' ልጄን ትተህ እኔን ብላኝ ! '
🙏" ከእግዚአብሔር በታች እኔና ልጄን የታደገችን ጎረቤቴ ወ/ሮ መቅደስ ናት " - መምህርት ደንበሌ አስራት
➡️" እናትና ልጅን ለማዳን ከ10 ደቂቃ በላይ ከጅቡ ጋር ታግለናል" - ወ/ሮ መቅደስ ተካ
ከሰሞኑ መምህርት ደንበሌ አስራት የተባሉ እናት በሀዲያ ዞን ሆሳዕና ከተማ 'ጃሎ ናራሞ ' ተብሎ በሚጠራዉ አከባቢ የ12 ዓመት ልጃቸዉን ሊበላ ከያዘ ጅብ ጋር በመታገል ልጇን ማዳኗን ሲዘገብ ነበር።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም ወደ መምህርት ደንበሌ አስራት የእጅ ስልክ በመደወል ስለጉዳዩ ጠይቋቸዋል።
መምህርት ደንበሌ ስለ ጉዳዩ ሲያስረዱ" ጥር 11/2017 ዓ/ም ረፋድ 3 ሠዓት አከባቢ ዉሃ ለመቅዳት ከልጄ ጋር ሽላንሻ ወደተባለው ምንጭ በወረድንበት አጋጣሚ ነበር አፉ በደም የተለወሰ አንድ ጅብ ወደ እኛ በመምጣት በእኔና በጎረቤቴ ወ/ሮ መቅደስ መሃል የነበረዉን የ12 ዓመት ሕፃን እግር ነክሶ በመያዝ ወደ ጫካ ዉስጥ መጎተት ሲጀምር ዐይኔ እያዬ ልጄን አይበላብኝም በማለት ቀኝ እጄን የጅቡ አፍ ዉስጥ በመክተት 'ኤ ሲቴ' ኤ ሲቴ'በሀዲየኛ (ልጄን ትተህ እኔን ብላኝ) እያልኩ መጮህ ጀመርኩ " ብለዋል።
" ጎረቤቴ ወ/ሮ መቅደስ ተካ በጄርካንና በመዘፍዘፊያ ጅቡን እየመቱ መጯጯህ ቀጠልን ፤ በመሃል ትግልና ጩኸታችን ስለበዛ ጅቡ እኔንም ልጄንም ትቶ ወደ ወ/ሮ መቅደስ ሲዞር አፉ ደም በደም ሆኖ ነበር " ሲሉ አስረድተዋል።
መምህርት ደንበሌ አስራት " እየጮህን ስንታገል የሰሙ ሰዎች ደርሰዉ ጅቡን በመግደላቸዉ እኛ ወደ ሆስፒታል ተወሰድን " ብለዋል።
" ከፈጣሪ በታች እኔንና ልጄን የታደገችን ጎረቤቴ ወ/ሮ መቅደስ ናቸዉ " የሚሉት መምህርት ደንበሌ አስራት ለተደረገላቸው እገዛ ምስጋና አቅርበዋል።
ወ/ሮ መቅደስ ተካ በበኩላቸው " ልጅና እናቱን ከጅቡ አፍ ለማስጣል ከ10 ደቂቃ በላይ ታግለናል " ያሉ ሲሆን " የናቲቱ ወ/ሮ ደንበሌ ለልጇ መስዋዕት ለመሆን መዘጋጀት እኔም እናት ነኝና ሆዴን አባብቶ ጅቡን በጋራ ታግለን የከፋ አደጋ እንዳይደርስ አድርገናል" ብለዋል።
ከዚህ ቀደም አንዲት እናት ተመሳሳይ አደጋ በራሳቸዉ ላይ መድረሱን የሚያስታውሱት ሁለቱ እናቶች ከአደጋዉ ባሻገር በሀዲያ ዞን ዋና ከተማ ሆሳዕና ዉስጥ ሆነን " ከጅቦች ጋር ታግለን የምንጠቀመዉ የዉሃ ችግር እልባት ሊሰጠዉ ይገባል " ሲሉ አሳስበዋል።
@tikvahethiopia
🙏" ከእግዚአብሔር በታች እኔና ልጄን የታደገችን ጎረቤቴ ወ/ሮ መቅደስ ናት " - መምህርት ደንበሌ አስራት
➡️" እናትና ልጅን ለማዳን ከ10 ደቂቃ በላይ ከጅቡ ጋር ታግለናል" - ወ/ሮ መቅደስ ተካ
ከሰሞኑ መምህርት ደንበሌ አስራት የተባሉ እናት በሀዲያ ዞን ሆሳዕና ከተማ 'ጃሎ ናራሞ ' ተብሎ በሚጠራዉ አከባቢ የ12 ዓመት ልጃቸዉን ሊበላ ከያዘ ጅብ ጋር በመታገል ልጇን ማዳኗን ሲዘገብ ነበር።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም ወደ መምህርት ደንበሌ አስራት የእጅ ስልክ በመደወል ስለጉዳዩ ጠይቋቸዋል።
መምህርት ደንበሌ ስለ ጉዳዩ ሲያስረዱ" ጥር 11/2017 ዓ/ም ረፋድ 3 ሠዓት አከባቢ ዉሃ ለመቅዳት ከልጄ ጋር ሽላንሻ ወደተባለው ምንጭ በወረድንበት አጋጣሚ ነበር አፉ በደም የተለወሰ አንድ ጅብ ወደ እኛ በመምጣት በእኔና በጎረቤቴ ወ/ሮ መቅደስ መሃል የነበረዉን የ12 ዓመት ሕፃን እግር ነክሶ በመያዝ ወደ ጫካ ዉስጥ መጎተት ሲጀምር ዐይኔ እያዬ ልጄን አይበላብኝም በማለት ቀኝ እጄን የጅቡ አፍ ዉስጥ በመክተት 'ኤ ሲቴ' ኤ ሲቴ'በሀዲየኛ (ልጄን ትተህ እኔን ብላኝ) እያልኩ መጮህ ጀመርኩ " ብለዋል።
" ጎረቤቴ ወ/ሮ መቅደስ ተካ በጄርካንና በመዘፍዘፊያ ጅቡን እየመቱ መጯጯህ ቀጠልን ፤ በመሃል ትግልና ጩኸታችን ስለበዛ ጅቡ እኔንም ልጄንም ትቶ ወደ ወ/ሮ መቅደስ ሲዞር አፉ ደም በደም ሆኖ ነበር " ሲሉ አስረድተዋል።
መምህርት ደንበሌ አስራት " እየጮህን ስንታገል የሰሙ ሰዎች ደርሰዉ ጅቡን በመግደላቸዉ እኛ ወደ ሆስፒታል ተወሰድን " ብለዋል።
" ከፈጣሪ በታች እኔንና ልጄን የታደገችን ጎረቤቴ ወ/ሮ መቅደስ ናቸዉ " የሚሉት መምህርት ደንበሌ አስራት ለተደረገላቸው እገዛ ምስጋና አቅርበዋል።
ወ/ሮ መቅደስ ተካ በበኩላቸው " ልጅና እናቱን ከጅቡ አፍ ለማስጣል ከ10 ደቂቃ በላይ ታግለናል " ያሉ ሲሆን " የናቲቱ ወ/ሮ ደንበሌ ለልጇ መስዋዕት ለመሆን መዘጋጀት እኔም እናት ነኝና ሆዴን አባብቶ ጅቡን በጋራ ታግለን የከፋ አደጋ እንዳይደርስ አድርገናል" ብለዋል።
ከዚህ ቀደም አንዲት እናት ተመሳሳይ አደጋ በራሳቸዉ ላይ መድረሱን የሚያስታውሱት ሁለቱ እናቶች ከአደጋዉ ባሻገር በሀዲያ ዞን ዋና ከተማ ሆሳዕና ዉስጥ ሆነን " ከጅቦች ጋር ታግለን የምንጠቀመዉ የዉሃ ችግር እልባት ሊሰጠዉ ይገባል " ሲሉ አሳስበዋል።
@tikvahethiopia