Addis Ababa Education Bureau


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


ይህ ቻናል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የቴሌግራም ቻናል ሲሆን በከተማ አስተዳደሩ እስከ ትምህርት ቤት ድረስ የተከናወኑ እንዲሁም ሀገራዊ ፣ አህጉራዊ እና አለማቀፋዊ የትምህርት መረጃዎች ተደራሽ የሚደረጉበት ነው፡፡

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций


የየካ ክፍለ ከተማ ብልጽግና ፖርቲ ቅርጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መገርሳ ገላና በተማሪዎችና መምህራን መካከል የሚካሄዱ ስፖርታዊ ውድድሮች የርስ በእርስ ወዳጅነትን ከማጠናከሩ ባሻገር ተተኪ ስፖርተኞችን ማፍራት የሚያስችል መርሀ ግብር በመሆኑ የክፍለ ከተማው አስተዳደር ስፖርታዊ ውድድሩ ቀጣይነት እንዲኖረው ተገቢውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አስገንዝበዋል።

የየካ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፈይሳ ወዳጆ በበኩላቸው ስፖርታዊ ውድድሩ ለተከታታይ 15 ቀናት በተለያዩ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች በድምቀት ሲካሄድ መቆየቱን ገልጸው በውድድሩ ክፍለ ከተማውን ወክለው በከተማ ደረጃ በሚካሄድ ተመሳሳይ ውድድር የሚሳተፉ ብቁ ስፖርተኞች መመልመላቸውን አስታውቀዋል።

በስፖርታዊ ውድድሩ የመዝጊያ መርሀግብር በአትሌቲክስ፣ጠረጴዛ ቴኒስ፣ቼዝ፣ቅርጫት ኳስ፣መረብ ኳስ ፣በእግር ኳስ እንዲሁም በሽብርቅ አሸናፊ የሆኑ መምህራን እና ተማሪዎች ከክብር እንግዶች የዋንጫ እና ሜዳልያ ሽልማት የተበረከተ ሲሆን ውድድሩ በ ኬት እንዲካሄድ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላትም የምስጋና ምስክር ወረቀት ተሰቷል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc


የየካ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤት በመንግስትና በግል ትምህርት ቤቶች መካከል "የትምህርት ቤቶች ስፖርት ሊግ ውድድርን ባህል በማድረግ ጤናማ ንቁና ብቁ ትውልድ እንፈጥራለን" በሚል መሪ ቃል ሲያካሂድ የቆየው የተማሪዎችና የመምህራን ስፖርት ሊግ ውድድር በድምቀት ተጠናቀቀ።

(መጋቢት 6/2017 ዓ.ም) በመዝጊያ መርሀ ግብር የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳምሶን መለሰን ጨምሮ የክፍለ ከተማው ብልጽግና ፓርቲ ቅርጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መገርሳ ገላና፣ የክፍለ ከተማና ወረዳ አመራሮች፣ርዕሳነ መምህራን፣መምህራን ፣ተማሪዎች እንዲሁም ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው የትምህርት ማህበረሰብ አካላት የተገኙ ሲሆን በመዝጊያ መርሀግብሩ በአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች መካከል በእግር ኳስ በተደረገ የዋንጫ ጨዋታ ሚያዝያ 23 ትምህርት ቤት ዳንሴን 3 ለ 1 በማሸነፍ የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳምሶን መለሰ በትምህርት ተቋማት የሚካሄዱ ስፖርታዊ ውድድሮች ተማሪዎች በክፍል ውስጥ በንድፈ ሀሳብ የሚማሩትን ትምህርት በተግባር በማሳየት በአካልም ሆነ አዕምሮ የዳበረና ትውልድ ለመፍጠር የሚያስችል ተግባር መሆኑን ገልጸው የየካ ክፍለ ከተማ በተማሪዎችና መምህራን መካከል በዚህ መልኩ ደማቅ ውድድር በማዘጋጀቱ ምስጋና አቅርበው በስፖርታዊ ውድድሩ አሸናፊ ለሆኑ መምህራን እና ተማሪዎች እንኳን ደስ አላችሁ በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል።


የአራዳ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤት በመንግስትና በግል ትምህርት ቤቶች መካከል ሲያካሂድ የቆየው የተማሪዎችና የመምህራን ስፖርት ሊግ ውድድር በድምቀት ተጠናቀቀ።

(መጋቢት 6/2017 ዓ.ም) በመዝጊያ መርሀ ግብሩ የአራዳ ክፍለ ከተማ ዋና አፈጉባኤ አቶ ደሳለኝ አገኘሁ የአራዳ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽህፈት ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ደበሌ እንዲሁም የክፍለ ከተማው ወጣቶችና ስፖርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ይልማ ደረሰን ጨምሮ የክፍለ ከተማና ወረዳ አመራሮች፣ርዕሳነ መምህራን፣መምህራን ፣ተማሪዎች እንዲሁም ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው የትምህርት ማህበረሰብ አካላት ተገኝተዋል።

የአራዳ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽህፈት ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ደበሌ በትምህርት ተቋማት የሚካሄድ ስፖርታዊ ውድድር ተማሪዎች በአካል በመዳበር እና በአዕምሮ በልጽገው በትምህርታቸው ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያስችል ተግባር መሆኑን ገልጸው ስፖርታዊ ውድድሩ በተማሪዎችና መምህራን መካከል በዚህ መልኩ በድምቀት ተካሂዶ እንዲጠናቀቅ ኃላፊነታቸውን ለተወጡ ባለድርሻ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።

ጽህፈት ቤት ኃላፊው አያይዘውም ስፖርታዊ ውድድሩ ለተከታታይ 15 ቀናት በተለያዩ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች በድምቀት ሲካሄድ መቆየቱን ገልጸው በውድድሩ ክፍለ ከተማውን ወክለው በከተማ ደረጃ ለሚካሄድ ውድድር የሚሳተፉ ብቁ ስፖርተኞች መመልመላቸውን አስታውቀዋል።

በስፖርታዊ ውድድሩ የመዝጊያ መርሀግብር በአትሌቲክስ፣ጠረጴዛ ቴኒስ፣ቼዝ፣ቅርጫት ኳስ፣መረብ ኳስ ፣በእግር ኳስ እንዲሁም በሽብርቅ አሸናፊ የሆኑ መምህራን እና ተማሪዎች ከክብር እንግዶች የዋንጫ እና ሜዳልያ ሽልማት የተበረከተ ሲሆን ውድድሩ በስኬት እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላትም የምስጋና ምስክር ወረቀት ተሰቷል።


የሴት የትምህርት አመራሮችን አቅም ለማጎልበት እና ወደ አመራርነት ለማምጣት የሚያስችል ስልጠና ተሰጠ።

(መጋቢት 6/2017 ዓ.ም) ስልጠናው በሁሉም የመንግስት አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለሚገኙ ዋና እና ምክትል ርዕሳነ መምህራን በዘርፉ ልምድ ባላቸው አካላት መሰጠቱን ከመርሀ ግብሩ አዘጋጆች ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የዘርፈ ብዙና ቀዳማይ ልጅነት ትግበራ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወይዘሮ በላይነሽ የሻው በስልጠናው መክፈቻ ባስተላለፉት መልዕክት በትምህርት ዘርፉ የሚገኙ ሴት አመራሮችን አቅም የማጎልበትና ወደ አመራርነት የማምጣት ስራ በከፍተኛ ትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸው የዛሬው የስልጠና መርሀግብር ቢሮው በትምህርት ሴክተሩ ብቃት ያላቸው እና በራስ መተማመናቸው ከፍተኛ የሆነ ሴት የትምህርት አመራሮችን ለማፍራት ያስቀመጠው ግብ ስኬታማ እንዲሆን የሚያስችል መሆኑን አስገንዝበዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ቡድን መሪ አቶ ይልማ ተሾመ በበኩላቸው ስልጠናው በትምህርት ሴክተሩ ብቃታቸው የተረጋገጠና ተጽኖ ፈጣሪ ሴት አመራሮችን ለመፍጠር የሚያስችል መርሀግብር መሆኑን ጠቁመው በቀጣይ ከወረዳ ጀምሮ እስከ ትምህርት ቢሮ ድረስ ለሚገኙ ሴት የትምህርት አመራሮች ተመሳሳይ ስልጠና የሚሰጥ መሆኑንም አመላክተዋል።

ስልጠናውን በአዲስ አበባ ዩኒ ቨርሲቲ የ3ኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ በሚገኙት እና በዘርፉ ከፍተኛ ልምድ ባላቸው ወይዘሮ ሩት ሹሜ እንዲሁም ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ቢሮ በመጡት ወይዘሮ ሰላማዊት በላቸው መሰጠቱን የስልጠናው አስተባባሪዎች አስታውቀዋል።


መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc




















ስልጠናው በመማር ማስተማር ሂደቱ የሚስተዋሉ ችግሮችን በመቅረፍ የተማሪዎች ውጤት እንዲሻሻል የሚያግዝ መሆኑን የቢሮው የመምህራን እና ትምህርት አመራር ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ አበራ ገልጸው በነገው እለት ከ5ኛ እስከ 8ኛ ክፍል ለሚያስተምሩ የእንግሊዘኛ ቋንቋ መምህራን ተመሳሳይ ስልጠና እንደሚሰጥ አስታውቀዋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc



Показано 15 последних публикаций.