በትግራይ ክልል ያለው ውጥረት ወደ ግጭት እንዳያመራ ስጋት ስለመኖሩ ተነገረ‼️
የሁለቱ የህወሓት ቡዱኖች አለመግባባት አሁን ላይ ወደ ግጭት እየተሸጋገረ ያለ ይመስላል። ዛሬ ማለዳ የአዲግራት ከተማ አስተዳደር ፅህፈት ቤት "በጉልበት" የተቆጣጠረው በእነ ደብረፅዮን የሚመራው ህወሓት በአዲግራት ያደረገውን በሌሎች የትግራይ ከተሞች ለመድገም እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ዳጉ ጆርናል በትግራይ የተለያዩ ከተሞች ካሉ ምንጮቹ ሰምቷል።
ዛሬ መጋቢት 2 ቀን 2017 ዓ/ም በነ ደብረፅዮን የሚመራው የህወሓት ቡዱን የመንግስት ስልጣን ከጊዜያዊ አስተዳደሩ ለመቀማት ከሞከረባቸው አከባቢዎች መካከል አንደኛዋ በሆነችው ዓዲ ጉዶም ከተማ ዛሬ በተኩስ ድምፅ ስትናወጥ ማምሸቷን የነገሩን አንድ የከተማዋ ነዋሪ "የዛሬው ድርጊታቸው በስልጣናቸው ለመጣ ምንም ርህራሄ እንደሌላቸው ማሳያ ነው" ብለዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ቡድኑ በመቀለ ከተማ የሚገኙ የክፍለ ከተማ አስተዳደር ፅህፈት ቤቶችን በተለይም የአዲ ሓቂ ክፍለ ከተማ ፅህፈት ቤት በጉልበት ለመቆጣጠር ያደረገው ጥረት በገጠመው ከፍተኛ ተቃውሞ ምክንያት ሳይሳካ መቅረቱ ተገልፆል።
በእነ ደብረፅዮን የሚመራው የህወሓት ቡድን እያካሄደው ያለው ስልጣን የማስመለስ ዘመቻ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በተገለፀበት በዚህ ወቅት በአዲግራትና አዲ ጉዶም ከተሞች የተስተዋለው ክስተት ወደ ግጭት እንዳያድግ ስጋት ጭሯል።
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት አቶ ጌታቸው ረዳ ትላንት በሰጡት መግለጫ በእነ ደብረፅዮን የሚመራው የህወሓት ቡድን ዳግም ወደ ስልጣን እንዳይመለስ ለማድረግ እንደሚሰሩ በገለፁ ማግስት ቡድኑ የአዲግራት ከተማ መስተዳድር በመቆጣጠር የራሱ ከንቲባ ወደ ቢሮ ማስገባቱ በይፋ አስታውቋል።
#ዳጉ_ጆርናል
የሁለቱ የህወሓት ቡዱኖች አለመግባባት አሁን ላይ ወደ ግጭት እየተሸጋገረ ያለ ይመስላል። ዛሬ ማለዳ የአዲግራት ከተማ አስተዳደር ፅህፈት ቤት "በጉልበት" የተቆጣጠረው በእነ ደብረፅዮን የሚመራው ህወሓት በአዲግራት ያደረገውን በሌሎች የትግራይ ከተሞች ለመድገም እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ዳጉ ጆርናል በትግራይ የተለያዩ ከተሞች ካሉ ምንጮቹ ሰምቷል።
ዛሬ መጋቢት 2 ቀን 2017 ዓ/ም በነ ደብረፅዮን የሚመራው የህወሓት ቡዱን የመንግስት ስልጣን ከጊዜያዊ አስተዳደሩ ለመቀማት ከሞከረባቸው አከባቢዎች መካከል አንደኛዋ በሆነችው ዓዲ ጉዶም ከተማ ዛሬ በተኩስ ድምፅ ስትናወጥ ማምሸቷን የነገሩን አንድ የከተማዋ ነዋሪ "የዛሬው ድርጊታቸው በስልጣናቸው ለመጣ ምንም ርህራሄ እንደሌላቸው ማሳያ ነው" ብለዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ቡድኑ በመቀለ ከተማ የሚገኙ የክፍለ ከተማ አስተዳደር ፅህፈት ቤቶችን በተለይም የአዲ ሓቂ ክፍለ ከተማ ፅህፈት ቤት በጉልበት ለመቆጣጠር ያደረገው ጥረት በገጠመው ከፍተኛ ተቃውሞ ምክንያት ሳይሳካ መቅረቱ ተገልፆል።
በእነ ደብረፅዮን የሚመራው የህወሓት ቡድን እያካሄደው ያለው ስልጣን የማስመለስ ዘመቻ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በተገለፀበት በዚህ ወቅት በአዲግራትና አዲ ጉዶም ከተሞች የተስተዋለው ክስተት ወደ ግጭት እንዳያድግ ስጋት ጭሯል።
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት አቶ ጌታቸው ረዳ ትላንት በሰጡት መግለጫ በእነ ደብረፅዮን የሚመራው የህወሓት ቡድን ዳግም ወደ ስልጣን እንዳይመለስ ለማድረግ እንደሚሰሩ በገለፁ ማግስት ቡድኑ የአዲግራት ከተማ መስተዳድር በመቆጣጠር የራሱ ከንቲባ ወደ ቢሮ ማስገባቱ በይፋ አስታውቋል።
#ዳጉ_ጆርናል