“ ድርጅቱ ለኪራይ፣ ደመወዝና ለሌሎች ወጪዎች ክፍያ ባለመፈጸሙ ሠራተኛው ከፍተኛ ችግር ላይ ወድቋል ” - የፐርፐዝ ብላክ ባለአክሲዮኖች
ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ሕብረት ባንክ ካለው ገንዘብ ውጪ በሌሎች ባንኮች ያለውን ገንዘብ እንዲያንቀሳቅስ ፍርድ ቤት ውሳኔ ቢሰጥም በዐቃቢ ህግ ይጎባኝ ውሳኔው መታገዱን የፍርድ ቤት ሰነድና ባለአክሲዮኖች አመለከቱ።
ሁነቱን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ያስረዱት ባለአክሲዮኖች የፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ አካውንት ለሰባት ወራት ተዘግቶ መቆየቱን፣ በልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለደመወዝና ሥራ ማስኬጃ ክርክር ሲካሄድ ቆይቶ እንደነበር ገልጸዋል።
በክርክር ሂደቱም፣ ፍርድ ቤት ሕብረት ባንክ ከተቀመጠው ገንዘቡ ውጪ በሌሎች ባንኮች ያለው የፐርፐዝ ብላክ ገንዘብ እንዲንቀሳቀስ፣ ለማንቀሳቀስ አስተዳዳሪ እንዲሾም ወስኖ እንደነበር አስረድተዋል።
“ነገር ግን ዐቃቤ ሕግ ውሳኔውን በመቃወም ይግባኝ ጠይቆ የስር ፍርድ ቤቱ የሰጠውን ውሳኔ አሳግዶታል” ብለዋል።
“ድርጅቱ ለኪራይ፣ ደመወዝና ለሌሎች ወጪዎች ክፍያ ባለመፈጸሙ ሠራተኛው ከፍተኛ ችግር ላይ ወድቋል” ያሉት ባለክሲዮኖቹ፣ “ድርጅቱ የሚፈርስ እንኳን ከሆነ አግባብ ባለው መንገድ መፍረስ ነበረበት እጅግ ከባድ ሁኔታ ተፈጥሯል” ሲሉ አማረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው ሰነድ፣ “መዝገቡ ከቀጠሮ በፊት የቀረበው ይግባኝ ባይ በቀን 10/6/2017 ዓ/ም በተፃፈ አቤቱታ ያቀረዝነው ይግባኝ ታይቶ የመጨረሻ ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስ የፌ/ከፍ/ፍርድ ቤት በወ/መ/ቁ 326384 የሰጠው ውሳኔ ታግዶ እንዲቆይ እንዲታዘዝልን በሚል ባቀረበው አቤቱታ ነው” ይላል።
አክሎም፣ ይግባኝ ቅሬታ ለመስማት ለ20/06/2017 ዓ/ም የተያዘው ቀጠሮ ተሰብሮ የእግድ አቤቱታውን በመመርመር ዝርዝር ትዕዛዝ መስጠቱን ያስረዳል።
የፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ አካውንቶች መዘጋታቸው፣ የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍስሃ እሸቱ (ዶ/ር) አገር መውጣታቸው አይዘነጋም።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ሕብረት ባንክ ካለው ገንዘብ ውጪ በሌሎች ባንኮች ያለውን ገንዘብ እንዲያንቀሳቅስ ፍርድ ቤት ውሳኔ ቢሰጥም በዐቃቢ ህግ ይጎባኝ ውሳኔው መታገዱን የፍርድ ቤት ሰነድና ባለአክሲዮኖች አመለከቱ።
ሁነቱን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ያስረዱት ባለአክሲዮኖች የፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ አካውንት ለሰባት ወራት ተዘግቶ መቆየቱን፣ በልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለደመወዝና ሥራ ማስኬጃ ክርክር ሲካሄድ ቆይቶ እንደነበር ገልጸዋል።
በክርክር ሂደቱም፣ ፍርድ ቤት ሕብረት ባንክ ከተቀመጠው ገንዘቡ ውጪ በሌሎች ባንኮች ያለው የፐርፐዝ ብላክ ገንዘብ እንዲንቀሳቀስ፣ ለማንቀሳቀስ አስተዳዳሪ እንዲሾም ወስኖ እንደነበር አስረድተዋል።
“ነገር ግን ዐቃቤ ሕግ ውሳኔውን በመቃወም ይግባኝ ጠይቆ የስር ፍርድ ቤቱ የሰጠውን ውሳኔ አሳግዶታል” ብለዋል።
“ድርጅቱ ለኪራይ፣ ደመወዝና ለሌሎች ወጪዎች ክፍያ ባለመፈጸሙ ሠራተኛው ከፍተኛ ችግር ላይ ወድቋል” ያሉት ባለክሲዮኖቹ፣ “ድርጅቱ የሚፈርስ እንኳን ከሆነ አግባብ ባለው መንገድ መፍረስ ነበረበት እጅግ ከባድ ሁኔታ ተፈጥሯል” ሲሉ አማረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው ሰነድ፣ “መዝገቡ ከቀጠሮ በፊት የቀረበው ይግባኝ ባይ በቀን 10/6/2017 ዓ/ም በተፃፈ አቤቱታ ያቀረዝነው ይግባኝ ታይቶ የመጨረሻ ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስ የፌ/ከፍ/ፍርድ ቤት በወ/መ/ቁ 326384 የሰጠው ውሳኔ ታግዶ እንዲቆይ እንዲታዘዝልን በሚል ባቀረበው አቤቱታ ነው” ይላል።
አክሎም፣ ይግባኝ ቅሬታ ለመስማት ለ20/06/2017 ዓ/ም የተያዘው ቀጠሮ ተሰብሮ የእግድ አቤቱታውን በመመርመር ዝርዝር ትዕዛዝ መስጠቱን ያስረዳል።
የፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ አካውንቶች መዘጋታቸው፣ የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍስሃ እሸቱ (ዶ/ር) አገር መውጣታቸው አይዘነጋም።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia