በትግራይ ወቅታዊ ጉዳይ ለመወያየት የአሜሪካ፣ እንግሊዝ፣ ጣሊያን፣ ጀርመን፣ ዴንማርክ፣ ፈረንሳይ እና የአውሮፓ ህብረት ልዑካን መቀለ መግባታቸው ተገለጸ!
የአሜሪካ፣ እንግሊዝ፣ ጣሊያን፣ ጀርመን፣ ዴንማርክ፣ ፈረንሳይ እና የአውሮፓ ህብረት ልዑካን ዛሬ የካቲት 4 ቀን 2017 ዓ.ም መቀለ መግባታቸው ተገለጸ።ልዑካኑ መቀለ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
የልዑካን ቡድኑ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት አተገባበር፣ በትግራይ ወቅታዊ ሁኔታ እና በክልሉ ዘላቂ ሰላም ማረጋገጥ በሚቻልባቸው መንገዶች ዙሪያ ከጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ጋር ይመክራሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ከትግራይ ቴሌቪዢን ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
ከሳለፍነው አመት መገባደጃ ጀምሮ በኢትዮጵያ የአሜሪካን አምባሳደር የሆኑት ኤርቪን ማሲንጋን ጨምሮ የበርካታ ሀገራት ተወካዮች ወደ ትግራይ በማቅናት በህወሓት አመራሮች መካከል የተፈጠረውን ውዝግብ ለማርገብ ትኩረት ያደረገ ጉብኝቶች ሲያደርጉ እንደነበር ይታወሳል።
https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1
የአሜሪካ፣ እንግሊዝ፣ ጣሊያን፣ ጀርመን፣ ዴንማርክ፣ ፈረንሳይ እና የአውሮፓ ህብረት ልዑካን ዛሬ የካቲት 4 ቀን 2017 ዓ.ም መቀለ መግባታቸው ተገለጸ።ልዑካኑ መቀለ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
የልዑካን ቡድኑ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት አተገባበር፣ በትግራይ ወቅታዊ ሁኔታ እና በክልሉ ዘላቂ ሰላም ማረጋገጥ በሚቻልባቸው መንገዶች ዙሪያ ከጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ጋር ይመክራሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ከትግራይ ቴሌቪዢን ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
ከሳለፍነው አመት መገባደጃ ጀምሮ በኢትዮጵያ የአሜሪካን አምባሳደር የሆኑት ኤርቪን ማሲንጋን ጨምሮ የበርካታ ሀገራት ተወካዮች ወደ ትግራይ በማቅናት በህወሓት አመራሮች መካከል የተፈጠረውን ውዝግብ ለማርገብ ትኩረት ያደረገ ጉብኝቶች ሲያደርጉ እንደነበር ይታወሳል።
https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1