✞ይላል አንደበቴ✞
ይላል አንደበቴ እግዚአብሔር ቅዱስ ነው
አይተወኝምና ወላጅ እንደሌለው
ትናንት የጠበቀኝ የነገም ተስፋዬ
ትልሃለች ነፍሴ ፍቅር ነህ ጌታዬ
አዝ----------
የትናንት ሕይወቴን ዞር ብዬ ሳየው
ማምለጫ የሌለው አጥሩም እሾህ ነው
ወደ እረፍቴ ወጣሁ ይድረስ ምስጋናዬ
ደጆች ቢዘጉብኝ በር ሆኖኝ ጌታዬ (2)
አዝ----------
በጥልቁ በረሃ ምግብ መጠጥ ሆኖኝ
መንገዴን አቀናው እጄን በአፌ አስጫነኝ
በእሳትና ውሃ መካከል አልፌ
ተመስገን እላለሁ ቅኔ ሞልቶት አፌ (2)
አዝ----------
የብቸኝነቴን ማዕበል ገስጿል
ለእኔ ብርሃን ሆኖ ለከሳሽ ጨልሟል
ቀስቱን እያጠፈ ታደገኝ ከስቃይ
የጌታዬ ሃሳብ ፍቅር ነው በእኔ ላይ (2)
አዝ----------
ትናንት ዛሬ ነገ ዘላለም ጠባቂ
የልቤን ፍላጎት ሳልነግረው አዋቂ
በባሕርይው ቅዱስ የሌለው አምሳያ
ስሙ ወደቤ ነው መልህቄን መጣያ
ሊቀ መዘምራን
ቴዎድሮስ ዮሴፍ
ይላል አንደበቴ እግዚአብሔር ቅዱስ ነው
አይተወኝምና ወላጅ እንደሌለው
ትናንት የጠበቀኝ የነገም ተስፋዬ
ትልሃለች ነፍሴ ፍቅር ነህ ጌታዬ
አዝ----------
የትናንት ሕይወቴን ዞር ብዬ ሳየው
ማምለጫ የሌለው አጥሩም እሾህ ነው
ወደ እረፍቴ ወጣሁ ይድረስ ምስጋናዬ
ደጆች ቢዘጉብኝ በር ሆኖኝ ጌታዬ (2)
አዝ----------
በጥልቁ በረሃ ምግብ መጠጥ ሆኖኝ
መንገዴን አቀናው እጄን በአፌ አስጫነኝ
በእሳትና ውሃ መካከል አልፌ
ተመስገን እላለሁ ቅኔ ሞልቶት አፌ (2)
አዝ----------
የብቸኝነቴን ማዕበል ገስጿል
ለእኔ ብርሃን ሆኖ ለከሳሽ ጨልሟል
ቀስቱን እያጠፈ ታደገኝ ከስቃይ
የጌታዬ ሃሳብ ፍቅር ነው በእኔ ላይ (2)
አዝ----------
ትናንት ዛሬ ነገ ዘላለም ጠባቂ
የልቤን ፍላጎት ሳልነግረው አዋቂ
በባሕርይው ቅዱስ የሌለው አምሳያ
ስሙ ወደቤ ነው መልህቄን መጣያ
ሊቀ መዘምራን
ቴዎድሮስ ዮሴፍ