቲክቶክ እንዲጨልም አልፈልግም " ሲሉ ገልጸዋል።

ትራምፕ እንደ ጋራ ሽርክና አሜሪካ በቲክቶክ ውስጥ የ50% የባለቤትነት ድርሻ እንድትወስድ ሀሳብ አቅርበዋል።

ይህ ማለት ከወላጅ ኩባንያው ባይትዳንስ ወይም ከአዳዲስ ባለቤቶች ጋር " በአሜሪካ እና በመረጠችው ግዢ መካከል ትብብር ሊፈጥር ይችላል።

ትራምፕ " ይህንን በማድረግ ቲክቶክን እንታደገዋለን ፣ በጥሩ እጆች ውስጥ እናቆየዋለን " ብለዋል።

" ያለ አሜሪካ ፍቃድ ቲክቶክ የለም " ያሉት ትራምፕ " ከኛ ይሁንታ ጋር በመቶ ቢሊዮን ዶላር ምናልባትም ትሪሊዮን የሚቆጠር ዋጋ አለው " ሲሉ ጽፈዋል።

@temhert_bebete


በ2017 ዓ.ም ለሚሰጠው የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና የተፈታኞችን ምዝገባ ለማካሄድ ይረዳን ዘንድ ፈተናውን ለመጀመሪያ ጊዜ የሚፈተኑ ተማሪዎችን መረጃ ለመሰብሰብ የሚያስችል የሶፍት ዌር ቴምፕሌት በትምህርት ሚኒስቴር የተዘጋጀ መሆኑ ይታወቃል፡፡
በመሆኑም በታህሳስ 30 /2017ዓ.ም በቁጥር 11/77/1201/17 ባለስልጣን መስሪያቤቱ ባወጣው ማስታወቂያ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተፈታኞቻቸውን መረጃ በሶፍት ዌር ቴምፕሌት ማስገባታችሁ ይታወቃል:: ነገር ግን በተሰጠው ጊዜ ቀን ገደብ ያላስገባቹ ተቋማት እና ማስተካከያ እንድታደረጉ እድል የተሰጣቹ ተቋማት በድጋሜ በሶፍት ዌር ቴምፕሌት ከ09/05/2017 ዓ.ም እስከ 14/05/2017 ዓ.ም ድረስ እንድታስገቡ እያልን ጥንቃቄ በተሞላበት አግባብ እንዲሆን እናሳስባለን፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete


#Update

በ2017 ዓ.ም አጋማሽ የሚሰጠውን የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ዳግም ለመውሰድ ፍላጎት ያላቸው አመልካቾች ምዝገባ ከጥር 8-14/2017 ዓ.ም እንደሚከናወን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡

ለመመዝገብ 👉 https://exam.ethernet.edu.et

ፈተና የሚሰጥበትን ጊዜ በቀጣይ እንደሚያሳውቅ ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡

ከምዝገባ ጋር ተያይዞ ለሚኖራችሁ ጥያቄ ዘውትር በሥራ ሰዓት በተከታዮቹ አማራጮች ማብራሪያ መጠየቅ የምትችሉ መሆኑን ተገልጿል፡፡

Email: ngat@ethernet.edu.et
☎️ 0911824528 / 0913678404 / 0913949676 / 0910076453 / 0923106826 / 0913866717 / 0911335683

Note:
➫ የመፈተኛ User Name እና Password በመመዝገቢያ ፖርታል በኩል የሚላክ ይሆናል።
➫ የመመዝገቢያ ክፍያ ብር 500 በቴሌብር በኩል ብቻ መፈፀም ይኖርባችኋል፡፡
➫ ምዝገባ ማድረግ የሚቻለው በተጠቀሱት የምዝገባ ቀናት ብቻ ነው፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete



Показано 17 последних публикаций.