✞ እናቱ ታውቅ ነበር ✞
እናቱ ታውቅ ነበረ መድኃኒት መሆኑን
ኢየሱስ አለችው ስታወጣ ስሙን
መልዓኩ ገብርኤል ከእግዚአብሔር ተልኮ
ሲታጠቅ ሲፈታ ፊትሽ ተንበርክኮ
ትይዋለሽ አለሽ ልጅሽን ኢየሱስ
መድኃኒት ነውና ሁሉን የሚፈውስ
አዝ= = = = =
ከስጋዋ ስጋ ነስቶ ከነፍሷ ነፍስ
በተዋህዶ ሚስጢር የኛን ስጋ ቢለብስ
አማኑኤል ተባለ ቢዛመድ ከሰው
ቅዱስ እግዚአብሔር ከኛ ጋር ነው
አዝ= = = = =
ብላ ሰየመችው መድኃኒአለም
ሰውን ወዷልና እስከዘለዓለም
ልጄ ወዳጄ ሆይ ስትለው ነበር
እርሱም ለእናቱ ታዟል በፍቅር
አዝ= = = = =
የትንቢቱን መጽሐፍ እያነበበች
ሀር ወርቁን አስማምታ እየፈተለች
ዙፋኑ መሆኑን አውቃ ነበርና
ገለጸች እራሷን በፍጹም ትህትና
አዝ= = = = =
ጨለማን የሚያርቅ ብርሃን ወለዳለች
እርሷም የብርሃን እናቱ ተባለች
አምላክን በክንዷ ብትታቀፈው
ወላዲተ አምላክ የእርሷ ስም ነው
መዝሙር
ሊቀ መዘምራን ዲያቆን ቴድሮስ ዮሴፍ
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯
እናቱ ታውቅ ነበረ መድኃኒት መሆኑን
ኢየሱስ አለችው ስታወጣ ስሙን
መልዓኩ ገብርኤል ከእግዚአብሔር ተልኮ
ሲታጠቅ ሲፈታ ፊትሽ ተንበርክኮ
ትይዋለሽ አለሽ ልጅሽን ኢየሱስ
መድኃኒት ነውና ሁሉን የሚፈውስ
አዝ= = = = =
ከስጋዋ ስጋ ነስቶ ከነፍሷ ነፍስ
በተዋህዶ ሚስጢር የኛን ስጋ ቢለብስ
አማኑኤል ተባለ ቢዛመድ ከሰው
ቅዱስ እግዚአብሔር ከኛ ጋር ነው
አዝ= = = = =
ብላ ሰየመችው መድኃኒአለም
ሰውን ወዷልና እስከዘለዓለም
ልጄ ወዳጄ ሆይ ስትለው ነበር
እርሱም ለእናቱ ታዟል በፍቅር
አዝ= = = = =
የትንቢቱን መጽሐፍ እያነበበች
ሀር ወርቁን አስማምታ እየፈተለች
ዙፋኑ መሆኑን አውቃ ነበርና
ገለጸች እራሷን በፍጹም ትህትና
አዝ= = = = =
ጨለማን የሚያርቅ ብርሃን ወለዳለች
እርሷም የብርሃን እናቱ ተባለች
አምላክን በክንዷ ብትታቀፈው
ወላዲተ አምላክ የእርሷ ስም ነው
መዝሙር
ሊቀ መዘምራን ዲያቆን ቴድሮስ ዮሴፍ
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯