Фильтр публикаций


አስመጪዎች ያለባንክ ዋስትና መላክ የሚችሉት ቅድመ ክፍያ መጠን ላይ ማሻሻያ ሊደረግ ነዉ ተባለ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስመጪዎች ያለባንክ  ዋስትና መላክ በሚቻለው ቅድመ ክፍያ መጠን ላይ ጭማሪ ለማድረግ መመሪያውን እየከለሰ እንደሚገኝ ተሰምቷል።

ላለፉት 27 አመታት ሲተገበር በቆየው አሰራር መሰረት አስመጪዎች ያለባንክ ዋስትና ለሚያስገቡት እቃ በቅድሚያ መላክ/መክፈል የሚችሉት የውጭ ምንዛሬ መጠን ከ5 ሺ ዶላር መብለጥ እንደማይችል የማእከላዊ ባንኩ መመሪያ ደንግጓል።

ይህን ተከትሎ ከ5ሺ ዶላር በላይ ቅድመ ክፍያ መፈፀም ከፈለጉ ከአገር ውስጥ ባንክ ዋስትና ማቅረብ ይጠበቅባቸው እንደነበር ይታወቃል ።

ይህ የጭማሪ መጠኑ ምን ያህል እንደሆነ የተገለፀ ነገር ባይኖርም አዲሱ መመሪያው ግን በቀጣይ መጋቢት ወር ወደ ስራ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል።

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


የእስራኤል ጦር ፍልስጥኤማዉያን በፈቃደኝነት እንዲለቁ የሚያስችል ዕቅድ እንዲነደፍ አዘዘ

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ ጦራቸዉ ጋዛ የሚኖሩ ፍልስጥኤማዉያን ግዛቲቱን በፈቃደኝነት እንዲለቁ የሚያችል ዕቅድ እንዲነድፍ አዘዘ።

የሚንስትሩ ትዕዛዝ የተሰማው የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የጋዛ ሰርጥን ለመቆጣጠር እንደሚፈልጉ ካስታወቁ በኋላ ዓለማቀፍ ተቃዉሞ እየተሰማ ባለበት ወቅት ነው።

የመከላከያ ሚንስትሩ እስራኤል ካትዝ፣ ትራምፕ ከ2 ሚሊዮን በላይ ፍልስጥኤማዉያን የሚኖሩባትን ጋዛን ለመቆጣጠር ማቀዳቸውን አድንቀው «የፕሬዚደንቱን በድፍረት የተሞላ ዕቅድ በደስታ እንቀበላለን ፤ በየትኛውም ዓለም እንደሚሆነው የጋዛ ነዋሪዎች ከመኖሪያቸዉ በነጻነት መውጣት እና መሰደድ ሊፈቀድላቸው ይገባል ብለዋል።

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


“ነፍሳችንን ቢያስከፍለን እንኳን ጋዛን አንለቅም”- የጋዛ ነዋሪዎች

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋዛን የመቆጣጠር እቅድ እንዳላቸው መግለጻቸውን ተከትሎ በርካታ ፍልስጤማውያን ተቃውሟቸውን እየገለጹ ነው።

በትራምፕ ውሳኔ የተገረሙ እና የተደናገጡ የጋዛ ነዋሪ ፍሊጤየማውያን “ጋዛን ለቀን አንወጣም” ሲሉ ተቃውሞዋቸውን አሰምተዋል።

በዴይር አል ባላህ በድንኳን መጠለያ ውስጥ የሚገኙ የጋዛ ነዋሪዎች ከቢቢሲ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የጋዛ ነዋሪዎችን በቋሚነት ወደ ሌላ ስፍራ ለማስፈር የተያዘው እቅድ እንዳስደነገጣቸው በመግለጽ እቅዱ ተቀባይነት የለውም ሲሉ እምቢተኝነታቸውን አመላክተዋል።

“ነፍሳችንን ቢያስከፍለን እንኳን ጋዛን አንለቅም” ያሉት ነዋሪዎቹ፤ “የትራምፕን ውሳኔ እንቃወማለን፣ ጦርቱን አስቁሟል፤ ነገር ግን እኛን ማፈናቀል ህይወታችን እንዲያበቃለት ያደርጋል” ብለዋል።

"በአሜሪካ የተሰራችው እስራኤል በጋዛ የሚገኘውን ቤቶቻችንን ካፈረሰች በኋላ ከፍርስራሽ መውጣት እንዳለብን እየተነገረን ነው፤ በልጆቻችን ውስጥ አንድ የደም ጠብታ እንኳ ቢቀር ጋዛን አንለቅም፣ ተስፋም አንቆርጥም” ብለዋል ነዋሪዎቹ።

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ወደ ዋይትሃውስ እንደገቡ የጋዛ ፍርስራሽ እስኪጸዳ ድረስ ፍልስጤማውያን እንደ ግብጽ እና ዮርዳኖስ ባሉ ሀገራት እንዲጠለሉ ሃሳብ ማቅረባቸው ይታወሳል።

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


የአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት እርዳታ ማቋረጡ ኢትዮጵያ በኤች አይ ቪ ላይ የምታደርገውን ትግል አደጋ ላይ የሚጥል መሆኑን የመንግስታቱ ድርጅት አስታወቀ

ከሩብ ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ የቫይረሱ ተጠቃሚዎችን ለአደጋ ያጋልጣል ሲል አስጠንቅቋል

ከኤች አይ ቪ/ኤድስ ጋር በተያያዘ የአሜሪካ መንግስት ለኢትዮጵያ የሚሰጠው ድጋፍና እርዳታ መቋረጥ በኦሮሚያ እና ጋምቤላ ክልሎች እንዲሁም በአዲስ አበባ ከተማ ለሚገኙ ከ270 ሺ በላይ ለሚሆኑ የቫይረሱ መከላከያ መድሃኒት ተጠቃሚዎችን ህይወት ይበልጥ ከባድ ያደርገዋል ሲል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኤች አይ ቪ/ኤድስ ፕሮግራም አስጠንቀቀ።

በርካቶች ኤች አይቪን ጨምሮ በግብረ ሥጋ ግንኙነት ወቅት የሚተላለፉ በሽታዎችን ለመከላከል የሚውል ኮንዶም ከአሁን በኋላ አይደርሳቸውም ብሏል።

በተጨማሪም የገንዘብ ድጋፍ መቋረጡ የአካባቢ ጤና አጠባበቅ አቅም ለመገንባት የሚደረገውን ጥረት እንዳያደናቅፈው ስጋት እንዳለው አስታውቋል፤ የጤና ባለሙያዎች የሚሰጡት ስልጠና ላይ ተፅዕኖ በማሳደር በኢትዮጵያ የኤችአይቪ በሽታ መከላከል ሂደት ላይ እየተመዘገበ ያለውን እድገት ያዘገየዋል ሲል አመልክቷል።

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


የትግራይ ህዝብ ያደረጋቸው ጦርነቶች “ህልውናውን ለማረጋገጥ እና ለጭቆና እጅ አልሰጥም በማለት ነው” - ህወሓት

ህወሓት የትግራይ ህዝብ የሰላም ምኞት ዕውን እንዲሆን ሁሉም ገንቢ ሚና ይጫወት ሲልም ጥሪ አቅርቧል።

በደብረጺዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ቡድን "የትግራይ ህዝብ እና የትግራይ ልሂቃን ቀዳሚ ምርጫው ሰላም ነው" ሲል ትላንት ጥር 28 ቀን 2017 ዓ.ም አመሻሽ ላይ ጠ/ሚኒስት አብይ አህመድ (ዶ/ር) ጥሪ ማቅረባቸውን ተከትሎ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

ህወሓት የጠ/ሚኒስትሩን ጥሪ ተከትሎ መግለጫ ያወጣ ሲሆን፤ በመግለጫውም "የትግራይ ህዝብ ቀዳሚ ምርጫ ሰላም ነው" ብሏል።

የትግራይ ህዝብን የሰላም ምኞት አውን ለማድረግ ሁሉም ገንቢ ሚና ይጫወት ሲል ጠይቋል። ከማንኛውም አካል ጋር በሰላም ዙሪያ ለመስራት ዝግጁ ነኝ ሲልም አስታውቋል።

ህወሓት በመግለጫው ባለፉት መቶ አመታት የትግራይ ህዝብ ያደረጋቸው ጦርነቶች “ህልውናውን ለማረጋገጥ እና ለጭቆና እጅ አልሰጥም በማለት ነው” ሲል በመግለጽ፤ “የትግራይ ህዝብ ያደረጋቸው ተጋድሎዎች ያኮሩታል እንጂ አያስቆጩትም” ብሏል።


https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


ግብፅ በሕዳሴው ግድብ ፍላጎቷን ለማሳካት፣ የጋዛ ነዋሪዎችን ተቀብላ ማስፈር እንዳለባት አሜሪካ ለካይሮ ገለፀች

ትራምፕ በትናንትናው ዕለት ጋዛን እንቆጣጠራለን ማለታቸው ይታወሳል።

ግብጽ የጋዛ ነዋሪዎችን ተቀብላ እንድታሠፍር ለማግባባት የሕዳሴ ግድብን አጀንዳ እንደ መሳሪያ እየተጠቀመችበት መኾኑን ከዲፕሎማቲክ ምንጮች ሰምቻለሁ ሲል፣ ዘ ኒው ዓረብ ድረገጽ ዘገበ።

  የአሜሪካ ከፍተኛ ልዑካን ቡድንበቅርቡ ወደ ካይሮ በማቅናት፣ ከግብጽ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ባደር አብደላቲና ሌሎች ባለሥልጣናት ጋር በዚኹ ጉዳይ ዙሪያ ተወያይተው እንደነበርም ዘገባው አውስቷል። የሕዳሴው ግድብ ውዝግብን ለመፍታት አሜሪካ ገንቢ ሚና እንድትጫወት ከተፈለገ፣ ግብጽ የጋዛ ነዋሪዎችን ተቀብላ ማስፈር እንዳለባት የአሜሪካ ባለሥልጣናት ለግብጽ አቻዎቻቸው ነግረዋቸዋል ነው የተባለው።

ፕሬዝዳንት ትራምፕ በቀደመው የሥልጣን ዘመናቸው፣ የግድቡን ውዝግብ ለመፍታት ያቀረቡትን አስገዳጅ የስምምነት ሰነድ ኢትዮጵያ ውድቅ ማድረጓ የሚታወስ ነው።

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


በአዲስ አበባ የሚገኙ የትግራይ ተወላጆች የድጋፍ ሰልፍ እያካሄዱ ነው

ምርጫችን ሠላም ነው" በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ የሚገኙ የትግራይ ተወላጆች የድጋፍ ሠልፍ እያካሄዱ ነው።

በመዲናዋ የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች ለሠላም ያላቸውን ድጋፍ እና ቁርጠኝነት የሚገልፅ ሰልፍ ነው እያካሄዱ የሚገኙት።

ነዋሪዎቹ ለትግራይ ልማት እንጂ ዳግም ጦርነት አያሥፈልጋትም፣ በክልሉ ያለውን ሠላማዊ እንቅሥቃሴ እና መሠል እንቅሥቃሴዎች በማሥተጓጎል የሚገኝ ጥቅም የለም የሚሉ እና ሌሎች መልዕክቶችን እያስተላለፉ ይገኛሉ።

ለትግራይ እና ነዋሪዎቿ ሠላም በምንም የማይተካ መሆኑንም ሠልፈኞቹ አጽንኦት ሰጥተዋል።

ፖለቲከኞች ችግሮቻቸውን በመነጋገር እንዲፈቱ ለሠላም ጠንቅ ከመሆን እንዲታቀቡም አስገንዝበዋል።

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


የአሜሪካው የስለላ ድርጅት ሲአይኤ ሁሉንም ሰራተኞቹን ሊያሰናብት ነው

ሲአይኤ የስራ መልቀቂያ ለሚያስገቡ ሰራተኞቹ የስምንት ወራት ደመወዝ እከፍላለሁ ብሏል።

ሲአይኤ በአሜሪካ ህግን ተከትለው ከማይፈጸሙ ጥፋቶች ጀርባ እጁ አለበት የሚል ቅሬታ ቀርቦበታል።

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


በመምህርነት ሙያ ከዲፕሎማ ወደ መጀመሪያ ዲግሪ የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና በክረምት መርሐግብር ሲከታታሉ ለቆዩ መምህራን የመውጫ ምዘና ቅዳሜ የካቲት 1/2017 ዓ.ም ይሰጣል።

የምዘና ፈተናው መምህራኑ በሚኖሩባቸው አቅራቢያ ባሉ አሰልጣኝ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና እንደተጠናቀቀ ማለትም ቅዳሜ የካቲት 1/2017 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር መግለፁ ይታወሳል።

ትምህርት ሚኒስቴር ለዩኒቨርሲቲዎች እና ለክልል ትምህርት ቢሮዎች በጻፈው ደብዳቤ፥ የመውጫ ምዘና ላልወሰዱ መምህራን ማስረጃ እንዳይሰጥ ማሳሰቡ ይታወቃል።

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


በትግራይ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት አለ - የመቐለ ከተማ ከንቲባ

"ምንም እንኳ የትግራይ ጊዝያዊ አስተዳደር በይፋ መፈንቅለ መንግስት ተደርጓል ብሎ ባያውጅም በመቐለ ከተማ በስሙ መጠራት ያለበት ወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት አለ" ሲሉ በጊዝያዊ አስተዳደሩ የመቀለ ከተማ ከንቲባ ተደርገው ተሾመው አሁን ድረስ ፅህፈት ቤታቸው ገብተው ስራ መጀመር ያልቻሉት አቶ ብርሀነ ገብረ እየሱስ ገለፁ።

ከንቲባው መቀመጫውን በመቀለ ከተማ ካደረገው "ላዛ ትግርኛ" ከተሰኘ የሚድያ ተቋም ጋር በነበራቸው ቆይታ በአሁኑ ሰዓት በትግራይ ውስጥ ከፕሬዝደንቱ በላይ የሆነና ለፕሬዝደንቱና ለካቢኔው የማይታዘዝ ሀይል ተፈጥሯል ሲሉ ተደምጠዋል።

"ከትግራይ ሰማይ ስር" በተሰኘው ፕሮግራም ላይ ሰፋ ያለ ቃለ መጠየቅ የሰጡት ከንቲባው ከህዳር 1 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ የመቀለ ከተማ ህጋዊ ከንቲባ ተደርጌ ብሾምም ወደ ፅህፈት ቤቴ ገብቼ ስራ እምዳልጀምር የመቀለ ከተማ አስተዳደር ፅህፈት ቤት እንዲጠብቁ በተመደቡ በታጣቂዎች ወደ ቢሮየ እንዳልገባ፣ የመቀለ ከተማ ህዝብም አገልግሎት እንዳያገኝና እንዲጉላላ እየተደረገ ይገኛል ይህ የሚደረገው ደግሞ በወታደራዊ ሀይል ነው ሲሉ ከንቲባው ገልፀዋል።

ከመቀለ ከተማ ከንቲባው በተጨማሪ ከ8 ወራት በፊት የትግራይ ሰሜን ምዕራብ ዞን እንዲያስተዳድሩ የተመረጡት ሃለፊ ብሎም ከ4 ወራት በፊት ደግሞ መካከለኛው ዞን እንዲያስተዳድሩ በጊዝያዊ አስተዳደሩ የተሾሙ ግለሰቦችም በስራ ገበታቸው ተገኝተው መስራት አለመቻላቸው ተገልፆል።


https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


አየር መንገዱ የሀገር ውስጥ ተርሚናል አገልግሎቱ ለጊዜው መቋረጡን ገለፀ!!

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሀገር ውስጥ ተርሚናል አገልግሎቱ ለጊዜው መቋረጡን አስታውቋል፡፡

በዚህም የሀገር ውስጥ መንገደኞች በዓለም አቀፍ መንገደኞች ማስተናገጃ ተርሚናል በኩል እንዲስተናገዱ አየር መንገዱ አሳስቧል፡፡

አየር መንገዱ ጉዳዩን አስመልክቶ በሰጠው መግለጫ፤ ዛሬ ከቀኑ 6:30 በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የሀገር ውስጥ መንገደኞች ማስተናገጃ ሕንፃ ውስጥ ወደ በረራ ይዞ መግባት ከሚከለከሉ ቁሳቁሶች መካከል ከመንገደኞች የሚሰበሰብ የሲጋራ መለኮሻ (ላይተር) ጊዜያዊ የማስቀመጫ ስፍራ ውስጥ ጭስ በመከሰቱ ለመንገደኞች ደህንነት ሲባል ሕንፃው ለጊዜው አገልግሎት አቋርጧል ብሏል፡፡

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


በትረምፕ ትዕዛዝ በርከት ያሉ የዩናይትድ ስቴትስ የትምህርት ሚንስቴር ሠራተኞች እረፍት እንዲወስዱ ታዘዙ!

የፌደራሉ የሠራተኞች ማኅበር እንዳመለከተው በዩናይትድ ስቴትስ ትምህርት ሚንስቴር ውስጥ የሚሠሩ ቁጥራቸው የበዛ ሠራተኞች ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በአወጡት እና በፌዴራል መንግሥት ውስጥ ‘ብዝሃነት፣ ፍትሃዊነት እና አካታችነት’ የተባሉ ፕሮግራሞችን ለመሰረዝ በሰጡት ትእዛዝ መሰረት መፈጸሙን አመልክቷል።

የዩናይትድ ስቴትስ የመንግሥት ሠራተኞች ፌዴሬሽን የትምህርት ሚንስቴር ሠራተኞችን የሚወክለው 252 የተባለው ጽ/ቤት ፕሬዝዳንት ሸሪያ ስሚዝ በትላንትናው ዕለት ሲናገሩት ደሞዝ እየተከፈላቸው ለጊዜው እረፍት እንዲወስዱ የታዘዙት ሠራተኞች ቁጥራቸው ምን ያህል እንደሆነ፤ ወይም በምን ምክንያት ይህ ውሳኔ ሊሰጣቸው እንደቻለ ግልፅ አይደለም’ ብለዋል።

ቢያንስ ቁጥራቸው 55 የሚደርሱ ሠራተኞች ቀደም ሲል ትራምፕ በፈረሙት የፕሬዝዳንታዊ ትዕዛዝ መሰረት ወዲያውኑ እንደሚፈጸም የሚገልጽ የኢሜል መልዕክት ባለፈው አርብ ደርሷቸዋል።ትራምፕ ‘የትምህርት ሚኒስቴርን እዘጋለሁ’ የሚል ቃል በመግባት የምርጫ ቅስቀሳ ማድረጋቸው ይታወሳል።

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


ከአዲስ አበባ የሚወጡ 4 የፍጥነት መንገዶችን ለመገንባት ጥናት እየተደረገ እንደሚገኝ ተገለጸ!

ከአዲስ አበባ በተለያዩ መስመሮች የሚወጡ 4 አዳዲስ የፍጥነት መንገዶችን ለመገንባት የሚያስችል ጥናት እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር አስታውቋል፡፡ጥናቱ እየተደረገ የሚገኘው ከአዲስ አበባ ደሴ፣ ከአዲስ አበባ ጅማ፣ ከአዲስ አበባ ደብረማርቆስ እና ከአዲስ አበባ ነቀምት በሚዘልቁት መንገዶች ላይ መሆኑ ተነግሯል፡፡

እነዚህ የፍጥነት መንገዶች የሚገነቡበት የጥራት ደረጃ ፣ የሚኖራቸውም አጠቃላይ የጎን ስፋት ከፍ ያለ እና የሚገነቡበት መልክአ ምድር አብዛኛውን ተራራማ ቦታዎችን የሚሸፍን በመሆኑ ከፍተኛ የሆነ ወጪ እና የቆረጣ ሥራዎችን የሚጠይቁ መሆናቸውን አስተዳደሩ ገልጿል፡፡

በጥናቱ መሰረት ፕሮጀክቶቹ የሚኖራቸው ርዝመት በአማካይ 300 ኪሜ ሲሆን፤ ግንባታቸውም በተለያዩ ምዕራፎች እና በተወሰነ ኪሎሜትር ተከፋፍሎ እንደሚጀመርም ተመላክቷል፡፡በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቶቹ የአዋጭነት እንዲሁም መሰረታዊ የዲዛይንና የዝግጅት ሥራ እየተከናወነ ሲሆን፤ ለዝግጅት ሥራው የሚያስፈልጉ የጥናት ሥራዎችንም ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑም ተገልጿል።

አራቱን የፍጥነት መንገዶች ለመገንባት የሚያስፈልገው ወጪ የሚሸፈነው በመንግሥትና የግል አጋርነት ትብብር ስለመሆኑም አሐዱ ከአስተዳደሩ ያገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡ከፍጥነት መንገዶቹ መካከል የአዲስ ጅማ እና አዲስ ደብረ ማርቆስ ፕሮጀክቶች ለገንዘብ ሚኒስቴር የመንግሥት የግል አጋርነት ቦርድ የቀረቡ ሲሆን፤ ቀሪዎቹም በቅርቡ ይቀርባሉ ተብለው እንደሚጠበቁ ተጠቁሟል።

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


ፕሬዝዳንት ትራምፕ ዩናይትድ ስቴትስ "የጋዛን ሰርጥ እንደምትቆጣጠርና" እና "በባለቤትነት እንደምትይዝ" ዛሬ የእስራኤሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ካነጋገሩ በሗላ በመግለጽ "የፍልስጤም ህዝብ ሌላ ቦታ መኖር አለበት" የሚለውን ሀሳብ ማስተዋወቃቸውን ቀጥለዋል::

ከእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ጋር በጋራ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ አስተያየታቸው የሰጡት ትራምፕ "በጋዛ የሚገኙት ፍልስጤማውያን በዳግም ግንባታ ሂደት ውስጥ ማለፍ የለባቸውም:: እዛ በአሳዛኝ የህልውና ሁኔታ ሲኖሩ ቆይተዋል” ብለዋል።

ዛሬ ከሰዓት በኋላ፣ በኦቫሉ ቢሮቸው ውስጥ ከናታንያሁ ጋር ባደረጉት ውይይት፣ ፕሬዝዳንቱ "ፍልስጤማውያን በሌላ ቦታ 'በቆንጆ ቤቶች' ውስጥ 'በቋሚነት መቋቋም' አለባቸው"ም ብለዋል።

ትራምፕ "አሜሪካ የጋዛ ሰርጥን ትቆጣጠራለች:: ስራ እንሰራለን:: እኛ ባለቤት እንሆናለን:: በዛ አካባቢ ላይ ያሉትን አደገኛ ያልተፈነዱ ቦምቦችን እና ሌሎች መሳሪያዎችን እናመክናለን:: የተበላሹ ሕንፃዎችን እናስወግዳለን:: እናስተካክላለን:: ለአካባቢው ሰዎች ያልተገደበ ቁጥር ያላቸው ስራዎችን እና መኖሪያ ቤቶችን የሚያቀርብ የኢኮኖሚ ልማት መፈጠር" አለበት ሲሉ በንግግራቸው አሰምተዋል::

"ወደ ኋላ አትመለሱ:: ወደ ኋላ ከተመለሳችሁ ወዳለፋት መቶ አመት ወደ ነበረው መንገድ መመለስ ነው" ሲሉም ለፍልስጤማውያን መልዕክት አስተላልፈዋል::

ፕሬዚዳንቱ "የሌላ ሉዓላዊ ግዛትን ለመረከብ ምን ስልጣን አለዎት?" በሚል በጋዜጠኞች ተጠይቀው፣ ጉዳዩን ለወራት በቅርበት ሲያጠኑት እንደቆዩ ገልጸው "ቦታውን ለረጅም ጊዜ በባለቤትነት መያዝ የሚለውን አይቼዋለሁ፣ ይህም በመካከለኛው ምስራቅ ክፍል፣ ምናልባትም በዛ አካባቢ በአጠቃላይ ትልቅ መረጋጋትን እንደሚያመጣ ነው ያየሁት" ብለዋል ።

https://t.me/voa_amharic1


እስራኤል በጋዛ የተኩስ አቁም ጉዳይ ላይ ለመወያየት ወደ ኳታር ተደራዳሪ ቡድን ልትልክ ነው

የትራምፕ እና የኔታኒያሁ ስብሰባ በዋሽንግተን ዲሲ የሚካሄደው የጋዛ የተኩስ አቁም ስምምነት ሁለተኛ ምዕራፍ ላይ በእስራኤል እና በሃማስ መካከል ቀጥተኛ ያልሆነ ድርድር ሊደረግ ባለበት ወቅት ነው።የኔታኒያሁ ጽህፈት ቤት ዛሬ ቀደም ብሎ እንዳስታወቀው የእስራኤል ተደራዳሪ ቡድን በመጪዎቹ ቀናት በሁለተኛው ምዕራፍ ላይ ለመነጋገር ወደ ኳታር ዋና ከተማ ዶሃ ለመጓዝ በዝግጅት ላይ መሆናቸዉን አስታዉቋል።

ቡድኑ በስምምነቱ ላይ "ለመቀጠል ቴክኒካዊ ዝርዝሮችን" እንደሚወያይ በመግለጫው ተነግሯል፡፡ጦርነቱ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ኳታር ከግብፅ እና ከአሜሪካ ጋር በመሆን በእስራኤል እና በሃማስ መካከል ሽምግልና ላይ ነች።ትራምፕ ከእስራኤል እና ከሌሎች ሀገራት ጋር በመካከለኛው ምስራቅ ያደረጉት ውይይቶች "እድገት እያሳዩ" ብለዋል፡፡ነገር ግን ምንም ዝርዝር መግለጫ አልሰጡም፡፡

ፕሬዚዳንቱ ግን የተኩስ አቁም ስምምነት እርግጠኛ አለመሆኑን አምነዋል።ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት ሰላሙ እንዲሰፍን ምንም አይነት ዋስትና መስጠት እንደማችሉ አክለዋል።ሰኞ እለት ከኔታንያሁ ጋር የተገናኙት የመካከለኛው ምስራቅ መልዕክተኛው ስቲቭ ዊትኮፍ አክለው እኛ በእርግጠኝነት ለሰላም ተስፋ እናደርጋለን ብለዋል።

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


የጤና ሚኒስትር በሲዲሲ እና ዩኤስኤአይዲ የበጀት ድጋፍ የተቀጠሩ ሠራተኞችን ዉል ማቋረጡን አስታወቀ!

ከ 5 ቀን በፊት ለሁሉም መንግስታዊ የጤና ቢሮ በተፃፈው ደብዳቤ እንደተገለፀዉ በጤና ሚኒስቴር ድጋፍ ከዩኤስኤአይዲ እና ሲዲሲ ጋር በተደረገው ውል በኮንትራት የተቀጠሩ ሠራተኞች ዉል መቋረጡን እና ይህን ዉሳኔ እንዲያስፈፅሙ ማሳሰቢያ ሰጥቷል።

ሚኒስትሩ ለዚህ እርምጃ የደረሰዉ ከአሜሪካ መንግሥት በ "ሲዲሲ" ወይም "ዩኤስኤአይዲ" አማካይነት በተገኘ የበጀት ድጋፍየ ሚከናወን ማንኛውም ስራም ሆነ ክፍያ ከየካቲት 17 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ እንዲቋረጥ ማሳሰቢያ ስለደረሰዉ እንደሆነ ጠቁሟል።

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


የሱዳን ወታደራዊ መንግሥት፣ የሱዳን ፈጥኖ ደራሹ ኃይል በኦምዱርማን ከተማ ባንድ የገበያ ቦታ ላይ ፈጽሞታል ላለው የከባድ መሳሪያ ጥቃት ለተመድ የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤትና ለተመድ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን አቤቱታ ማስገባቱን የመካከለኛው ምሥራቅ የዜና ምንጮች ዘግበዋል።

የሱዳን ባለሥልጣናት፣ ቡድኑ በዚህ ጥቃት በርካታ ሰላማዊ ሰዎችን በመግደል ዓለማቀፍ ሕግጋትን ኹሉ ጥሷል በማለት መክሰሳቸውን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል።

የሱዳን መንግሥት በዚኹ አቤቱታው፣ ቡድኑ በእዚህና መሰል ጥሰቶች፣ አሸባሪ ድርጅት ተብሎ ሊፈረጅ የሚያስችሉትን መስፈርቶች አሟልቷል ብሏል ተብሏል።

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


የዩ.ኤስ.ኤይድ ዋና ቢሮ ሰራተኞች ከዛሬ ጀምሮ በቤታቸው እንዲቆዩ ትዕዛዝ ተላልፏል

የአሜሪካ ዓለም አቀፍ የልማት ኤጀንሲ (USAID) ዋና ቢሮ ሰራተኞች ከዛሬ ጀምሮ በቤታቸው እንዲቆዩ ትእዛዝ መተላለፉን ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን እየዘገቡ ነው፡፡

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትላንት ለጋዜጠኞች በሰጡት ቃል የአሜሪካ አለም አቀፍ የልማት አጀንሲን እየመሩ የሚገኙት “ፅንፈኛ የዘራፊዎች ቡድን ናቸው፤ ለማባረር ውሳኔ እናሳልፋለን” ብለው ከተናገሩ ከሰዓታት በኋላ ነው ሰራተኞቹ ዛሬ ወደ ቢሮ እንዳይመጡ ትዕዛዝ የተሰጣቸው፡፡

አዲሱ የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ የአሜሪካ ዓለም አቀፍ የልማት ኤጀንሲ ኃላፊነትን ደርበው መረከባቸውም ታውቋል፡፡

በፕሬዝዳንት ትራምፕ አስተዳደር የመንግስት ተቋማትን ሪፎርም ለማድረግ ስልጣን የተሰጣቸው ቱጃሩ ኤለን መስክ ከውሳኔው በስተጀርባ ቁልፍ ሚና እንዳቸውም እየተገለፀ ይገኛል፡፡

በአውሮፓውያኑ 1961 በፕሬዝዳንት ጆን ኤፍ ኬኔዲ የተመሰረተው ዩ.ኤስ.ኤይድ፤ ለሰብዓዊ እርደታ፣ ድህነት ቅነሳ፣ ለበሽታ መከላከል፣ ለተፈጥሮ አደጋ ጊዜ ስራዎች ከፍተኛ የገንዘብ ድጋፍ የሚያደርግ ተቋም እንደነበር የሚታወስ መሆኑን ኤፒ ኒውስ እና ሲኤንኤን ዘግበዋል፡፡

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


ኬንያ በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ላይ ያነጣጠረ ወታደራዊ ዘመቻ መጀመሯን አስታወቀች!

ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር በምትዋሰንበት የድንበር ግዛቶቿ ላይ ባሉ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ላይ ያነጣጠረ ወታደራዊ ዘመቻ መጀመሯን አስታወቀች።የኬንያ መንግሥት የጦሩ አባላት ተደብቀውባቸዋል ባላቸው የማርሳቤት እና ኢሲዮሎ ግዛቶች ላይ "ወንጀለኞችን የማስወገድ" የተሰኘ ከፍተኛ የጸጥታ ዘመቻ ባለፈው ወር ጥር፣ 25/ 2017 ዓ.ም መጀመሩን ገልጿል።

እነዚህ ግዛቶችን "ድንበር ዘለል የወንጀል ድርጊቶችን ለማሳለጥ የሚጠቀምባቸው ናቸው" ሲል የኬንያ መንግሥት ብሔራዊ የፖሊስ አገልግሎት ሰኞ ጥር፣ 26/ 2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ቡድኑን ወንጅሎታል።የኢትዮጵያ መንግሥት በተለያዩ ጥሰቶች የሚወነጅለው "ሸኔ" እያለ የሚጠራው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት በኬንያ ግዛቶች ውስጥም ህገወጥ የማዕድን ማውጣትን ጨምሮ ሌሎች ጥሰቶች እየፈጸመ ነው ኬንያ ወንጅላለች።

የኬንያ ብሔራዊ ፖሊስ ቡድኑ "በተለያዩ ህገወጥ የጦር መሳሪያ፣ አደንዛዥ ዕጾች ዝውውር፣ ህገወጥ የማዕድን ማውጣት ህገወጥ የሰዎች ዝውውር ንግድ ተሰማርቶ ይገኛል" ብሎታል በመግለጫው።የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት "ለገንዘብ ሲል እገታዎችን በመፈጸም እንዲሁም ድንበር ዘለል ወረራዎችን በማካሄድ እና በጎሳዎች መካከል ግጭቶች እንዲቀሰቀሱ በማድረግ ለኬንያ የብሔራዊ ደህንነት ከፍተኛ ስጋት" ሆኗል ሲል መግለጫው አስፍሯል።

የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት በበኩሉ ቡድኑን መወንጀል አዲስ ነገር እንዳልሆነ ጠቅሶ በዘረፋዎችም ሆነ በህገወጥ ተግባራት እንዳልተሳተፈ እና "ለፍትህ" የሚታገል ድርጅት መሆኑን ለቢቢሲ ገልጿል።"እንዲህ አይነት ጥሰቶችን የሚፈጽሙ አካላትን ከኬንያ መንግሥት ጋር በመተባባር እንደሚዋጉ" የጦሩ ዋና አዛዥ አማካሪ ጂሬኛ ጉዴታ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

ኬንያ በታጣቂዎቹ ላይ የጀመረችው ዘመቻ ባለፈው ወር የኢትዮጵያ ብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጄኔራል አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ወደ ኬንያ ተጉዘው ከአገሪቱ ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶ ጋር ከተነጋገሩ በኋላ ነው።በውይይቱ ላይ የኬንያው የብሔራዊ መረጃ አገልግሎት ዳይሬክተር ጄኔራል ኑረዲን ሐጂ ተገኝተው ነበር።

ታጣቂው ቡድን "በኬንያ ቦረና እና በኢትዮጵያ ኦሮሞ መካከል ያለውን የባህል ትስስር እንዲሁም ቅርብ ዝምድና በመጠቀም በማርሳቤት እና ኢሶዮሎ ግዛቶች ውስጥ ባሉ ህዝቦች መካከል ሰርጎ በመግባት በድንበር አካባቢ በሚኖሩ ማህበረሰቦች ላይ ጥሰቶችን" እየፈጸመ ይገኛል ብሎታል የኬንያ ፖሊስ መግለጫ።

መግለጫው አክሎም "ቡድኑ በሴቶች እና በታዳጊዎች ላይ ወሲባዊ ጥቃቶችን ጨምሮ ማስፈራራት፣ በኃይል ንብረትን መውሰድ በአካባቢው በመፈጸሙ ማህበረሰቡን ለሰቆቃ ዳርጎታል" ብሏል።

ህይወትን፣ ንብረትን እንዲሁም ሰላምን ለማስጠበቅ በግዛቲቱ ተደብቀው የሚገኙ "የኦሮሞ ነጻነት ወንጀለኞችን ለማስወገድ" የኬንያ ብሔራዊ የፖሊስ አገልግሎት የወታደራዊ የመጀመሪያ ምዕራፍ ዘመቻ በይፋ መጀመሩን የአገሪቱ ፖሊስ ምክትል ዋና አዛዥ ጊልበርት ማንጊሲ እንዲሁም የወንጀል ምርመራ አገልግሎት ዳይሬክተር መሀመድ አሚን በትናንትናው ዕለት ገልጸዋል።

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


በሩዋንዳ የሚደገፉት ኤም 23 አማፂያን በኮንጎ የተኩስ አቁም አወጁ

በሩዋንዳ የሚደገፈው አማጺ ቡድን በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በሰብዓዊ ጉዳዮች ምክንያት የተኩስ አቁም ማወጁን አስታዉቋል፡፡የኤም 23 አማፂ ጥምረት ከማክሰኞ ጀምሮ የአንድ ወገን የተኩስ አቁም ተግባራዊ እንደሚያደርግ ይፋ አድርል። ከጎረቤት ሩዋንዳ በመጡ በሺዎች በሚቆጠሩ ወታደሮች የሚደገፈው ቡድኑ ባለፈው ሳምንት የምስራቅ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ግዛት ዋና ከተማ የሆነችውን ጎማንን የተቆጣጠረ ሲሆን የተባበሩት መንግስታት በበኩሉ 900 ሰዎች ሲሞቱ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ደግሞ ተፈናቅለዋል ብሏል።

ሰዎች ከጦርነቱ እንዲያመልጡ የሚያስችል የሰብአዊነት ኮሪደር እንዲቋቋም ጥሪዎች እየጨመሩ ይገኛል። ይሁን እንጂ በኪንሻሳ የሚገኘው የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ መንግስት ስለ ተኩስ አቁሙ አፋጣኝ አስተያየት አልሰጠም፣ የሀገሪቱ ጦር የተኩስ አቁም ስምምነቱን ሊያከብር እንደሚችል ግልፅ የሆነ መረጃ የለም።"የአሊያንስ ፍሌቭ ኮንጎ (ኤም 23) በኪንሻሳ ገዥው አካል ለተፈጠረው ሰብዓዊ ቀውስ ምላሽ ከየካቲት 4 ቀን 2025 ጀምሮ በሰብአዊነት ምክንያት የተኩስ አቁም እንደሚያውጅ ለሕዝብ ያሳውቃል" ሲል አማፅያኑ በኤክስ ላይ በለጠፈው መግለጫ ላይ አስታዉቋል።

በመንግስት ሃይሎች እና በአማፂያኑ መካከል የተቀሰቀሰው ከባድ ግጭት ለበርካቶች ሞት እና የአካል ጉዳት ዳርጓል።የኮንጎ ጤና ሚኒስቴር ቅዳሜ እለት በጎማ 773 አስከሬኖች መነሳታቸዉን እና አንዳንዶቹ በጎዳና ላይ እንደሚገኙ ገልጿል።የዓማፅያኑ ጥምረት የኮንጎ ታጣቂ ኃይሎች ነፃ በወጡ አካባቢዎች ወገኖቻቸውን የሚገድሉ ቦምቦችን በካቩሙ አውሮፕላን ማረፊያ ወታደራዊ አውሮፕላኖችን መጠቀማቸውን ያወግዛል ብሏል።

የኮንጎ መንግስት ወደ 3 ሚሊዮን የሚጠጋ ህዝብ ያላትን የጎማ ከተማ ከአማጺ ቡድኑ እጅ ለማስመለስ ቃል ገብቷል። ኮንጎ ሩዋንዳ ኤም 23ን ለመደገፍ ወታደሮቿን ወደ ጎማ ልካለች ስትል ከሳለች።የሩዋንዳው ፕሬዝዳንት ፖል ካጋሜ ሰኞ እለት ኤም 23ን ትደግፋላችሁ የሚለውን ክስ በማስተባበል የሀገራቸው ወታደሮች በኮንጎ ምስራቃዊ ክፍል ውስጥ እንዳሉ የማያውቁ መሆኑን እና በኤም 23 በታጠቀው ቡድን እና በኮንጎ ወታደሮች መካከል የተደረገ ውጊያ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ህይወት ነጥቋል ሲሉ ተደምጠዋል፡፡

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1

Показано 20 последних публикаций.