የመውጫ ፈተና ውጤት ከሁለት ቀናት በኋላ ይፋ ይደረጋል፡፡ - ትምህርት ሚኒስቴር
ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ከጥር 26-30/2017 ዓ.ም በመላ ሀገሪቱ በ87 የፈተና ማዕከላት መሰጠቱ ይታወቃል፡፡
ከፈተናው ጋር በተያያዘ በርካታ ቅሬታዎች ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ደርሰዋል፡፡ በተለይ የComprehensive Nursing ተፈታኝ ተማሪዎች፥ ፈተናው ከBlue Print ውጪ የተዘጋጀ እንደነበር በመግለፅ ትምህርት ሚኒስትር ለቅሬታቸው አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፡፡
የመውጫ ፈተና ውጤት ከሁለት ቀናት በኋላ ይፋ እንደሚደረግ ከትምህርት ሚኒስቴር መስማቱን የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሪዎች ህብረት ለቲክቫህ ገልጿል፡፡
ሚኒስቴሩ ከComprehensive Nursing የመውጫ ፈተና ጋር ተያይዞ የቀረበ ቅሬታን እያጣራ እንደሚገኝ ለህብረቱ አስረድቷል፡፡
በዚህም ከሁለት ቀናት በኋላ (ረቡዕ/ሐሙስ) አጠቃላይ የመውጫ ፈተና ውጤት ይፋ እንደሚደረግ ሚኒስቴሩ አሳውቋል፡፡
tikvahuniversity